TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Tigray

በአሜሪካ የህግ መወሰኛ ም/ቤት የቨርሞንት ክፍለ ሃገር ሴኔተር ፓትሪክ ሌሂ በትግራይ ጉዳይ መግለጫ አውጥተዋል።

መግለጫው ሲጀምር "በ1984 እአአ በኢትዮጵያ በተራዘመ ድርቅ ሳቢያ በስፋት በተከሰተው የምግብ እጥረትና በመንግሥት አድላዊ ፖሊሲዎች የተነሳ የደረሰውን ከባድ ረሃብ በዚያም ምክንያት ብዙዎቹ የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ሰውነታቸው በረሃብ ያለቀ ፤ 1 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የተሰደዱበትን የሚዘገንን ቸነፈር በደንብ አስታውሰዋለሁ"

ቆይቶ ዝናብ መጣል ጀመረ። ስደተኞቹም ወደቀያቸው ተመለሱ። ይሁን እንጂ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሃገሪቱ በየጊዜው ግጭት እና የበቂ ምግብ ዕጦት ተለይቷት አያውቅም ሲሉም የዩናይትድ ስቴትሱ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል አክለዋል።

ዛሬ የትግራይ ህዝብ ዘግናኝ በሆነ ደረጃ ጭካኔ የተመላበት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ጥቃት እየተፈጸመበት ነው ያሉት ሴኔተር ሌሂ ህዝቡ በአጣዳፊነት የሚያስፈልገው የምግብ እርዳታ እንዳይደርሰው የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ወታደራዊ ኃይሎች እንዲሁም ሌሎች ታጣቂ ቡድኖች እየከለከሉ ናቸው" ብለዋል።

“የአሜሪካ እና ሌሎችም ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደረጉ ቢሆንም የግጭቱ ተሳታፊ ወገኖች ግጭቱን አቁመው ሰላማዊ መፍትሄ ለመፈለግ የወሰዱት አንዳችም ትርጉም ያለው እርምጃ የለም" ሲሉ አክለዋል።

"ትግራይ ውስጥ የሚፈጸሙትን ግድያዎች፣ በግዴታ ከቀዬ ማፈናቀል፣ ወሲባዊ ጥቃቶች እና ሌሎችም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንዲሁም በውሃ አቅርቦት ስፍራዎችና በሆስፒታሎችና በመሰል የጤና ማዕከሎች ላይ የሚደርሰውን ውድመት የአሜሪካ መንግሥት አውግዟል።

ያንብቡ : telegra.ph/Tigray-06-07 #VOA

@tikvahethiopia
ባለፉት ቀናት በሱዳን ጉብኝት ያደረጉት የUSAID ኃላፊ ሳማንታ ፖውር ኢትዮጵያ ይገኛሉ።

ፖወር ወደኢትዮጵያ መግባታቸው በይፋ በሚዲያ ሳይታወቅ እና እሳቸው ሆነ ተቋማቸው ሳያሳውቁ ነው ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው መግለጫ የሰጡት።

ለመሆኑ በመግለጫቸው ምን አሉ ?

- ከሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል እና ከዶ/ር ሊያ ታደሰ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

- በትግራይ ክልል ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ የሰላም አማራጮች መታየት እንዳለባቸው ፣ ግጭት መቆም እንዳለበት ፣ ሁሉም ተፋላሚ ኃይሎች ወደ ድርድር መምጣት እንዳለባቸው ከሰላም ሚኒስትር ጋር መነጋገራቸውን ገልፀዋል።

- የትግራይ ያለው የውጥ ግጭት ሊፈታ የሚችለው በሰላማዊ አማራጭ ብቻ መሆን እንዳለበት መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።

- የአሜሪካ መንግስት ይሁን ሌሎች አካላት የሚሰጡት መገልጿቸው ሃሳቦች መፍትሄ ከማፈላለግ ሃሳብ ጋር የተያያዙ ናቸው ብለዋል።

- ለውጣዊ ግጭት ወታደራዊ አማራጭ መፍትሄ እንደማይሆን፣ ሁሉም አካላት ግጭቱን አስቸኳይ አቁመው ውይይት መጀመር እንዳለባቸው ተናግረዋል።

- ግጭቱ እየሰፋ መሄዱን ተናግረው ሰላማዊ መፍትሄ ካልተበጀለት ይበልጥ እየተስፋፋ በርካታ ሰዎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

- በአፋር እና አማራ ክልል ህወሃት በፈፀመው ጥቃት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸው አንስተዋል።

- ዓለም አቀፍ ህጎች መከበር እንዳለባቸው፣ ንፁሃን ለአላስፈላጊ ጉዳት መዳረግ እንደሌለባቸው ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ሰራተኞች ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተናግረዋል።

- ከሰሞኑ የአሜሪካ መንግስት ይፋ ካደረገው 149 ሚሊዮን ዶላር የሰብዓዊ ድጋፍ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት 45 ሚሊዮን ተጨማሪ በጀት ለኮቪድ ወረርሽኝ ለመከላከል ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል ለኢትዮጵያ ይፋ አድርገዋል።

#VOA

@tikvahethiopia
#Ethiopia

አጫጭር መረጃዎች #1፦

- የደብረሲና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ ጀምሯል፤ ነገር ግን በተሟላ አቅሙ ወደ ስራ አልገባም። አሁን ላይ የድንገተኛ ህክምና ፣ የተኝቶ ህክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው። ሆስፒታሉ የመብራት መቆራረጥ፣ የመድሃኒት እጥረትና የአምቡላንስ ችግር አለበት። የነበረው አንድ አምቡላንስ ለህልውና ዘመቻ ሄዶ እስካሁን ያልተመለሰ ሲሆን የአምቡላንስ አለመኖር በታካሚዎች ላይ ትልቅ ችግር ይፈጥራል ተብሏል። ሆስፒታሉ የጎደሉት እንዲሟሉለት ጥሪ ቀርቧል።

- ህወሓት በአማራ ክልል በከፈተው ጦርነት ሳቢያ ከሰሜንና ደቡብ ወሎ አካባቢዎች ተፈናቅለው ደብረብርሃን የቆዩ ወገኖች ወደ መኖሪያ ቀያቸው ሲመለሱ የደ/ብርሃን ህዝብና ሌሎች አካላት ስላደረጉላቸው መስተንግዶ አመስግነዋል። ደ/ብርሃን በጦርነት የተፈናቀሉ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ያስጠለለች ከተማ ስትሆን አብዛኛው ተፈናቃዮች አሁን ወደቀያቸው ተመልሰዋል።

- በሰሜን ኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ላይ የደረሰውን ውድመት ተከትሎ ዶ/ር ጥላሁን ጎሹ (Mihret Medical Supply) ከአጋሮቻቸው ጋር በመሆን ከነትራንስፖርታቸው 4.8 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጡ የህክምና መሳሪያዎችን፣ የህክምና ቁሳቁሶችን፣ ቪታሚኖችና አንድ ኮንቴነር ሙሉ መድሀኒቶችን በመርከብ ወደ ኢትዮጵያ ልከዋል።

