TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ምርጫ2013

በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ፦

- የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ መዘግየት ፣
- በድምፅ አሰጣጥ ላይ የሚታይ መደነጋገር፣
- ሰዓት አለማክበር፣
- የኮቪድ-19 ፕሮቶኮል አለመጠበቅ፣
- ረጃጅም ሰልፎች (በፍጥነት አለመሄድ) ፣
- የሰልፍ ተራ አለመጠበቅ፣
- የምርጫ ቁሳቁስ መቀያየር
- ቀልጥፍ ያለ መስተንግዶ ክፍተት
- መራጮች ምርጫ ካርዳቸውን የወሰዱበትን መታወቂያ ሳይዙ መሄድ
- "እከሌን ምረጡ" የሚል ቅስቀሳ ለማድረግ መሞከር የመሳሰሉት ችግሮች ከመስተዋላቸው በዘለለ የምርጫ ሂደቱ #በሰላም እየተካሄድ መሆኑን ከአዲስ አበባና ከክልል የምርጫ ጣቢያዎች የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።

የ Tikvah - Ethiopia አባላት በተመለከቷቸው የምርጫ ጣቢያዎች እድሜያቸው የገፋ ዜጎች ፣ እናቶች አባቶች ድምፅ ለመስጠት ተሰልፈው ተመልከተዋል። ነፍሠ ጡሮች፣ ልጅ የታቀፉ እናቶች ተሰልፈው ድምፅ ሲሰጡ አስተውለዋል።

በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ በፀጥታ እና በሰላም ረገድ ምንም ጥቆማ ከአባላቶቻችን አልተላከም፤ ሁሉም ሂደት #በተረጋጋ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልፀውልናል።

Photo Credit : Tikvah Family (Addis Ababa)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HappeningNow በአሁን ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ህወሓትን እና ሸኔን የሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ነው። በሰልፉ ላይ የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትንና የውጭ ሀገር መገነኛ ብዙሃንን አጥብቀው የሚተቹ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ የተፃፉ የተለያዩ መፈክሮች በሰልፈኞች ተይዘዋል። ሰልፈኞች ካያዟቸው መፈክሮች መካከል ፦ - የአሜሪካ…
#Update

" ሰልፉ በሰላም ተጠናቋል " - የአዲስ አበባ ፖሊስ

በመስቀል አደባባይና በዙሪያው የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ #በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ፕሮግራሙ በሰላም እንዲጠናቀቅ የከተማው ነዋሪ በተለይ ደግሞ የሰላማዊ ሰልፉ ታዳሚዎች ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ተገቢውን ትብብር በማድረጋቸው ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።

በተጨማሪ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ላሉ የፀጥታ አካላት እንዲሁም ሰልፉን ላስተባበሩ እና ለመሩ አካላት በሙሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ። በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ። ዶ/ር…
#Peace

የተደራዳሪ ቡድኑ !

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል።

የቡድኑ አባላት ፦

1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ
2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል
3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል
4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️ አባል
5ኛ. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ➡️ አባል
6ኛ. ሌ/ል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ ➡️ አባል
7ኛ. ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ➡️ አባል መሆናቸውን የኢፕድ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Tigray

ህወሓት ፤ ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ባወጣው መግለጫ " አምባገነን " ሲል የጠራቸው የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በትግራይ ዘግናኝ ግፍ እየፈፀሙ ነው ብሏል።

በአጠቃላይ የኤርትራ ጦር በደቡብ አፍሪካ የጦርነት ማቆም ስምምነት ከተፈረመ በኋላም በትግራይ እና በህዝቡ ላይ የሚያደርሰውን #ሁሉን_አቀፍ ጥቃት አጠናክሮ ቀጥሏል ሲል ከሷል።

የኢትዮጵያ መንግሥት #ኃላፊነቱን_እንዲወጣ ፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ኢሳያስ አፈወርቂ በትግራይና በህዝቡ ላይ እየፈጸመው ያለውን ግፍ እና በደል በአስቸኳይ እንዲያስቆም እንዲያደርግ ፤ ከትግራይ እንዲወጣ እንዲያስገድዱ ፤ ሲፈጽመው ለነበረው ወንጀል #ተጠያቂ እንዲሆን እንዲያደርጉ ሲል ጥሪ አቅርቧል።

" ህወሓት " በዛሬው መግለጫው ያነሳቸው ነጥቦች ምንድናቸው ?

- በተፈረመው #የሰላም_ስምምነት መሰረት ጦርነት እንዲቆም ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት እንዲከበር፣ የኤርትራና ሌሎችም ሃይሎች ከትግራይ እንዲወጡ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብሏል።

- ህወሓት ፤ " አምባገነን " ሲል የጠራቸው የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ፤ በሰላም ስምምነቱ #እንዳልተደሰቱ ገልጾ ፤ " ወታደሮቹን ያስወጣል ተብሎ ቢጠበቅም ተጨማሪ ክፍሎችን (ኃይሎቹ) ወደ ትግራይ እያመጣ ነው " ብሏል። ይኸው ጦር በህዝባችን ላይ አሰቃቂ ወንጀል እየፈጸመ ይገኛል ሲል ገልጿል።

- የኤርትራ ጦር በሴቶቻችን ላይ ጾታን መሰረት ያደረገ እጅግ አረመኔያዊ ጥቃት እየፈፀመ ፤ ንፁሀን ዜጎችን እየጨፈጨፈ ፣ የህዝብና የግል ንብረት እየዘረፈ ወደ ኤርትራ እያጓጓዘ ፤ የተረፈውን ደግሞ #እያጠፋ እና እያቃጠለ ነው ፤ የትግራይ ቅርሶችም በከፍተኛ ደረጃ እየወደሙና እየተዘረፉ ነው ፤ በአጠቃላይ የኤርትራ ጦር በደቡብ አፍሪካ (ፕሪቶሪያ) የጦርነት ማቆም ስምምነት ከተፈረመ በኋላም በትግራይ እና በህዝቡ ላይ የሚያደርሰውን ሁሉን አቀፍ ጥቃት አጠናክሮ ቀጥሏል ብሏል።

- ህወሓት የኢትዮጵያ መንግሥት ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ኢሳያስ አፈወርቂ በትግራይ እና በሕዝቡ ላይ እየፈጸመ ያለውን ግፍ እና በደል #በአስቸኳይ_እንዲያስቆም ፤ ከትግራይ እንዲወጣም እንዲያስገድደው እንዲሁም በትግራይ ሲፈጽመው ለነበረው ወንጀል ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆን ማደረግ አለበት ብሏል።

- ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በተለይም አፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ፣ የአሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በኢሳያስ አፈወርቂ " አምባገነን " ስርዓት ላይ ትክክለኛ ማዕቀብ እንዲጥልና ተጨባጭ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርቧል።

ይህንን የህወሓት ክስ በተመለከተ ከ "ኤርትራ" በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ጦርነት እንዲያበቃ ፤ ያሉት ችግሮችም #በሰላም እንዲፈቱ ፤ የሰብዓዊ ድጋፍ ያለገደብ ለተቸገሩት ዜጎች ሁሉ እንዲደርስ ፤ መሰረታዊ አገልግሎቶች ስራ እንዲጀምሩ ለማድረግ በደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ (የስምምነቱ ማስፈፀሚያ ላይ) ስምምነት መፈረማቸው አይዘነጋም።

በናይሮቢ ስምምነት በትግራይ ክልል ያሉ ታጣቂዎችን ትጥቅ ማስፈታት የውጭ ኃይሎችን እና ከኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆኑ ኃይሎችን ሁሉ ከክልሉ (ከትግራይ ክልል) ከማስወጣት ጋር #አብሮ እንደሚከናወን መገለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ መንገደኞችን ይዞ የበረረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን #በሰላም አሉላ አባ ነጋ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት አርፏል። ዛሬ መቐለ ያረፈው የመንገደኞች አውሮፕላን ከ19 ወራት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

Photo : Addis Ababa Bole Airport (ENA)

@tikvahethiopia
እንኳን አደረሳችሁ !

እንኳን ለጥምቀት ከተራ በዓል #በሰላም አደረሳችሁ።

@tikvahethiopia
#ጥምቀት

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ #በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ።

መልካም የጥምቀት በዓል!
Baga Ayyaana Cuuphaa Nagaan Geessan! Ayyaana Gaarii
ርሑስ በዓል ጥምቀት !

@tikvahethiopia
#ከተራ #ጥምቀት

መንግስት የዘንድሮ ዓመት የከተራ እና የጥምቀት በዓል በመላው ሀገሪቱ #በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቋል።

የበዓላቱን በሰላም መጠናቀቅ አስመልክቶ ዛሬ ማምሻውን በኮሚኒኬሽን አገልግሎት በኩል መግለጫ ያወጣው መንግሥት ፤ የከተራ እንዲሁም የጥምቀት በዓላት በድምቀት እና በሰላም እንዲጠናቀቁ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU ኮሞሮስ የ2023 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርነትን #ከሴኔጋል በይፋ ተረክባለች። 36ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተጀምሯል። በጉባዔው መክፈቻ መርሐግብር የወቅቱ የሕብረቱ ሊቀ መንበር ሴኔጋል ለኮሞሮስ ሊቀ መንበርነቷን በይፋ አስረክባለች። የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ ከፕሬዜዳንት ማኪ ሳል የሊቀመንበርነቱን ቦታ የተረከቡ ሲሆን 2023ን የህብረቱ…
#AU #ETHIOPIA

የ36ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ትላንት ቅዳሜ እንዲሁም ዛሬ እሁድ ተደርጎ ተጠናቋል።

ይህን ተከትሎ የጉባኤው ተሳታፊ ሀገራት መሪዎች ወደ አገራቸው መመለስ ጀምረዋል።

እስካሁን የበርካታ ሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

እስካሁን ድረስ ወደ ሀገራቸው ከተመለሱት መካከል ፦
- የጋና፣
- የሞዛምቢክ፣
- የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣
- የኬኒያ፣
- የሩዋንዳ፣
- የሞሮኮ፣
- የማዳጋስካር ፣
- የኡጋንዳ፣
- የዚምባብዌ ፣
- አንጎላ ፣
- ደቡብ አፍሪካ ፣
- ኮንጎ ብራዛቢል፣
- ቻድ እንዲሁም የሴንትራል አፍሪካ ሪፐብሊክ መሪዎች ይጠቀሳሉ።

የተመድ ዋና ፀሀፊት አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ ሌሎችም የጉባኤው ተካፋዮች ተሸኝተዋል።

መሪዎቹ ትላንትናና ዛሬ በአዲስ አበባ በተካሄደው ጉባኤ ላይ ከመሳተፍ ባለፈ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር የሁለትዮሽ ውይይቶችን አድርገዋል።

በሌላ በኩል የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 36ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ #በሰላም መጠናቀቁን ገልፀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉባኤው በሰላም እንዲጠናቀቅ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን " ኢፍጣራችን ለወገናችን " በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጧር ስነስርዓት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚሁ ዝግጅት ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምዕመን ተገኝቶ ስነስርዓቱን እየታደመ ነው። @tikvahethiopia
#AddisAbaba

የዘንድሮው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጧር ስነስርዓት በአዲስ አበባ ከተማ ተካሄደ።

የዘንድሮው ኢፍጧር ስነስርዓት " ኢፍጧራችን ለወገናችን " በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን እጅግ ከፍተኛ የሆነ ምዕመን ስነስርዓቱን ታድሟል።

በሌላ በኩል ፥ የአዲስ አበባ ፖሊስ የኢፍጧር ፕሮግራሙ #በሰላም_መጠናቀቁን አሳውቋል።

ለፕሮግራሙ በሰላም መጠናቀቅ የከተማው ነዋሪ በተለይም የሙስሊሙ ማህበረሰብ ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ተገቢውን ትብብር ማድረጉን ፖሊስ ገልጿል።

ለኘሮግራሙ ሠላማዊነት የድርሻቸውን ላበረከቱ እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ አካላት ምስጋና አቅርቧል።

Photo : Mayor Office & Addis TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸው እና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት 9 አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት #እንዲሾሙ ውሳኔ ማሳለፉን የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ዘግቧል። @tikvahethiopia
#Update

" የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል " - ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

- የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ #በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል።

- ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል።

- በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ዛሬ ውሳኔ ተላልፏል።

- የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን አሁን 7 አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል እነሱ በሚያቀርቡት ጥናት ሹመት ይካሄዳል። የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል። ዋናው ነገር ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመው የትኛው ነው ? የሚለውን የጉባኤው አባላት በሙሉ ተስማምቶ ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ሃሳብ፣ በመነጋገር ውሳኔ ተላልፏል።

- ረቡዕ የማጠቃላይ መግለጫ በቅዱስ ፓትርያርኩ ይሰጣል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ፦

" ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን፤ ምዕመናን በሙሉ ተጨንቃችኃል፤ አንዳንድ ጊዜ እውነት ነው ሌላ ጊዜ ወሬም ብዙ ይበዛል በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን በጣም ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን ፤ በእውነት እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ግሩም የሆነ የትምህርት ጊዜ፣ ግሩም የሆነ የውይይት ጊዜ ፣ ቤተክርስቲያን ለይተን የምትፈልገው ምንድነው የሚለውን የተወያየንበት ጊዜ ነው ፤ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን !! "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታላቁ አንዋር መስጂድ በሰላማዊ ምእመናን ላይ የደረሰውን ጉዳት ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ከሚመለከተው የፌደራል ፓሊስ ኮሚሽን ጋር የተፈጠረውን ቀውስ ለማረጋጋት እና ባስቸኳይ የተጎዱትን ለማትረፍ በሚቻልበት መንገድ ላይ እየተነጋገሩ መቆየታቸው ተሰምቷል። በተፈፀመው ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ወደ…
#Update

" በአንዋር መስጂድ የነበሩ በቁጥር እጅግ በርካታ ሰዎች በሰላም እንዲወጡ ተደርጓል " - የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ እና የበላይ አመራሮች በአንዋር መስጂድ ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ የማረጋጋት ስራ በመስራት አንድ ሸሂድ (መስዋእት) የሆነ ሙስሊም እና ጉዳት የደረሰባቸውን ወደ ሆስፒታል እንዲሄዱ ማድረጋቸውን ም/ቤቱ አሳውቋል።

የጁመዓ ሰላት ለመስገድ በአንዋር መስጂድ የተገኙና በተፈጠረው ችግር ምክንያት በመስጂዱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ታግተው የቆዩ ምእመናንም ወደየቤታቸው #በሰላም ሸኝተዋል።

አንድም ሰው እንዳልቀረ ካረጋገጡ በኃላ አመራሮቹ የመስጂዱን ቅጥር ጊቢ ለቀው መውጣታቸው ተገልጿል።

ከፍተኛ ም/ቤቱ ፤ " ለሞቱት ጀነት እንዲወፍቃቸው፣ ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ ለተጎዱትም ቶሎ ማገገምን ይቸር ዘንድ አላህን እንጠይቃለን " ብሏል።

በቀጣይ ህዝበ ሙስሊሙ እየተፈፀሙበት ያለውን አላግባብ የመብት ጥሰቶች በተገቢው መልኩ መፍትሄ ያገኝ ዘንድ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ጠቅላላ ጉበኤ ውሳኔ መሰረት የተቋቋመውን ዘጠኝ አባላት ያሉት ኮሚቴን እና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የሚሰጠውን አቅጣጫ እንደ መሪ ተቋም በማክበር ተግባራዊ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

መረጃው የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amahara በአማራ ክልል ከሚገኙ ከተሞች አንፃራዊ የሚባል ሰላም እና መረጋጋት የነበራት ባህር ዳር ዛሬ በተለያዩ አካባቢዎች በተኩስ ስትናጥ መዋሏን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ከስፍራው ዘግቧል። ምንም እንኳን ስለደረሰው ጉዳት የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ትላንት ማታ ቦምብ የፈነዳ ሲሆን ዛሬ ቅዳሜ ከጥዋት ጀምሮ በተለይ  " ቀበሌ 14 " በሚባለው አካባቢ ላይ መንገዶች ተዘግተው ፤ የንግድና ትራንስፖርት እንቅስቃሴ…
#Amhara

በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች ያለው ውጥረት አሁንም የቀጠለ ሲሆን በተለያዩ ቀጠናዎች ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

በክልሉ ባለው ግጭት እና ፍጥጫ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት ተስተጓጉሏል ፣ የኢንትርኔት አገለግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ አካባቢዎች በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ናቸው።

" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ " ዋና ሰብሳቢ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አግልግሎት ዳይሬክትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ትላንት እሁድ በሰጡት ማብራሪያ፤ በአማራ ክልል የተጣለውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያስፈጽመው ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ሕግ የማስከበር ሥራውን በማከናወን ክልሉን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው በአጭር ጊዜ እንዲመለስ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

አቶ ተመስገን ፤ አማራ ክልል የተከሰተው በትጥቅ የታገዘው እንቅስቃሴ " የክልሉን መንግሥት በማፍረስ ወደ ፌደራል መንግሥቱ የሚዞር ግብ ያለው " ነው ብለዋል።

በክልሉ የተለያዩ ክፍሎች ሕገወጥነት ተከስቷል ያሉት ሰብሳቢው ፤ " የተደራጁ ዘራፊ ቡድኖች " ሲሉ የጠሯቸው አካላት በክልሉ ውስጥ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን #ተቆጣጥረው የፍትሕ እና የሕዝብ ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ ከማስተጓጎል ባሻገር " በአንዳንድ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችን ሰብረው ወንጀለኞችን እንዲያመልጡ እስከማድረግ የደረሰ ውንብድና ፈጽመዋል " ብለዋል።

በክልሉ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር እንዲሁም የመንግሥት እና የፓርