TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2015 የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶች የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለምክር ቤት እያቀረበ ይገኛል። በዚህም ወቅት ተከታዩን ሰምተናል ፦ በ2014 የበጀት ዓመት እና ከዚያ በፊት በፌዴራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች በተከናወነው የኦዲት ሪፖርት መሰረት እርምጃ የተወሰደ እንደሆነ ማጣራት ተደርጎ ነበር። በ92 መስሪያ ቤቶች ተመላሽ እንዲደረግ…
#ኢትዮጵያ #ኦዲት

የ2015 በጀት ዓመት የፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኦዲት ክንውን ላይ ማብራሪያ እየተሰጠ ነው።

ሂሳብ አቅራቢ የነበሩት 173 የፌዴራል መንግስት ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች ሲሆኑ የ162 መ/ቤቶች እና 58 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በፌዴራል ኦዲተር መ/ቤት 11 ደግሞ በሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ኦዲት ሊደረጉ ታቅዶ ነበር።

10 መስሪያ ቤቶች 4 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በጸጥታ ምክንያት ኦዲት ተጀምሮ ተቋርጧል። 1 መ/ቤት ቢሮ አላቀረበም።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጥሬ ገንዘብ ሂሳብ ላይ ታገቢው ቁጥጥር ይደረግ እንደሆነ ለማረጋገጥ ክትትል ሲደረግ ፥ በሁለት መስሪያ ቤቶች ብቻ ብር 383 ሺህ 238 ከ48 ሳንቲም ጉድለት ተገኝቷል።

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት የ2015 በጀት ዓመት የፌዴራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኦዲት ክንውን ላይ ማብራሪያ እየተሰጠ ነው። ሂሳብ አቅራቢ የነበሩት 173 የፌዴራል መንግስት ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች ሲሆኑ የ162 መ/ቤቶች እና 58 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በፌዴራል ኦዲተር መ/ቤት 11 ደግሞ በሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ኦዲት ሊደረጉ ታቅዶ ነበር። 10 መስሪያ ቤቶች 4 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በጸጥታ…
#ኦዲት #ኢትዮጵያ

ጤና ሚኒስቴር እና ትምህርት ሚኒስቴር  ከፍተኛ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት መካከል መሆናቸው ተሰምቷል።

ለውሎ አበል እና ለመጓጓዣ እንዲሁም ለግዥ የተሰጠ ክፍያ ሰራተኛው ስራውን አጠናቆ ከተመልሱ በኃላ በ7 ቀናት መወራረድ እንዳለበት መመሪያ አለ።

ነገር ግን በ124 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው ብር 14.1 ቢሊዮን በወቅቱ ያልተወራረደ ወይም ያልተሰበሰበ ተሰብሳቢ ሂሳብ መኖሩ በኦዲት ታውቋል።

ጊዜው ሲታይም ከ1 ወር በላይ እስከ 1 ዓመት 1 ቢሊዮን 193 ሚሊዮን ብር ፤ ከ1 ዓመት በላይ እስከ 5 ዓመት 10.9 ቢሊዮን ብር ፤ ከ5 ዓመት በላይ እስከ 10 ዓመት 1.7 ቢሊዮን ብር ፤ ከ10 ዓመት በላይ 139 ሚሊዮን ነው።

ቀሪው ሂሳብ በቆይታው ጊዜ ያልተተነተነ ነው።

ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ከተገኘባቸው ተቋማት #ከፍተኛውን ድርሻ የያዙት እነማን ናቸው ?

#ጤና_ሚኒስቴር 6 ቢሊዮን
የመስኖ ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.1 ቢሊዮን
የትምህርት ሚኒስቴር 1 ቢሊዮን 12 ሚሊዮን
በፌዴራል መንግስት የህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት 970.9 ሚሊዮን
ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚኒሊየም የህክምና ኮሌጅ 756.3 ሚሊዮን
የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 433.5 ሚሊዮን
የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 286.8 ሚሊዮን
የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን 272.4 ሚሊዮን
የመንግስት ግዥ አገልግሎት 265.2 ሚሊዮን
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 250.7 ሚሊዮን
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር 218.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

በተጨማሪ የፕሮጀክት ሂሳብ በታየባቸው 4 መስሪያ ቤቶች 514.5 ሚሊዮን በወቅቱ ያልተወራረዳ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ ተገኝቷል።

እንደ የፌዴራል መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ መመሪያ መሰረት የተሰብሳቢ ሂሳብ በቂ ማስረጃ ሲቀርብበት ብቻ  ነው በተሰብሳቢ ሂሳብነት የሚመዘገበው። የተሰብሳቢ ሂሳብ ክምችት እንዳይኖር ቁጥጥር መደረግ አለበትም ይላል።

ነገር ግን በ15 መስሪያ ቤቶች በጠቅላላው 363.1 ሚሊዮን ማስረጃ ባለመቅረቡ የሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ አልተቻለም።

የተሰብሰቢ ሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ ካልተቻለባቸው መስሪያ ቤቶች መካከል ፦

🔴 የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 253.3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ግዥ አገልግሎት 39.1 ሚሊዮን
🔴 ጤና ሚኒስቴር 28 ሚሊዮን ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦዲት የተሰበሰበው ገቢ #ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ሂሳብ ኦዲት ሲደረግ በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #በዶላር የተሰበሰበ 1.3 ሚሊዮን ገቢ ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ #አልተቻለም። የፌዴራል ዋና ኦዲተር ማንኛውም ገቢ ተገቢ ማስረጃ ሳይሟላ በገቢ መመዝገብ ፍጹም ትክክል እንዳልሆነ አስገንብዝቦ የገቢ ማስረጃዎች በትክክል ተደራጅቶ እንዲያዝ ተገቢው ማስተካከያም እንዲደረግና እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።…
#ኢትዮጵያ #ኦዲት

በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል።

በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል።

በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል።

በ11 መ/ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ማስረጃ ሳይኖረው በወጪ ሂሳብ የተመዘገበ ሲሆን ማስረጃም ባለመቅረቡ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልተቻለም።

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 17.4 ሚሊዮን
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ባለስልጣን 8.7 ሚሊዮን
የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት 8.7 ሚሊዮን
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 4.4 ሚሊዮን
የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት 3.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

ከዚህ ባለፈ ፤ በወጪ ለተመዘገቡ ክፍያዎች የተሟላ ማስረጃ መቅረቡን ለማረጋገጥ በተደረገው ኦዲት በ 48 መ/ቤቶች የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 44 ሚሊዮን 440 ሺህ በወጪ ተመዝግቦ ተገኝቷል።

የተሟላ ማስረጃ ሳይዙ ወጪ ከመዘገቡት መካከል ፦
🔴 ማዕድን ሚኒስቴር 5 ሚሊዮን 719 ሺህ
🔴 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 5 ሚሊዮን 716 ሺህ
🔴 የጤና ሚኒስቴር 4 ሚሊዮን 677 ሺህ
🔴 ገንዘብ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን 34 ሺህ
🔴 በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገዋኔ የግብርና የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ 2 ሚሊዮን 450 ሺህ
🔴 የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት 2 ሚሊዮን 185 ሺህ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

የፌዴራል ኦዲተር መስሪያ ቤት ፤ ማስረጃ ካልቀረበ የሂሳቡን #ትክክለኝነት_ማረጋገጥ_እንደማይቻል ፤ የወጪ ማስረጃ ላልቀረበላቸው ክፍያዎች የወጪ ማስረጃ እንዲቀርብላቸው የማይቀርብላቸው ከሆነ #ገንዘቡ_ተመላሽ እንዲደረግ አሳስቧል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ኦዲት በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል። በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል። በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል። በ11 መ/ቤቶች 43.5…
#ኦዲት #ኢትዮጵያ

(ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት)

➡️ የበጀት አጠቃቀም ፦

ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል።

በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ ወጪ የሆነ ሂሳብ ከመደበኛው በጀት ብር 524. 7 ሚሊዮን ፣ ከውስጥ ገቢ 288.9 ሚሊዮን ፣ ከካፒታል በጀት 489.4 ሚሊዮን በድምሩ 1.3 ቢሊዮን ብር ተገኝቷል።

በኮድ ከተደለደለው በጀት በላይ ውጭ ያደረጉ ዋና ዋና መ/ቤቶች ፦
🟠 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 322.5 ሚሊዮን
🟠 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ተጠሪ ተቋማቱ 267.9 ሚሊዮን
🟠 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 173.2 ሚሊዮን
🟠 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 125.1 ሚሊዮን
🟠 የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 109.5 ሚሊዮን
🟠 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 91.3 ሚሊዮን
🟠 አምቦ ዩኒቨርሲቲ 83.3 ሚሊዮን
🟠 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 75.1 ሚሊዮን

ሁለት መስሪያ ቤቶች ደግሞ 9.7 ሚሊዮን ብር በጀት ስለመኖሩ ሳይረጋገጥ / ሳይፈቀድ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኘቷል።

➡️ ከደንብ እና መመሪያ ውጭ የተከፈለ ፦

በ30 መ/ቤቶች ብር 16 ሚሊዮን 470 ሺህ ከደንብና መመሪያ ውጭ አላግባብ ተከፍሏል።

ዋና ዋናዎቹ መ/ቤቶች ፦
🔴 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን
🔴 የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት 2 ሚሊዮን 889 ሺህ
🔴 ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን 42 ሺህ
🔴 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ 1 ሚሊዮን 156 ሺህ

➡️ በመስሪያ ቤት ለሌሉና ከስራ ገበታ ለተሰናበቱ ሰራተኞች የተከፈለ ደመወዝ ፦

በ16 መስሪያ ቤቶች በመስሪያ ቤት ለሌሉ እና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ብር 485 ሺህ 183 ከ56 ሳንቲም ደመወዝ ተከፍሎ ተገኝቷል።

➡️ በበልጫ አላግባብ የተከፈለ ወጪ ፦

በ32 መ/ቤቶች እና በ9 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በተለያዩ የግንባታና ግዥዎች 4.9 ሚሊዮንና ለውሎ አበልና ሌሎች ክፍያዎች 57.6 ሚሊዮን በድምር 62.6 በብልጫ ተከፍሎ ተገኝቷል።

➡️ የግዥ አዋጅ ደንብና መመሪያ ያልተከተሉ ግዥዎች ፦

በ73 መ/ቤቶች እና በ15 ቅ/ጽቤቶች ብር 2 ቢሊዮን 199 ሚሊዮን የመንግስት ግዥ አዋጅ ደንብ እና መመሪያን ሳይከተል ግዥ ተፈጽሟል።

° በጨረታ መግዛት ሲገባው ያለጨረታ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 1.8 ቢሊዮን ብር
° መስፈርት ሳይሟላ በውስን ጨረታ የተገዛ 104.3 ሚሊዮን ብር
° ግልጽ ጨረታ መውጣት ሲገባው በዋጋ ማወዳደሪያ የተፈጸመ 96.1 ሚሊዮን ብር
° የዋጋ ማወዳደሪያ ሳይሰበሰብ በቀጥታ የተፈጸመ ግዥ 13.8 ሚሊዮን ብር
° ሌሎች የግዥ ሂደት ያልተከተሉ 134.6 ሚሊዮን ዋና ዋና ናቸው።

ዋና ዋና መስሪያ ቤቶች (ደንብና መመሪያ ሳይከተሉ ግዥ የፈጸሙ)፦
ገቢዎች ሚኒስቴር በዋናው መ/ቤትና በቅርንጫፍ ፅ/ቤት 1.4 ቢሊዮን
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 91 ሚሊዮን
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 65.5 ሚሊዮን
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 62.9 ሚሊዮን
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 57.1 ሚሊዮን
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 37.4 ሚሊዮን
የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት እና በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 34 ሚሊዮን

➡️ በአማካሪ መሃንዲሳ ሳይረጋገጥ የተከፈለ ክፍያ ፦

የግንባታ ክፍያ #በአማካሪ_መሃንዲስ ተረጋግጠው መከፈላቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት በ2 መ/ቤቶች 170 ሚሊዮን  394 ሺህ በአማካሪ መሃንዲስ የክፍያ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሳይቀርብ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኝቷል።

👉 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 169.7 ሚሊዮን ብር ከፍሎ ተገኝቷል።

➡️ የተከፋይ ሂሳብ ፦

በ14 መ/ቤቶች 1.7 ቢሊዮን ብር በተከፋይ ሂሳብ ተይዞ ተገኝቷል። ለማን እንደሚከፈል እንኳን ተለይቶ አይታወቅም።

የተከፋይ ሂሳብ ለባለመብት መለየት ካልቻሉ መስሪያ ቤቶች ፦
🔵 የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 1.5 ቢሊዮን
🔵 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 131.8 ሚሊዮን
🔵 ማዕድን ሚኒስቴር 29.9 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ኢትዮጵያ

በቀጣዮቹ 10 ቀናት ለክረምት ዝናብ መፈጠር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ከቀን ወደ ቀን በተሻለ መልኩ ይጠናከራሉ።

በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ መካከለኛው እና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አከባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡
  
በቀጣይ 10 ቀናት ....

አዲስ አበባ

ከኦሮሚያ ክልል ፦
- ቡኖ በደሌ
- ኢሉባቦር
- ጅማ
- ምስራቅ እና ምዕራብ ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ፣ ቄለም ወለጋ
- ምዕራብ ሀረርጌ
- አርሲ እና ምዕራብ አርሲ
- ሰሜን ሸዋ (ሰላሌ)
- ምዕራብ፣ ደቡብ ምዕራብ እና ምስራቅ ሸዋ ዞኖች

ከአማራ ክልል ፦
- ሰሜን፣ ማዕከላዊ፣ ደቡብ እና ምዕራብ ጎንደር
- ሰሜን እና ደቡብ ወሎ
- የኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን
- አዊ
- ምስራቅ እና ምዕራብ ጎጃም፣ ሰሜን ሸዋ፣ ዋህግምራ

ከትግራይ ክልል ፦ ማዕከላዊ፣ ሰሜን ምዕራብ፤ ምስራቅ፤ ደቡብ፤ እና ምዕራብ ዞኖች

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፦ መተከል፣ ፓዌ፤ አሶሳ ፣ ካማሺ ዞኖች

ከጋምቤላ ክልል ፦ ማዣንግ እና አኝዋክ ዞኖች

ከሱማሌ ክልል፦ ሲቲ እና ፋፋን ዞኖች

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፦ ጉራጌ፣ ሀላባ ፣ ስልጤ ፣ ጠምባሮ ፣ ሃዲያ ፣ የየም ልዩ ዞን

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፦ ቤንች ሸኮ ፣  ዳውሮ ፣ ከፋ ፣ ሸካ ፣ ኮንታ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፦ ጎፋ ፣ ጋሞ ፣ ኮንሶ ፣ ወላይታ ፣ ጌድኦ ፣ አማሮ ፣ አሪና ደራሼ ዞኖች

የሲዳማ ክልል ዞኖች

ሀረር እና ድሬዳዋ

... ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡

ከዕለት ወደ ዕለት ከሚጠናከሩት የአየር ሁኔታ ገጽታዎች ላይ በመነሳት ፦
° ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሀረርጌ፣ ባሌ እና ምስራቅ ባሌ፣ ቦረና፣ ጉጂ እና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች፤
° ከሱማሌ ክልል ጀራር፣ ኤረር፣ ኖጎብ፣ አፍዴር፣ ሊበን እና ዳዋ ዞኖች፤
° ከአፋር ክልል ቅልበቲ፣ ፈንቲ፣ አውሲ እና ሀሪ ዞኖች፤
° ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን፤
° ከጋምቤላ ክልል ንዌር እና የኢታንግ ልዩ ዞን ቀላል መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡

#EthiopianMeteorologyInstitute

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

 በየዓመቱ ከ8 ቢሊዮን እስከ 5.6 ቢሊዮን ብር በጀት ሊመደብለት ይችላል።

የፌዴራል መንግሥት ፤ በየዓመቱ ከአገር ውስጥ ገቢ ምንጭ ከሚመድበው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ0.5 በመቶ እስከ አንድ በመቶ ያህል ለአረንጓዴ አሻራ እና ለተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ እንዲሰጥ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል።

ረቂቅ አዋጁ ፤ " የአረንጓዴ አሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድን ለማቋቋም እና አስተዳደሩን ለመወሰን የወጣ አዋጅ " የሚል ስያሜ አለው።

ረቂቅ አዋጁ ምን ይዟል ?

ለም/ ቤቱ የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ባለበት ሁኔታ ከፀደቀ በልዩ ፈንድ ከ2.8 ቢሊዮን ብር እስከ 5.6 ቢሊዮን ብር የሚደርስ በጀት ከመንግሥት ብቻ ሊቀርብለት ይችላል።

ልዩ ፈንዱ ዘጠኝ ዓላማዎች አሉት። ከእነዚህም መካከል ፦
- የተጎሳቆለ መሬት በተፈጥሮና በመልሶ ማልማት መርህ በመታገዝ እንዲያገግም ማድረግ፣
- የደን ልማትና የደን መልሶ ማልማትን መደገፍ፣
- የአገሪቱን የካርቦን ልቀት ቅነሳ ግብ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ማድረግ፣
- የከተማ ማስዋብ እና አረንጓዴ ልማት ሥራዎችን መደገፍ የሚሉ ይገኙበታል።

የልዩ ፈንዱ የፋይናንስ ምንጮች ፦
1ኛ. የፌዴራል መንግሥት የሚመድበው በጀት፣
2ኛ. የልማት አጋሮች፣
3ኛ. የሲቪክ ማኅበረሰቦች፣
4ኛ. የግል ዘርፍ የሚሰጡት ድጋፍ ነው።

የፌዴራል መንግሥት ለፈንዱ ከሚመድበው በጀት የሚሰበሰበው ገንዘብ ለልዩ ፈንዱ በተከፈተው የባንክ ሒሳብ በየ3 ወራቱ በገንዘብ ሚኒስቴር ተቀማጭ ይሆናል። የሌሎች ምንጮች ድጋፍ የሚተዳደርበት አኳኋን የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመርያና የአሠራር ሥርዓት ይወሰናል።

መንግሥት የሚመድበው ዓመታዊ በጀት የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መሥፈርት መሠረት ለፌዴራል መንግሥትና ለክልሎች ይደለደላል።

ለክልሎች ከሚደለደለው በጀት ላይ የእያንዳንዱን ክልል ድርሻ ለመወሰን የሚያገለግለውን የገንዘብ ሚኒስቴር አዘጋጅቶ እንዲፀድቅ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይቀርባል። ሆኖም ለመሸጋገሪያነት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያፀደቀው ጠቅላላ የበጀት ድጋፍ ቀመር በጥቅም ላይ ሊውል ይችላል።

ከተደለደለው ዓመታዊ የሀብት ድርሻ ላይ በየ3 ወሩ ወደ ተጠቃሚ አካላት ገንዘብ ሊተላለፍ የሚችለው የሥራ አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ፣ ክልሎች ተጓዳኝ በጀት ሲመድቡና በክልሉ ለሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ፈሰስ ሲያደርጉ ይሆናል።

ክልሎች የሚመድቡት ዝቅተኛ ተጓዳኝ በጀት ተፈጻሚ የሚሆነው በተጓዳኝ በጀቱ መጠን ላይ በረቂቅ አዋጁ የልዩ ፈንዱ አስፈጻሚ አካላት በሚል የተዘረዘሩት ፦
° የገንዘብ ሚኒስቴር፣
° የግብርና ሚኒስቴር፣
° የፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣
° የኢትዮጵያ ደን ልማት በክልሎች የገንዘብ ቢሮዎች መካከል በሚደረግ ምክክር የጋራ ስምምነት ላይ ሲደረስና በየክልሉና በከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤቶች ሲፀድቅ ነው።

እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ሳይተላለፍ የቀረ ገንዘብ በቀጣዩ ዓመት ለልዩ ፈንዱ ከሚመደበው በጀት ጋር ተደምሮ ይደለደላል።

የልዩ ፈንዱ ዓብይ ኮሚቴ አስፈጻሚ አካላት፦
° ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣
° ከኢትዮጵያ ደን ልማት
° ከክልሎች የገንዘብ ቢሮዎች የበላይ ኃላፊዎች ይዋቀራል። የገንዘብ ሚኒስቴርና የግብርና ሚኒስቴር ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢ ይሆናሉ።

ገንዘብ ሚኒስቴር ከተጠቃሚ አካላት ሚቀበለውን የሒሳብ ሪፖርት በማጠቃለል የልዩ ፈንዱን ሒሳብ ዘግቶ የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ በ3 ወራት ውስጥ በፌዴራል ዋና ኦዲተር ወይም የፌዴራል ዋና ኦዲተር በሚወክለው ኦዲተር እንዲመረመር የማድረግ ኃላፊነት አለበት።

(ሪፖርተር ጋዜጣ)

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

ጤፍን ጨምሮ በሌሎች የግብርና ግብዓት ምርቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መሆናቸውን የሚወስነዉ መመሪያዉ ተግባራዊ መደረግ እንደጀመረ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

የገንዘብ ሚኒስቴር በአገር ውስጥ የሚመረቱ እና ከውጭ አገር የሚገቡ እቃዎች እንዲሁም በአገር ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ መሆናቸውን አረጋግጧል።

ከሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ በተጀመረው በዚህ መመሪያ ዉስጥ የእህልና ጥሬጥሬ ፣ የግብርና ምርቶች እና የበሰሉ ወይም የተዘጋጁ ምግቦች / መጠጦች ይገኙበታል ።

በዚህ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ የሚሆኑ  እቃዎችን ለመወሰን በወጣው  መመሪያ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል መሰረታዊ የሆኑ የምግብ አቅርቦቶችን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ ሆኖ እንዲገዛ ማድረግ የወጪ ጫናውን በማርገብ ረገድ ጠቀሜታ አለው ተብሏል።

ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ከተደረጉት መካከል ፦
➡️ ጤፍ፣
➡️ ስንዴ፣
➡️ ገብስ ፣
➡️ ማዳበሪያ ፣
➡️ የእንስሳት መድሃኒት እንዲሁም በካፒታል ሊዝ ስምምነት የሚቀርብ የካፒታል ዕቃዎች ይገኙበታል።

መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 “ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል። የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ…
🇪🇹 የፓለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ መንግስት እንደ መንግስት ሥራውን እየሰራ አይደለም ” ሲል ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ተቸ።

የፓርቲው ሊቀመንበር ፤ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ስለወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች የፓርቲያቸውን ምልከታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርተዋል።

ሊቀመንበሩ በነበራቸው ቆይታ  ፦
- የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ጉዳይ
- የኑሮ ውድነት
- የሰላም እና ጸጥታ ጉዳይ
- ከሰሞኑን እየወጡ ስላሉ አዳዲስ አዋጆች
- ስለ ፖለቲካ ህዳሩ
- የመልካም አስተዳደር እጦት
- የኢኮኖሚ ጉዳይ ... ሌሎችም ተነስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም " መፍትሄው ምንድነው ? " ሲል ላቀረበው ጥያቄ ፓርቲው ምላሽ ሰጥቷል።

ምጣኔ ሀብትን በተመለከተ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ምን አሉ ?

“ የMacro Economy መናጋት አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የከፋ ሁኔታ ላይ ደርሷል።

የኢትዮጵያ የልማት ስትራቴጂ ሁኔታዎችን ያላገናዘበ ነው።

ይልቁንም ትኩረት የሚሹት ፦
➡️ ኢንፍራስትራክቸር፣
➡️ መብራት፣
➡️ ጤና፣
➡️ ውሃ መሠረታዊ ችግሮች ናቸው፤ ዜጎች በእነዚህ ነገሮች ተቸግረዋል።

ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ በሚል የሚሰራቸው ፕሮጀክቶች መቃኘት አለባቸው።

ከፍተኛ የሆነ የንግድ ጉድለት አለ። የምንሸጠው እና የምንገዛው ልዩነቱ የሰፋ ነው። የበጀት Deficit አለ።

መንግስት የሚሰበስበውና የሚያወጣውን ገንዘብ ለዚያውም አስፈላጊነታቸው አጠራጣሪ ፕሮጀክቶች ላይ ገንዘቡ ወጪ ይሆናል።

ይሄ ኢኮኖሚው እንዲናጋ አድርጓል ብለን እናምናለን።”

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-24

#ነእፓ #ኢትዮጵያ #የፖለቲካፓርቲዎችምንይላሉ?
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ጤፍን ጨምሮ በሌሎች የግብርና ግብዓት ምርቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መሆናቸውን የሚወስነዉ መመሪያዉ ተግባራዊ መደረግ እንደጀመረ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። የገንዘብ ሚኒስቴር በአገር ውስጥ የሚመረቱ እና ከውጭ አገር የሚገቡ እቃዎች እንዲሁም በአገር ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ መሆናቸውን አረጋግጧል። ከሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ በተጀመረው…
#ያንብቡ #ኢትዮጵያ

ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ የሚሆኑ እቃዎችን ለመወሰን የወጣው መመሪያ ፤ ' መመሪያ ቁጥር 1006/2016 ' ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

መመሪያው ተግባራዊ የተደረገው ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል መሰረታዊ የሆኑ የምግብ አቅርቦቶችን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ ሆኖ እንዲገዛ ለማድረግና የወጪ ጫናውን ለማርገብ ጠቀሜታ ስላለው መሆኑ ተገልጿል።

ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ የሆኑ እቃዎች እና አገልግሎቶች ዝርዝር ምንድናቸው ?

ከዚህ በታች የተዘረዘሩ በአገር ውስጥ የሚመረቱ እና ከውጭ አገር የሚገቡ እቃዎች እንዲሁም በአገር ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ ናቸው።

1ኛ. እህልና ጥራጥሬ
ጤፍ
ስንዴ
ገብስ
በቆሎ
ማሽላ
ዘንጋዳ
ዳጉሳ
አጃ
አተር ፣ ባቄላ ፣ ምስር፣ አኩሪ አተር፥ ሽምብራ፣ ግብጦ፥ ጓያ እና የመሳሰሉት ጥራጥሬዎች፤
የእነዚህ ዱቄት

2ኛ. የግብርና ግብአቶች
ማዳበሪያ
ጸረ-ተባይ ኬሚካል
የእንስሣት መድሃኒት
የመድሃኒት መርጫ

3ኛ. የበሰሉ ወይም የተዘጋጁ ምግቦች / መጠጦች
👉 እንጀራ
👉 ዳቦ
👉 ወተት

4ኛ. በካፒታል ሊዝ ስምምነት የሚቀርቡ የካፒታል እቃዎች

5ኛ. የወባ መከላከያ አጎበር ፤ ኮንዶም እና ለውሃ ማከሚያ የሚሆኑ ኬሚካሎች

#MinistryofFinance
#MinistryofRevenues

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

“ ሀኪሞች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው። ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት፤ ቤት እንኳ የላቸውም። በአውቶብስ ተጋፍተው ነው እየመጡ የሚሰሩት። ይህ ችግር ግን የጤና እከል የደረሰበትን ማህበረሰብ ከማገልገል አልከለከላቸውም ፤ ያንን እያደረጉ ግን ሲታመሙ እንደ ሞያተኛ ሳይሆን ለምነው ነው የሚታከሙት። ” - ዶክተር በሀሩ በዛብህ (የኢትዮጵያ ሕክምና ማኅበር የቦርድ አባል - ለቲክቫህ ኢትዮጵያ)

#EMA
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#ስፖርት #ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ፕሪሜየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ።

ቡድኑ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ፍጻሜውን እስካገኘበት የሊጉ የመጨረሻ መርሃግብር ድረስ ከመቻል የእግር ኳስ ቡድን ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ነው ሻምፒዮን የሆነው።

ዛሬ በተካሄደ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድህንን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል።

በዓመቱ 64 ነጥብ በመሰብሰብም ከመቻል በ1 ነጥብ በልጦ አጠናቋል።

መቻል በዓመቱ የፍጻሜ መርሃግብር ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ተፋልሞ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም በ1 ነጥብ ተበልጦ ዋንጫውን ተነጥቋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በመጣበት አመት በታሪኩ የመጀመሪያው የሆነውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫ ማሳካት ችሏል።

ቲክቫህ ስፖርት👇
https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport    
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ! " - ቋሚ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ፥ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ። በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ…
🔈#መልዕክት

" ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ፦
- ሰላምን፣ 
- መረጋጋትን
- ፍቅርን
- አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ " - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ


#ኢትዮጵያ🙏

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ! " - ቋሚ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ፥ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ። በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ…
🔈#ማስታወሻ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ

" ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ፦
- ሰላምን፣ 
- መረጋጋትን
- ፍቅርን
- አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ "


ቋሚ ሲኖዶስ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም ማወጁ አይዘነጋም።

#ኢትዮጵያ🙏

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬም ያው ነው ! ሜዳሊያ ውስጥ አልገባንም። ኬንያ ወርቁን ወስዳዋለች። ጣልያን ብሩን አግኝታለች። ለኔዘርላንድ የምትሮጠው ሲፋን ሀሰን 3ኛ በመውጣት ነሀስ ለሀገሯ አስገኝታለች። ከቀናት በፊት ሲፋን ለሀገሯ የነሃስ ሜዳሊያ ማስገኘቷ አይዘነጋም። @tikvahethiopia
#Ethiopia

በሴቶች የ10,000 ሜትር ፍጻሜ ላይ ምንም አይነት ሜዳሊያ አለማግኘታችን ብቻ ሳይሆን ደረጃችን እጅግ በጣም ዝቅ ያለ ነው።

ጉዳፍ ፀጋይ 6ኛ ፣ ፎቴን ተስፋይ 7ኛ እንዲሁም ጽጌ ገብረሰላማ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ነው ያጠናቀቁት።

በዘንድሮ የፓሪስ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚይዟቸው ደረጃዎች እጅግ በጣም የሚያስደነግጡ ናቸው።

በአትሌቲክሱ ዓለም ሀገራችን #ኢትዮጵያ ስሟ በዚህ መልኩ አይታወቅም ነበር።

@tikvahethiopia
#Ethiopia🇪🇹

" በዝምታ አንመለከትም " - ኢትዮጵያ

በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) በቀጣይ የሚኖረው አዲስ የሰላም ተልዕኮ አወቃቀር ሁኔታ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ላይ አዲስ ስጋት ይዞ መምጣቱ ኢትዮጵያን እንዳሳሰባት አሳውቃለች።

" የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለዚሁ አዲስ ሽግግር እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት፣ ቀጠናው ሊተነበይ ወደማይቻል ፈተና ውስጥ እየገባ ይገኛል"ም ብላለች።

በሁኔታው ላይ ቀደም ሲል ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ ወታደር ያዋጡ አገሮች ተደጋጋሚ ጥሪዎችና አስተያየቶች ትኩረት እንዳልተሰጣቸው አስገንዝባለች።

" የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት መልካም ስምና ዝናን እንዲሁም መስዋዕትነት የሚያጠለሹ ተከታታይ መግለጫዎች ሲወጡ ኢትዮጵያ በዝምታ እንድታልፍ ከአንዳንድ ወገኖች በኩል ፍላጎት መኖሩ ይታያል " ብላለች።

ሌሎች ተዋናዮች የአፍሪካ ቀንድ ክልልን ለማተራመስ እርምጃ ሲወስዱ ኢትዮጵያ በዝምታ እንደማትመለከት አሳውቃለች።

ይህም በመሆኑ በቀጣናው የብሄራዊ ደህንነቷን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሁሉ በንቃት እየተከታተለች እንደሆነም አመልክታለች።

የሶማሊያ መንግስት በቀጠናው ሰላም ለማስፈን የሚደረጉ ጥረቶች ከማጠናከር ይልቅ ቀጠናውን ለማተራመስ ከሚሹ የውጭ ኃይሎች ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ኢትዮጵያ አጽንኦት ሰጥታ ገልጻለች።

በሶማሊያ ለማሰማራት የታቀደውን አዲስ የሰላም ተልዕኮ የማዘጋጀትና የመፍቀድ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ሁሉ በቀጠናው የሚገኙና ቀደም ሲል ወታደር አዋጭ የሆኑ አገራትን ተገቢ የሆኑ ስጋቶች ሁሉ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብላለች።

ኢትዮጵያ ፥ " ለአጭር ጊዜ ፍላጎታቸውና ከንቱ አላማቸው ሲሉ በክልሉ ውጥረትን ለማቀጣጠል የሚሞክሩ ኃይሎች ዕኩይ ተግባራቸው የሚያስከትሏቸዉን መዘዞች መሸከም ይኖርባቸዋል " ብላለች።

ቀደም ሲል አህጉራዊና አለምአቀፋዊ አሸባሪ ቡድኖች ላይ የተገኘውን አበረታች ውጤት አደጋ ላይ የሚጥሉና የሚቀለብሱ ድርጊቶችን እንደማትታገስ ተናግራለች።

ኢትዮጵያ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ከሶማሊያ ህዝብና ከአለምአቀፉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል አሁንም ቁርጠኛ አቋም እንዳላት አመልክታለች።

#ኢትዮጵያ #Ethiopia🇪🇹

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia " ሌሎች ተዋናዮች የአፍሪካ ቀንድ ክልልን ለማተራመስ እርምጃ ሲወስዱ በዝምታ አንመለከትም " - ኢትዮጵያ @tikvahethiopia
#Ethiopia🇪🇹

" #ኢትዮጵያ ሶማሊያ እንደ አገር ትቆም ዘንድ ብዙ መስዋዕትነትን ከፍላለች፡፡ ብዙ ሺሕ የሚቆጣጠሩ ወንዶችና ሴቶች መስዕዋት አድርገናል ገብረናል፡፡

የቆጠብነው ነገር የለም ሕይወት ሰጥተናል፣ ደም ሰጥተናል፣ ላብ ሰጥተናል፣ ጉልበት ሰጥተናል፡፡ ነገር ግን በሶማሊያ በኩል ይህንን አስተዋጽኦ ከቁብ ላለመቁጠርና ውለታ ለማስቀረት የሚደረግ መግለጫ መስማት እንደ ኢትዮጵያዊ ይኮሰኩሳል።

እንደ አፍሪካዊና ሰላም ወዳድ እንደሆነው የሶማሊያ ሕዝብ ደግሞ ያማል።

በሶማሊያ በኩል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ያደረገውን ተጋድሎ በማንኳሰስ፣ የወሬያቸውና የንግግራቸው ሁሉ ማዋዣ ብቻ ሳይሆን ማዕከል እያደረጉት ነው ፤ ይህ ነውር ነው !!

ኢትዮጵያ ለዘመናት ያደረገችውን አስተዋጽኦ እና የከፈለችውን ዋጋ በማጣጣል፣ የኢትዮጵያን ጥቅም የሚፃረሩ ኃይሎችን ሶማሊያ መጋበዟን ልታቆም ይገባል።

ኢትዮጵያ የደኅንነት ሥጋት የሚፈጥርባትን አካል ዝም ብላ አትመለከትም። " - አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ (የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)

#Ethiopia #Reporter
@tikvahethiopia
" ኢትዮጵያ አሁን ያላትን የገበያ ፍላጎት ለማሟላት 10 ወደቦች ያስፈልጓታል " - ጅቡቲ

ጅቡቲ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ በሚል ከኢትዮጵያ 100 ኪ/ሜ ርቆ የሚገኘውን የ ' ታጁራ ወደብ ' ኢትዮጵያ እንድትጠቀምበት የሚል የመፍትሄ ሀሳብ አቅርባለች።

ለጊዜው በምን መልኩ ፤ እንዴት ነው የምትጠቀመው የሚለው በዝርዝር አልታወቀም።

ኢትዮጵያ ይህን የጅቡቲ ጥያቄ ትቀበለው አትቀበለው እስካሁን የሚታወቅ ነገር የለም።

የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ዩሱፍ ምን አሉ ?

" ይሄ ለኢትዮጵያ በጣም የሚጠቅም ነገር መሆኑን እናውቃለን።

ከአንድ መቶ ሚሊዮን በላይ ሸማቾች ያሏት ትልቅ ሀገር እንደመሆኗ
ኢትዮጵያ ከ3 እና 4 በላይ ወደቦች ያስፈልጓታል።

ኢትዮጵያ አሁን ያላትን የገበያ ፍላጎት ለማሟላት 10 ወደቦች ያስፈልጓታል።

እኛ እነዚህን የኢትዮጵያን ፍላጎቶች እንረዳለን። የሚጠበቀውን ለማድረግም እንሞክራለን።

ኢትዮጵያ የባህር ኃይል ጦር ሰፈር መገንባት አትችልም ግን ኢትዮጵያ ከአንድ በላይ ወደብ እንዲኖራት ለመርዳት እንፈልጋለን።

ኢትዮጵያ ከአንድ በላይ መተላለፊያ እንዲኖራት በማገዝ የተፈጠረውን ውጥረት በማርገብና ሁሉም እንዲረጋጋ በማድረግ በዋናው ቁምነገር ላይ ማተኮር አለብን።

እንደ ጅቡቲ ያለን ሚና ያ ነው። ላለፉት ዓመታት ስናደርግ የነበረውም ያንን ነው። አሁንም በነዚህ መርሆች ላይ መስራታችንን እንቀጥላለን።

እኛ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የነበረው መልካም ግንኙነት ወደነበረበት እንዲመለስ እንፈልጋለን " ብለዋል ለቪኦኤ በሰጡት ቃል።

ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት የአፍሪካ ግዝፏ ሀገር #ኢትዮጵያ የባህር በር አልባ ስትሆን ያላት ፍትሃዊ ጥያቄዋ ላለፉት በርካታት አመታት እንደ ሀገር አጀንዳ ሳይሆን ቆይቷል። ጉዳዩም በዚህ ልክ ተነስቶ አያውቅም ነበር።

ከወራት በፊት ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ ግን ጉዳዩ የዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኗል።

ምንም እንኳ ስምምነቱን ተከትሎ ሶማሊያ አኩርፋ ግንኙነቷን ብታሻክርም ችግሩን ለመፍታት በሚል የተለያዩ የመፍትሄ ሀሳቦች መቅረብ ጀምረዋል።

ሀገሪቱ (ሶማሊያ) ከ " ኢትዮጵያ ጋር አልነጋገርም " ብትልም ኢትዮጵያ ስለጉዳዩ ያላትን አቋም ከተመለከተች በኃላ በአሸማጋዮች አማካኝነት ወደ ውይይት ጠረጴዛ መጥታለች። ምንም እንኳ እስካሁን ውይይቶቹ ፍሬ አልባ ቢሆኑም።

#ETHIOPIA

@tikvahethiopia
ባለ ብዙ ቀለሟ ኢትዮጵያ !

(አሁን ላይ እየተከበሩ ያሉና በቀጣይ ቀናት የሚከበሩ በዓላት)

የሀዲያ የዘመን መለወጫ ' ያሆዴ '
የወላይታ የዘመን መለወጫ  ' ዮዮ ጊፋታ '
የካፊቾ የዘመን መለወጫ ' ማሽቃሮ '
የጋሞ የዘመን መለወጫ ' ዮ ማስቃላ ' 
የጊዲቾ የዘመን መለወጫ  ' ባላ ካዳቤ '
የዘይሴ የዘመን መለወጫ ' ቡዶ ኬሶ '
የቦሮ ሺናሻ የዘመን መለወጫ ' ጋሪ ዎሮ '
የጎፋ የዘመን መለወጫ ' ጋዜ ማስቀላ '
የኦይዳ የዘመን መለወጫ ' ዮኦ ማስቃላ '
የከምባታ ዘመን መለወጫ ' መሳላ '
➡️ የጠምባሮ ዘመንድ መለወጫ ' መሳላ '
የዶንጋ ዘመን መለወጫ ' መሳላ '
የየም ዘመን መለወጫ ' ሄቦ '

ይህ የመስከረም ወር በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ነው።

#ኢትዮጵያ

እንኳን አደረሳችሁ ፤ መልካም በዓል !

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፦

" ባለፉት ዓመታት ሲፈታተኑን የቆዩ ዙሪያ መለስ ችግሮች መስቀሉ ባስተማረን ሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝና ህዝባችን ያለምንም ስጋት ወጥቶ እንዲገባ ፣ ሰርቶ እንዲያተርፍ ፣ ተምሮ እንዲያውቅ ፣ ሃይማኖቱን በነጻነት እንዲከተል መንግሥትና ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለዘላቂ ሰላምና አንድነት አበክረው እንዲሰሩ በእግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። "

@tikvahethiopia