- በሰሜን ወሎ ዞን የመቄት ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ላይ በደረሰው ውድመት ምክንያት የረሀብ አደጋ ማንዣበቡን ገልፀዋል። ከመፈናቀል እየተመለሱ ያሉትን ለመደገፍ በወር 1.2 ሚልየን ኲንታል እህል እንደሚያስፈልገው የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ገልፆ ሁኔታው ከአቅሙ በላይ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እጆቻቸውን እንዲዘረጉ ጥሪ አቅርባል።

#AMC #AmbFitsumArega #VOA

@tikvahethiopia
#Afar

በበራህሌ ስደተኞች መገደላቸው ተገለፀ።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት " በራህሌ መጠለያ " ሰፈር ላይ በተፈፀመ ጥቃት ስደተኞች መገደላቸውን አስታወቀ።

ተመድ አፋር ክልል ውስጥ እየተካሄደ ያለው ውጊያ ከኤርትራ የገቡ ስደተኞች የተጠለሉበትን ሠፈር በብርቱ እንደጎዳ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

በአፋር እና ትግራይ ክልል አዋሣኝ በሚገኘው በራህሌ መጠለያ ሠፈር ላይ በተጣለ አደጋ 5 ሰዎች ሲገደሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ መሸሻቸውን አመልክቷል።

ጥቃቱ ባለፈው ወር መጨረሻ ላይ መፈፀሙን ተመድ ተናግራል።

የታጠቁ ሰዎች ጥር 26 ወደ መጠለያ ሠፈሩ ከገቡ በኋላ " ቢያንስ 5 ስደተኞችን መግደላቸውንና ብዙ ሴቶችን ጠልፈው መውሰዳቸውን " ከጥቃቱ የተረፉ ሰዎችን ጠቅሷል።

ተመድ ባወጣው መግለጫ በመጠለያው ላይ ጥቃት ያደረሱትን ኃይሎች ማንነት አልገለፀም።

ነገር ግን በዚህ ሳምንት አፋር ክልል ዋና ከተማ ሰመራ የደረሱ ሰዎች ጥቃቶቹን ያደረሰው ህወሓት መሆኑን ለAFP ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ከስደተኞቹ አንዱ የሆኑት መሃሙዳ አህመድ " አንድም የመንግሥት ደጋፊ ታጣቂ ሌለበት አካባቢ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈፀመ ጥቃት ነው " ሲሉ ተናግረዋል። " ወታደሮች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ተኩስ ሲከፍቱ አይቼ አላውቅም። የሚዋጋቸው ወታደርም አልነበረም። የነበሩት ሴቶችና ህፃናትን ጨምሮ ሲቪሎች ብቻ ነበሩ። እናም ከባድ መሣሪያዎችን ይተኩሱ ነበር " ብለዋል።

የአፋር ክልል መንግሥት ባለሥልጣናት እና የብሄራዊ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳዮች አስተዳደር ለጥቃቱ ተጠያቂው ህወሓት ነው ማለታቸውን AFP በዘገባው ላይ ጠቅሷል።

#AFP #VOA

@tikvahethiopia
" የዝንጀሮ ፈንጣጣ / መንኪፖክስ / ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብለን አንጠብቅም " - የዓለም የጤና ድርጅት

እስካሁን በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች መያዙ የታወቀው መንኪፖክስ ወይም የዝንጀሮ ፈንጣጣ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ደረጃ ይደርሳል ብለው እንደማይጠብቁ የዓለም የጤና ድርጅት ከፍተኛዋ የበሽታው ኤክስፐርት ተናገሩ።

ያን ይበሉ እንጂ በሽታው እንዴት እንደሚስፋፋ ሆነ ከአያሌ አሰርት በፊት የፈንጣጣ መከላከያ ክትባት ዘመቻ መቋረጡ ያስከተለው አንድምታ ይኖር እንደሆን ጨምሮ ብዙ የማይታወቁ ነገሮች መኖራቸውን አልደበቁም።

ዶክተር ሮዛሙንድ ሉዊስ በሰጡት ማብራሪያ ድርጅታቸው መንኪፖክስ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወይም በአየር በትንፋሽ ይተላለፍ እንደሆን በተጨማሪም የህመም ምልክት የሌላቸው ሰዎች በሽታውን ያስተላልፋሉ ወይ የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ጥያቄዎችን ይዞ እየመረመረ መሆኑን አመልክተዋል።

ካሁን ቀደም በሽታው በተቀሰቀሰባቸው ጊዜያት በቀላሉ የሚዛመት እንዳልሆነ ታይቷል ያሉት የዓለም የጤና ድርጅቱ ባለሙያ አሁንም ሥርጭቱን ለመቆጣጠር ጊዜ እንዳለ መግለፃቸውን ቪኦኤ /VOA ዘግቧል።

#VOA

@tikvahethiopia
#ኔዘርላንድ #አቶእሸቱ_ዓለሙ #ደርግ

በኔዘርላንድ የሚገኝ የይግባኝ ፍ/ቤት እ.አ.አ በ2017 ዓ.ም በጦር ወንጀለኝነት ጥፋተኛ የተባሉትን አቶ እሸቱ ዓለሙን የዕድሜ ልክ እስራት ባሳለፍነው ረቡዕ አጽንቷል።

የ67 ዓመቱ ተከሳሽ #በኢትዮጵያ በ1960 ዎቹ እና በ1970ዎቹ በነበረው ጨካኝ ኮሚኒስት ሥርዓት ወቅት የጦር ወንጀል ፈጽመዋል ሲል በደች የሚገኝ ፍ/ቤት የጥፋተኝነት ብይን ከ5 አመታት በፊት ሰጥቶ ነበር።

አቶ እሸቱ ዓለሙ የ2017 ፍርድ እንዲቀለበስላቸው ይግባኝ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም በሄግ የሚገኘው የይግባኝ ፍርድ ቤት ግን በ1960ዎቹ መጨረሻ እና በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ በኢትዮጵያ በኮ/ሌ መንግሥቱ ኃ/ማሪያም አመራር በተፈጸመው የቀይ ሽብር ዘመቻ ተሳታፊ ነበሩ ሲል ውሳኔውን አጽንቷል።

አቶ እሸቱ በመታመማቸው ምክንያት በይግባኝ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ አልተገኙም ነበር።

የጉዳዩ ባለሞያዎች እንደሚሉት ከሆነ ወደ 150,000 የሚጠጉ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ምሑራንና የፖለቲካ ሰዎች በወቅቱ የነበረው ስርዓት ተቃዋሚዎቹን ለማጥፋት ባደረገው ዘመቻ በጭካኔ ተገድልዋል።

አቶ ዓለሙ እአአ በ1978 በጎጃም ክፍለ ሀገር የደርግ ተወካይ የነበሩ ሲሆን በወቅቱ ደርግ በክፍለ ሀገሩ ከተቃዋሚዎቹ አንዱ ከነበረው ከኢህአፓ ጋር ሲፋለም ነበር።

ፍርድ ቤቱ እንዳለው " በተከሳሹ እውቅናና ተሳትፎ " የጦር ወንጀል በክፍለ ሃገሩ ይፈጸም ነበር።

በመቶዎች የሚቆጠሩና አብዛኞቹ ወጣት ተማሪዎች የሆኑት ሰለባዎች ካለ በቂ ምክንያት ተይዘው ኢሰብአዊ በሆነ ሁኔታ የታሰሩ ነበር።

አንዳንዶች በከፋ ሁኔታ ሲደበደቡ አብዛኞቹ ደግሞ ካለ ፍርድ ሂደት ወደ እስር ቤት ይጋዙ ነበር። በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰለባዎች ደግሞ በሞት ተቀጥተዋል።

" የሞት ቅጣቱ በተከሳሹ አመራር ሰጪነት በጭካኔ ይፈጸም ነበር " ብሏል ፍ/ቤቱ።

አቶ ዓለሙ በ2017 የጥፋተኝነት ውሳኔ በተሰጠበት የፍርድ ሂደቱ መጀመሪያ ላይ በስሜት ተሞልተው ባደረጉት ንግግር በደርግ ላይ የቀረበውን ውንጀላ ተቀብለው ነገር ግን እርሳቸው በግላቸድ የፈፀሟቸው አለመሆናቸውን ለዳኞች ገልፀው ነበር።

አቶ ዓለሙ በደች ፍ/ቤት ጉዳያቸው ሊታይ የቻለው ከ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ጀምሮ ኔዘርላንድ ውስጥ መኖር በመጀመራቸውና በ1998 የሀገሪቱን ዜግነት በመቀበላቸው ነው።

#ASSOCIATED_PRESS | #VOA

@tikvahethiopia
#የWFP_ማጠንቀቂያ

የተመድ ዓለም ምግብ ፕሮግራም ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረኀብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት እንደሚጀምር አስጠንቅቋል።

የድርጅቱ ዋና ኃላፊ ዴቪድ ቤስሊ ባለፈው ዐርብ  ቃለ ምልልስ ሰጥተው ነበር።

ቤስሊ ምን አሉ ?

- ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ #በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረሃብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት ይጀምራል።

- ባለፈው ዓመት፣ ከአሜሪካና ከጀርመን የተገኘውን ተጨማሪ ድጋፍ ይደነቃል ፤ ቻይና፣ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት፣ ቢሊየነር ባዕለ ጸጋዎች እና ሌሎችም ሀገራት፣ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ድጋፋቸውን ሊያፋጥኑ ይገባል።

- በ49 ሀገራት ውስጥ አስቸኳይ የሆነ #የምግብ ርዳታ የሚያስፈልጋቸውን 350 ሚሊዮን ሰዎች ለመርዳት 23 ቢሊየን ዶላር ሲሆን ይህ ገንዘብ ላያገኝ ይችላል ፤ ይህ ደግሞ በከፍተኛ ኹኔታ አስጨንቆኛል።

- አሜሪካ የምትሰጠውን የገንዘብ ርዳታ ከ3.5 ቢሊዮን ዶላር ወደ 7.4 ቢሊዮን አሳድጋለች፤ በተመሳሳይ ጀርመንም ከ350 ሚሊየን ዶላር ወደ 1.7 ቢሊዮን ከፍ አድርጋለች ፤ በዓለም ሁለተኛ ትልቁ የሆነውን ኢኮኖሚ የያዘችው ቻይና ባለፈው ዓመት ለተቋሙ የሰጠችው ገንዘብ 11 ሚሊየን ዶላር ብቻ በመሆኑ ድጋፏን ልታሳድግ ይገባል።

- #የነዳጅ_ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ከመጨመሩ ጋራ ተያይዞ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት የበለጠ እገዛ ሊያደርጉ ይችላሉ። በተለይ ከምሥራቅ አፍሪካ፣ ከሰሐራ እና ከሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ጋራ ግንኙነት ያላቸው የሙስሊም ሀገራት የተሻለ አስተዋፅኦ ማድረግ ይችላሉ።

- ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባቸው በአፍሪካ የሳሕል ክልል የሚገኙ ሀገራትና ምሥራቅ ሶማሊያ ፣ ሰሜናዊ ኬንያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣  #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ይገኙባቸዋል።

- የዓለም መሪዎች፣ ከፍተኛ የሆነ አለመረጋጋትን ሊያስከትሉ የሚችሉ የሰብአዊ ርዳታ ክፍተቶች ለአሉባቸው ሀገራት ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል።

ዴቪድ ቤስሊ በዓለም ትልቁ ሰብአዊ ርዳታ ሰጪ በሆነው ተቋም የነበራቸውን ሥልጣን በመጪው ሳምንት ለአሜሪካ አምባሳደር ሲንዲ ማኬይን ያስረክባሉ።

#VOA

@tikvahethiopia
" እኛ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ? በረሃብ ማለቅ አለብን ? " - ተፈናቃዮች

ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ በ2015 ዓ/ም በነበረው ማንነት ተኮር ግጭት የተነሳ ቤት እና ንብረታቸውን ጥለው ወደ አማራ ክልል፤ ቻግኒ የመጡ ተፈናቃዮች እርዳታ እየተደረገልን አይደለም፤ በረሃብ ምክንያት ባለፉት ሁለት ሳምንታት 2 ህፃናት ህይወታቸው አልፏል ብለዋል።

በቻግኒ የሚገኙት 2000 የሚደርሱ ተፈናቃይ ወገኖች ሲሆኑ በግለሰብ ፍርስራሽ ቤቶች እና ጅምር ፎቆች ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ።

የተፈናቃዮቹ አስተባባሪ አቶ መሀመድ ሀሰን፦

" ካለፈው ሳምንት ብቻ ሁለት ህፃናት በረሃብ ምክንያት ሞተውብናል።

እኛ እስከ ዞን እስከ ክልል ድረስ ወስደን ደብዳቤ አስገብተናል። ዞኑ እራሱ ፈርሞ የሞቱትን ሰዎች ዝርዝር በዛ ላይ አልተጠቀሱም ግን እንደሞቱ ሪፖርት አድርገናል።

በረሃብ ምክንያት ህፃን 34፣ ትላልቅ ሰዎች 21 በአጠቃላይ 55 ሰዎች እንደሞቱብን ሪፖርት አድርገናል።

እኛ ሰው ጠግቦ ይደር እያልን አይደለም ያለነው ቢያንስ ቀምሶ ይደር ህይወት ይዳን ነው። ምናለ መንግስት እንኳን ባያግዘን ሌላ ድርጅቶች ገባ ብለው ቢያግዙን ይሄ ሁሉ ጉዳት ይሄ ሁሉ ህዝብ እንዴት በረሃብ ይሞትብናል ?

ሰዎች ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሄድ ብለው የቀን ስራ ሰርተው እንዳበላ ያልታደሰ መታወቂያ ይዛችሁ አትሄዱም ተብለን ተዘግቶብናል። ተንቀሳቅሰን የቀን ስራ ካልሰራን እንዴት አድርገን ነው ህይወታችንን ማቆየት የምንችለው ? መንግሥትም እያገዘን አይደለም።

መንግሥት በቅርብ ወደሀገራችሁ ትገባላችሁ የሚል ነገር አንስቷል። ይሄም ቢሆን ደስ ይለናል በተለያዩ ቦታዎችም ምዝገባ አለ የሚባል ነገር አለ እዚህ ዞን ግን እስካሁን የመጣም ሆነ የተጠየቅነው ነገር የለም።

ወይ እርዳታ አልተደረገ፣ ወይ ወደተፈናቀልንበት ቦታ መንግስት ያለውን ነገር አረጋግጦ እየመለሰን አይደለም፣ እንዴት ነው የምንሆነው ኢትዮጵያዊ አይደለንም እኛ በረሃብ ማለቅ አለብን ? "

ከተፈናቃዮች መካከል አንዲት 60 ዓመት እናት፤ " እመጫትም ወልዳ የምትበላው የምትቀምሰው አጥታ ቁጭ ብለናል። እየተሰቃየች ነው ያለችው ተቸግረን ነው ያለነው በጣም በጣም ተሰቃይተናል " ብለዋል።

በምስራቅ ወለጋ ለ52 ዓመታት እንደኖሩ የሚናገሩት የ75 ዓመት እድሜ ያላቸው አዛውንት አቶ ሀሰን መሀመድ ከ8 ልጆቻቸው 5 ወንድ ልጆቻቸው በግጭቱ እንደተገደሉና አሁን ላይ ከቀሪ 3 ሴት ልጆቻቸው ጋር በቻግኒ የግለሰብ ፍርስራሽ ቤት ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ገልጸዋል።

የሚላስ የሚቀመስ የለንም የሚሉት አዛውንቱ " በጣም አጣዳፊ የሆነብን የምግብ ጉዳይ ነው፤ ልጆችን እየቀብርን ነው በረሃብ ምክንያት መንግስት ሊሰማን አልቻለም አላወቀንም እንዳንል አንድ ጊዜ እርዳታ መጥቶልናል፤ ስማችንም በኮምፒዩተር ገብቶ ይታወቃል። መጠለያ አልተሰጠንም የትም ተበትነን በየከተማው በየበረዳው ተቀምጠን ነው በደል የደረሰብን ብርዱ ፀሀዩ ረሃቡ እየተፈራረቀብን ነው " ብለዋል።

የቻግኒ የአደጋ መከላከልና የምግብ ዋስትና ፅ/ቤት ተወካይ ባለሞያ አቶ የሱፍ ሁሴን ምን አሉ ?

- ባለፈው ዓመት ግንቦት ላይ ነው እርዳታ የመጣው። አንዴ ተሰጣቸው ቆመ እስካሁን የለም።

- በረሃብ ተጎድተው ታመው የተኙ ሰዎች አሉ፣ በቂ ህክምና እንዳያገኙ ብር የላቸውም።

- ሃምሳ አምስት ሰው እንደሞተባቸው ለኛ ሪፖርት ሰጥተውናል። እሱን ደግሞ ለዞን ለክልል በደብዳቤ አሳውቀናል። ኮሚቴም ሄዶ እንዲያነጋግር ተደርጓል።

- ክልሉ 'እርዳታ አለ ግን ለማድረስ የመንገድ የፀጥታ ሁኔታ ችግር በመሆኑ ማድረስ አልችልም' የሚል ነው።

ያንብቡ ፡ https://telegra.ph/VOA-11-29 #VOA

@tikvahethiopia
#CPJ

ኤርትራ 16 #ጋዜጠኞችን_በማሠር ከአፍሪካ ቀዳሚውን ሥፍራ እንደምትይዝ በጋዜጠኞች መብት ላይ አተኩሮ የሚሠራው ሲፒጄ ያለፈውን የፈረንጆቹ 2023 ዓ/ም በተመለከተ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

16 ጋዜጠኞችን አሥራ የያዘችው ኤርትራ፣ በዓለም 7ኛ ደረጃን እንደምትይዝም ሲፒጄ ገልጿል።

አንዳንዶቹ ጋዜጠኞች በዓለም ለረጅም ግዜ የታሠሩ እንደሆነም ሪፖርቱ አመልክቷል።

በሁሉም ጋዜጠኞች ላይ ክስ ተከፍቶ እንደማያውቅም ሪፖርቱ ጠቁሟል።

እስካለፈው ወር ድረስ በአፍሪካ የታሠሩት ጋዜጠኞች ቁጥር 47 እንደነበር ያመለከተው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ 8 ጋዜጠኞችን በማሠር፣ ካሜሩን ደግሞ 6 በማሠር የሁለተኛና እና ሶስተኛ ረድፍ ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።

" በኢትዮጵያ በእሥር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች ቁጥር፣ በአገሪቱ የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን የሚገኙበትን አስቸጋሪ ሁኔታ ያስያል ሲል " ሲፒጄ በሪፖርቱ አመልክቷል።

ባለፈው ዓመት በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረውን ጦርነት ያስቆመ የሠላም ስምምነት ቢፈረምም፣ በአማራ ክልል በአካባቢው በሚገኙ ኃይሎች እና በፌዴራሉ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ግጭት አሁንም እንደቀጠለ ነው ያለው ሲፒጄ፣ ስምንቱም ጋዜጠኞች የታሠሩት ግጭቱን በተመለከተ ዘገባ ካወጡ በኋላ መሆኑን አስታውቋል።

ባለፈው ዓመት በመላው ዓለም ላይ የታሠሩ ጋዜጠኞች ቁጥር እስከአሁን ከታዩት ከፍተኛ ሆኑ ከተመዘገበው ዓመት ጋር እንደሚቀራረብ ያመለከተው ሲፒጄ፣ የእስራኤል እና ሐማስ ጦርነት ባለፈው ጥቅምት መጀመሩን ተከትሎ፣ እስራኤል ጋዜጠኞችን በብዛት ካሰሩ አገራት ጎራ መቀላቀሏን አስታውቋል።

ቻይና 44 ጋዜጠኞችን በማሠር ቀዳሚውን ሥፍራ ስትይዝ፣
ሚያንማር 43 በማሠር ሁለተኛ
➡️ ቤላሩስ 28 ጋዜጠኞችን በማሠር ሶስተኛ ሥፍራን ይዘዋል።

#VOA #CPJ

@tikvahethiopia
#Rwanda #UK

ዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን እንደተቃረበ ቪኦኤ ዘግቧል።

የዕቅዱ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስደተኞቹን #በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና በላይኛው ምክር የቀረበውን ተቃውሞ ለመቋቋም የታለመው ይህ ሕግ በዚህ ሳምንት በሃገሪቱ ፓርላማ ይድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‘ የሩዋንዳ ዕቅድ ’ የሚል ቅጽል የተሰጠው ይህ ውጥን ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ‘ሕገ ወጥ ስደተኞችን ወደዚያች አገር የሚያጓጉዙ ጀልባዎች እንቅስቃሴ’ ለማስቆም ለገቡት ቃል ‘ወሳኝ እርምጃ ነው’ ተብሏል።

የሱናክ ቃል አቀባይ ዴቭ ፓሬስ ምን አሉ ?

" የእንግሊዝ ፓርላማ በያዝነው ሳምንት በሕገ ወጥ አስተላላፊዎች ከፍተኛ እንግልት እና ብዝበዛ የሚፈጽምባቸውን ሰዎች ህይወት የሚታደግ ህግ የማጽደቅ እድል ያገኛል።

አሁን ባለው አካሄድ መቀጠል እንደማንችል ግልፅ ነው። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜው አሁን ነው። " ብለዋል።


በአነስተኛ ጀልባዎች ተጓጉዘው የእንግሊዝ ቻናልን በማቋረጥ ከዚያ የሚደርሱትን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሩዋንዳ ለማዛወር እና በቋሚነትም ኑሯቸውን በዚያ እንዲያደርጉ በማቀድ ሁለቱ አገሮች የተፈራረሙት ስምምነት 2 ዓመታት አስቆጥሯል።

በፍርድ ቤት የታገደው ዕቅድ እንግሊዝን በትንሹ 470 ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣት እንደሚችል ቪኦኤ በዘገባው አስፍሯል። #VOA

@tikvahethiopia
#CAR

የ77 ዓመቱ የቀድሞው የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ፍራንሷ ቦዚዜ ላይ የእስር ማዘዣ ትዕዛዝ ወጣ።

ማዘዣው የወጣው ሠራዊታቸው ከእአአ 2009 እስከ 2013 ባለው ጊዜ ውስጥ በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል ፈጽሟል በሚል ነው።

ማዘዣውን ያወጣው በባንጊ ላይ የተሰየመውና ከሃገር ውጪ ካሉ ፍርድ ቤቶች ጋራ የሚሠራው ልዩ የወንጀል ችሎት ነው።

ይህ ችሎት በእ.አ.አ 2015 በተመድ እገዛ የተቋቋመ እንደሆነ ተገልጿል።

የቀድሞ የሀገሪቱ መሪ ቦዚዜ ፦
- ግድያ፣
- አስገድዶ መሰወር፣
- ሰቆቃ፣
- መድፈር እና ሌሎች ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን ፈፅመዋል በሚል ተከሰዋል።

ቦዚዜ በመፈንቅለ መንግስት ወደ ስልጣን የመጡት በእ.አ.አ 2003 ሲሆን ከአስር (10) ዓመታት በኋላ ከወንበራቸው ተወግደዋል።

ቦዚዜ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ #በስደት ጊኒ ቢሳዉ የሚገኙ ሲሆን፣ ከዛ ሆነው ዋናኛ የሚባል አማጺ ቡድን በመምራት ላይ ይገኛሉ።

ጊኒ ቢሳዉ ተጠርጣሪውን ቦዚዜ #ይዛ እንድታስረክብ ተጠይቋል። #VOA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር #ታንዛኒያ ለሳምንታት በዘለቀ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት 155 ሰዎች ሲሞቱ ፤ 236 ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ጠ/ሚ ቃሲም ማጅዋሊ ተናግረዋል። በዚህ ሳምንት በጎረቤት #ኬንያ በደረሰው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 35 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። 40,000 ሰዎች  ደግሞ ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል።…
#Kenya

በጎረቤት ኬንያ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 188 ደርሷል።

ካለፈው መጋቢት ጀምሮ በደረሰው አውዳሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 188 መድረሱን የሀገር አስተዳደር ሚኒስቴር አሳውቋል።

እስካሁን ያልተገኙ በርካታ ሰዎች መኖራቸውም ተገልጿል።

በኬንያና ሌሎች የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች በተከታታይ እየጣለ ባለው ከባድ ዝናብ የብዙ ሰዎች ህይወት እየጠፋ ሲሆን የከፍታ ቦታዎች መናድም ነዋሪዎችን ካለመጠጊያ አስቀርቷል፡፡

መንገዶችን ድልድዮችን እና ሌላም የመሰረተ ልማት አውታሮችን ውድሟል። #VOA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #Ethiopia አሜሪካ በአማራ ክልል ይንቀሳቀሳሉ ያለቻቸው የፋኖ ኃይሎች " ውይይትን አልቀበልም " ማለታቸውን በመግለጽ ይህ " ለራሳቸውም አይጠቅማቸውም " አለች። ሀገሪቱ ይህን ያለችው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር በሆኑት ኢርቪን ማሲንጋ አማካኝነት ነው። አምባሳደሩ ፤ " በአማራ ክልል ውስጥ ውጊያ እያደረጉ የሚገኙት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ኃይሎች ' ውይይትን አንቀበልም…
#የአሜሪካ_አቋም!

" ግጭት የኢትዮጵያውያንን #ስቃይ_ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም " - አሜሪካ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ያላትን ፖሊሲ በተመለከተ ምን አሉ ?

- በትጥቅ ግጭት ውስጥ የገቡ አካላት፣ ግጭት አቁመው በንግግር ሰላምን ሊያሰፍኑና የሰብአዊ መብቶችን ማክበር አለባቸው።

- የታጠቁ ቡድኖች ፖለቲካዊ ዓላማዎቻቸውን በአመፅ ለማሳካት እየገፉ ናቸው ፤ መንግስትም ይህን ለመከላከል የሚወስዳቸው ርምጃዎች፣ በፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ የማይካድ ተጽእኖ አለው። ውይይትን ወደ ጎን ያለው ይህ አካሔድ የመብት ጥሰቶች እንዲቀጥሉ አድርጓል።

- ሰላማዊ ዜጎች፣ በተለያዩ ኀይሎች ከሕግ ውጭ ግድያ፣ የዘፈቀደ እስራት፣ አስገዳጅ ስወራ፣ ከግጭት ጋራ የተያያዘ ጾታዊ ጥቃት እና ሌሎችም ጥቃቶች እየተፈጸሙባቸው መሆኑን የሚገልጹ ዘገባዎችን ማየቱ እጅግ ያሳዝናል።

- የተፈጸሙ ጥፋቶች እውነተኛና ግልጽ የሽግግር ፍትሕ ሒደት በተከተለ የተጠያቂነት አሰራር በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል።

- ሽፍታዎች፣ የታጠቁ ቡድኖች፣ አንዳንዴም የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች፤ በህይወት የመኖር፣ የሰብዓዊ ክብርን፣ መከበርን በመሰሉ መብቶች ላይ ያለምንም ተጠያቂነት ጥሰቶች ይፈጽማሉ።

- በጦርነት እና ግጭት ወቅት እንኳ የሰብዓዊ መብቶች ሊረሱ አይገባም።

- ሁሉም ሀገር ራሱን የመከላከል ህጋዊ መብት አለው፤ ሆኖም ሀገራት ራሳቸውን የሚከላከሉበት መንገድ ያለምንም ጥርጥር የወደፊት ግጭቶችን አካሄድ የሚወስን ነው።

- ሀገር የመከላከያ መንገዶቹ በዛሬው እና በወደፊቱ የማህብረሰብ ትስስር ላይ ይበልጡኑ ተጽዕኖ የሚያሳድር ነው።

- የታጠቁ ወገኖች የፖለቲካ ግባቸውን ከውይይት ይልቅ በግጭት ለማሳካት ሲሞክሩ፤ ለሚፈጸሙ በደሎች ሁኔታዎች የተመቻቹ ይሆናሉ።

- በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ታጣቂ ቡድኖች ንግግር / ድርድር አንቀበልም ማለታቸው እራሳቸውን ነው የሚጎዳቸው። በአማራ ያሉ በርካታ ሰዎች " የቆሙለት ዓላማ ፍትሃዊ ነው " የሚል እምነት/አላቸው ይህንኑ መከራከሪያቸውን ከግጭት ይልቅ በውይይት ማቅረብ አለባቸው።

- በአማራ ክልል ውጊያዎች የሚቀጥሉ ከሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች እንዳለው በውጤቱ የሚሰቃዩት ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።  

- ህወሓት በኀይል ወሰን ለማስመለስ ከሚደረግ እንቅስቃሴ መቆጠብ አለበት።

- የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ኃይሎች በድርድር ተስፋ ሳይቆርጡ መተማመን ለመገንባት የሰላም ውይይትን ሊቀጥሉ ይገባል።

- ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በውስጣዊ ግጭቶች እየታመሰች ትገኛለች።

- የኢትዮጵያ መንግስት የአገሪቱን ችግሮች በኀይል ለመፍታት ከሚያደርገው ጥረት መቆጠብ አለበት። በእስር ላይ የሚገኙ ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎችን መፍታቱ ጠቃሚ ነው፤ ያን ተፈጻሚ ማድረግ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ውይይት ሊያግዝ ይችላል።

- ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈጸም ይገባል።

- ሁሉም የታጠቁ ተዋናዮች፣ በመላ አገሪቱ አዲስ የሕዝብ መፈናቀልን ጨምሮ ለሰዎች ስቃይ ምክንያት ከመሆን መገታት አለባቸው።

- የታጣቁ ኃይሎች ት/ቤቶችን፣ ጤና ተቋማትንና የውኃ መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ማድረግ ማቆም አለባቸው። የተሟላና ያልተገደበ ሰብአዊ አቅርቦት ሊኖር ይገባል። ይህም ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ማድረግን ይጨምራል።

- ግጭት የኢትዮጵያውያንን ሥቃይ ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም። ውይይት ትኩረት ሊደረግበት ይገባል።

- ምንም እንኳን ፍጹም ሊሆን ባይችልም፣ ሁሉም ወገኖች የአገራዊ ምክክሩን ዕድል ሊጠቀሙበት ይገባል።

#USEmbassyAddisAbaba
#VOA
#EthiopiaInsider

@tikvahethiopia
#OROMIA #PEACE

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ... ለሰላም ክፍት ነን ድርድሮችም እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም ቢሆን ያሉ ችግሮች #በሰላም እንዲፈቱ መንግሥት #ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

የክልሉ መንግሥት አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በአዲስ አበባ እንደመከሩ ተነግሯል።

በምክክሩ ላይ የተገኙት የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ውይይቱ ልማትና ጸጥታ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ሲሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

በውይይቱ ፦

- የልማት ስራ ያለ ሰላም ውጤት አልባ እንደሆነ / ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት እንደሆነ ፤

- ሰው ሰርቶ የሚበላው ፣ ወልዶ የሚስመው ሰላም ሲኖር እንደሆነ አጽንኦተ ተሰጥቶበታል ብለዋል።

" ሰላም ለመንግሥት ብቻ የተተወ ስላልሆነ እንዴት ነው አብሮ መስራት የሚቻለው ? " የሚለውም መነሳቱን አስረድተዋል።

" መንግሥት እና ሸኔ የጀመሩት ድርድር ፤ በተለያየ ምክንያት አኩርፈው ጫካ የገቡ ነፍጥ ያነገቡ ጓዶች አሉ ፤ መንግሥት በሆደ ሰፊነት ዛሬ ነገ ሳይል እነዚህን አካላት ጠርቶ በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር አለበት ይህ ሲደረግ ደግሞ ለሰዎቹ እውቅና ተሰጥቶ የህግ ከለላ ተሰጥቶ ነው ውይይት መደረግ ያለበት " የሚለውም መነሳቱን ገልጸዋል።

" በመንግሥት በኩል ' ዛሬም ቢሆን ክፍት ነው እንነጋገራለን ፣ ችግሮችን በጋራ ተነጋግረን እንፈታለን ' የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አሁንም ቢሆን የክልሉ መንግሥት በውይይት ያምናል ብለዋል።

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ሙሉ ትኩረታችን ወደ ሰላም ማምጣት ነው ያለብን። የፈለግነውን ነገር በአዳራሽ መወያይት ይቻላል። ጥረቶች ብዙ ነው ያደረግነው አሁንም ለሰላም ክፍት ነን እኛ 3ኛ ዙር ይሁን፣ 5ኛ ዙር ይሁን ፣ 10ኛ ዙር ድርድሮች እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " ብለዋል።

#Ethiopia
#Oromia #VOA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OROMIA #PEACE " የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ... ለሰላም ክፍት ነን ድርድሮችም እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም ቢሆን ያሉ ችግሮች #በሰላም እንዲፈቱ መንግሥት #ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል። የክልሉ መንግሥት አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በአዲስ አበባ…
ኦነግ እና ኦፌኮ በውይይቱ ተገኝተው ነበር ?

#አልተገኙም

" ውይይት መደረጉን የሰማነው እራሱ በሚዲያ ነው " - ኦፌኮ

በኦሮሚያ ክልል ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ ፓርቲዎች ጋር የክልሉ መንግሥት አድርጎታል በተባለው ውይይት ላይ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) #አልተሳተፉም

የኦፌኮ ዋና ፀሀፊ አቶ ጥሩነህ ገምታ ለቪኦኤ ሬድዮ ፥ " ውይይቱ መደረጉን የሰማነው ከብዙሃን መገናኛ ነው። እንደ ግለሰብ ይሁን እንደ ተቋም የደረሰን ጥሪ የለም የኮሚኒኬሽን ክፍተቱ ከማን በኩል እንደሆነ አላውቅም " ብለዋል።

ኦፌኮ የክልሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል ቢሆንም ባለው ቅሬታ ሙሉ ተሳትፎ እያደረገ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

አቶ ጥሩነህ ፤ ለውይይት በም/ቤት ይሁን በመንግስት ጥሪ አልደረሰንም ብለዋል።

የኦነግ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ በበኩላቸው ፤ ፓርቲያቸው በውይይቱ #እንዳልተሳተፈ ገልጸዋል።

" ለውይይቱ ጥሪ ሊደረግ ይችላል እኛ ግን የምንፈልገው በአንድ አካል አቅራቢነት የሚደረገውን ውይይት ሳይሆን ሁሉም በእኩልነት የሚሳተፍበትን ውይይት ነው። " ብለዋል።

" የምንፈልገው አንድ ሀገርን የሚያስተዳደር መንግሥት በሚሰጥህ ቦታ ተወስኖ መወያየት ሳይሆን እራሳችንን የመፍትሄ አካል ነን ብለን የምናይ አካላት በአንድ ላይ ሆነን በተመሳሳይ ድምጽ ተወያይተን ዘላቂ መፍትሄ የምናስቀምጥበት ካልሆነ ኦነግ በአንድ አካል ጥሪ የሚሳተፍበት መድረክ አይኖርም " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሞን ችግር የሚፈተው በእውነታ ላይ የተሰመሰረተ አካታች ውይይት እንደሆነ የገለጹት አቶ ለሚ ፤ ውይይት ሂደቱን ጠብቆ አካታች በሆነ መልኩ መከናወን አለበት አሁን ያለው አካሄድ ሂደቱን ያልጠበቀ ቅንነት የሌለው በአንድ አካል ብቻ ተጎትቶ እየሄደ ያለ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ም/ቤት ሰብሳቢ እና የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዜዳንት አቶ ሰለሞን ታፈሰ ኦነግ እና ኦፌኮ ከውይይት መቅረታቸውን አረጋግጠዋል።

" በድረገጻችን ላይ ለቀናል፣ በዋትስአፕ ላይ ተለቋል። እንደምንሄድ ኮሚቴው ሲወስን ተለቋል። በአካል አነጋሬያለሁ የሚመለከታቸውን ኦሮሚያ የኢትዮጵያ እምብርት ናት እናተ ስለሚመለከታችሁ ለምን አብረን አንሄድም? ብዬ ነግሬያቸዋለሁ። ተጋብዘዋልም " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

#Ethiopia
#Oromia #VOA
#OFC #OLF

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Kenya

ጎረቤት ኬንያ ታቃውሞ እየናጣት ነው።

መንግሥት በታክስ ላይ ጭማሪ ሊያደርግ ማቀዱን ተከትሎ በተለይም ወጣቱ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥቷል።

ከወጣቶቹ ሰልፍ ጋራ በተያያዘ ትላንት አንድ ሰው #ተገድሏል፡፡

ግድያው የተፈጸመው በፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ነው ተብሏል።

ዛሬም በናይሮቢና የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲካሄድ ውሏል።

ተቃዋሚዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሔድ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራታቸው ተነግሯል።

ይህ በኬንያ ወጣቶች መሪነት የተነሳው እና ባለፈው ማክሰኞ በናይሮቢ ከተማ ተጀምሮ በመላው አገሪቱ የተሰራጨው ተቃውሞ በመጭው ማክሰኞ ብሔራዊ የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

ተቃዋሚዎቹ ለምን አደባባይ ወጡ ?

ተቃዋሚዎች በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደስተኛ አይደሉም።

አካሄዳቸውም ለብዙ ኬንያውያን ኑሯቸውን አስቸጋሪ ማድረጉን ይገልጻሉ።

በተለይም መንግሥት አሁን ያዘጋጀው የታክስ ጭማሪ ረቂቅ አዋጅ የህዝቡን ኑሮ የሚያመሰቃቅል እንደሆነ በመግለጽ እየተቃወሙ ነው።

የታክስ ጭማሪውን በመቃወም ለወራት በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ሲደረግ ቆይቶ ነው ወደ ተቃውሞ ሰልፍ የተቀየረው።

የኬንያ መንግሥት ምን ይላል ?

መንግሥት የታክስ ጭማሪ ሊያደርግ ያቀደው ብድር ለመክፈል እና ለልማት ሥራዎች እንደሆነ ገልጿል።

ተቃውሞውን ተከትሎ ከረቂቅ አዋጁ ላይ የተወሰኑትን እንደሚተው ቢያስታውቅም ተቃውሞው ግን ዛሬም ቀጥሏል።

የታክስ ጭማሪው ምን ላይ ነው ?

መንግሥት በያዘው እቅድ የታክስ ጭማሪው በተለያዩ ሸቀጦች ላይ የሚደረግ ነው።

በነዳጅ ላይ ሊጨመር የታሰበው 9 ሺልንግ ሲሆን ጭማሪው ለፈረሱ መንገዶች መጠገኛ እንደሚሆን የአዋጁ አርቃቂዎች አስታውቀዋል።

መንግስት በተጨማሪ አካባቢን ለመጠበቅ በሚል ታክስ ለመጣል ያቀደ ሲሆን ይህም ደግሞ የፕላስቲ ውጤቶች የሚያስከትሉትን ብከላ ለመከላከል እንደሆነ አስታውቋል።

ብሔራዊ ሸንጎው ረቂቅ አዋጁን ሚቀጥለው ሳምንት እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ለተቃውሞ የወጡት ኬንያውያን ግን በተቃውሟቸው እንደሚገፉበት አስታውቀዋል።

#AFP
#VOA
#Kenya

@tikvahethiopia
#USA

ከግድያ የተረፉት የቀድሞው ፕሬዜዳንት ትረምፕ !

የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትረምፕ ለቀጣዩ ምርጫ ፔንሰልቬኒያ፣ ባትለር ውስጥ ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ እያሉ ከሕዝቡ መካከል በተተኮሰ ጥይት ደም በደም ሆነው ከመድረኩ ሲወርዱ ታይተዋል።

ትረምፕ የድንበር አቋራጮች ቁጥር ምን ያህል እንደደረሰ ለማሳየት ሲጋብዙ እና የቁጥር ማሳያ ደውል መደወል ሲጀምር ከሕዝቡ መካከል የተኩስ ድምጽ የተሰማው።

ከዚያም ትረምፕ ቀኝ እጃቸውን ወደ አንገታቸው ሲልኩ ታይተዋል።

ወዲያውኑ ፊታቸው ላይ ደም ሲወርድ ታይቷል።

ትረምፕ ተኩሱ ከተሰማበት አቅጣጫ በኩል ራሳቸውን ለመከለል ወደ ታች ሲሸሹ እና የደኅንነት ሠራተኞች በፍጥነት ወደ መድረኩ ሲሮጡ ታይተዋል።

በዚህ ሰዓትም የሕዝቡ ጩኸት ይሰማ ነበር።

ትረምፕ ቀና ብለው እጃቸውን ወደላይ ሲያነሱ በምርጫ ቅስቀሳው ላይ የነበረው ሕዝብ ጩኸት ከፍ ብሎ ተሰምቷል።

የ "ሴክሬት ሰርቪስ " የሕግ አስከባሪዎች ትራምፕ በፍጥነት ከመድረክ እንዲወርዱ አድርገዋል።

ትራምፕ የግድያ ሙከራው ከተደረገባቸው በኃላ ወደ ሆስፒታል ተወስደው እርዳታ ከተደረገላቸው በኃላ ኒው ጀርዚ ተመልሰዋል።

ያለ ምንም የሰው ድጋፍ እራሳቸው እየተራመዱ ከአውሮፕላን ሲወርዱ ታይተዋል።

" ደህና " መሆናቸውም ታውቋል።

የግድያ ሙከራውን የፈጸመው ግለሰብ በአሜሪካ ሴክሬት ሰርቪስ ደኅንነት አባላት መገደሉን ተሰምቷል።

ከተጠርጣሪው በተጨማሪ ሁለት ሰዎች በተኩስ ልውውጡ መገደላቸውን እና ሌሎች ሁለት ሰዎች ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ መቁሰላቸው ተገልጿል። #VOA #CNN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OFC #Ethiopia " በአንድ ፓርቲ ፍላጎትና ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም !! " - ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦ " ዋና የኢትዮጵያ ችግር ፈጣሪ መንግሥት ነው። ይሄ ምንም ጥያቄ የለውም። ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር ሆነን ፣ከዲፕሎማቲክ…
#OromiaRegion

" ችግሮች እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ችግሮቹ እንዲወሳሰቡ እያደረጉ ያሉት እኮ እነሱ ናቸው ( ኦፌኮን ጨምሮ አንዳንድ ፓርቲዎች) " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦

" የኢፌዴሪ መንግሥት ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ፣ ያሉትን አለመግባባቶች በሀሳብ ትግል እልባት ለመስጠት ብዙ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል።

ከነዚህ ውስጥ ከሀገሪቱ ታሪክ ፣ ከሀገረ መንግስቱ ግንባታ ጋር ተያይዞ ያደሩ ቅሬታዎች ስላሉ እነዚህ ቅሬታዎች እንዲፈቱ የምክክር ኮሚሽን አቋቁሞ እየሰራ ነው።

በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት ከጠብመንጃ ይልቅ በሀሳብ ትግል እንዲደረግ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ነው የቀጠለው።

ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከማድረግ አኳያ እኛ የምንታማበት ነገር የለም።

አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች
#ኦፌኮን ጨምሮ የድርሻቸውን ባለመወጣት ፤ ችግሮች እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ችግሮቹ እንዲወሳሰቡ እያደረጉ ያሉት እነሱ ናቸው።

አንዱ የኮሚሽኑ ስራ እንዳይሳካ እራሳቸውን በማግለል እየተንቀሳቀሱ መገኘታቸው ነው።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተከሰተውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አንደኛ በሀገር በቀል በገዳ ስርዓት አባገዳዎችን ፣ የሃይማኖት አባቶችን ፣ ሃደሲንቄዎችን በማሳተፍ እርቅ እንዲወርድ ብዙ ጥረት አድርገናል። ጥረታችን አልተሳካም።

ሁለተኛ የሶስተኛ ወገኖችን ባሳተፈ መልኩ ችግሩ ይፈታ በሚል ሀሳብ ስለቀረበ ተቀብለን በሁለት ዙር ከዚህ ከአሸባሪው ቡድን (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን ማለታቸው ነው) ውይይቶችን አድርገናል። ሁኔታው በሰላማዊ መንገድ ሊፈታ አልቻለም።

ነገር ግን በአንድ እና ሁለቴ ብቻ ተስፋ የሚያስቆርጥ ሳይሆን ለሰላም ጠንክረን እንሰራለን። "

#OromiaRegionalGovernment
#VOA

@tikvahEthiopia
" የ11 ወንዶች እና 2 ሴቶች አስክሬን ነው የተገኘው " - አይ ኦ ኤም

" ፍልሰተኞችን የጫነ ጀልባ በየመን የባህር ዳርቻ መስጠሙን ተከትሎ በርካታ ሰዎች መሞተዋል ፤ አልያም ጠፍተዋል " ሲል የተመድ የፍልሰተኞች ድርጅት አሳውቋል።

አደጋው የበርካቶችን ህይወት ከቀጠፉና በተደጋጋሚ ከደረሱ የጀልባ መስጠም አደጋዎች የቅርብ ጊዜው ነው።

በታይዝ ግዛት ጀልባው ለአደጋ በተዳረገበት ወቅት 25 #ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን እና ሁለት የመናዊ መረከብ ዘዋሪዎችን ጭኖ እንደነበረ ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ተቋም (አይ ኦ ኤም) ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

እስካሁን ድረስ የ11ወንዶች እና 2 ሴቶች አስክሬን የኤደን ባህረሰላጤ እና ቀይ ባህርን በሚያገናኘው በባበል ኤል መንደብ መተላለፊያ ባህር ዳርቻ መገኘቱን እና ሁለቱን የመናዊያን ጨምሮ 14 ሰዎች የገቡበት እንዳልታወቀ ተገልጿል።

ፍልሰተኞች ከጂቡቲ የተነሱ እንደነበሩ አይ ኦ ኤም አስታውቋል ።

እንደ ተቋሙ መረጃ ከሆነ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በየመን የሚደርሱት ስደተኞች በሦስት እጥፍ አድጓል።

በ2021 27,000 ገደማ የነበረው የፍልሰተኞች ቁጥር ባለፈው አመት ከ97,200 በላይ ደርሷል።

በአሁኑ ወቅት 380,000 የሚጠጉ ስደተኞች ግጭት ባየለባት ሀገር ውስጥ ይገኛሉ።

የመን ለመድረስ ፣ፍልሰተኞቹ ቀይ ባህርን ወይም በኤደን ባህረ ሰላጤ ለማቋረጥ በህገወጥ አዘዋዋሪዎች አማካይነት አደገኛ በሆኑና በተጨናነቁ ጀልባዎች ይወሰዳሉ።

ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 2,082 ስደተኞች የገቡበት አልታወቀም ከእነዚህ መካከል 693 ያህሉ ሰጥመው ቀርተዋል።

በሰኔ ወር ቢያንስ 49 ስደተኞች በየመን ደቡባዊ የባህር ዳርቻ ጀልባቸው በመስጠሙ ሞተዋል።

140 ሰዎች ደግሞ የገቡበት እንዳልታወቀ ድርጅቱ አስታውሷል።

ተጨማሪ 62 ስደተኞች ባለፈው ሚያዝያ ወር የመን ለመድረስ ሲሞክሩ በጅቡቲ የባህር ዳርቻ ላይ በተከሰቱት ሁለት የጀልባ መገልበጥ አደጋዎች ህይወታቸው አልፏል። #IOM #VOA

@tikvahethiopia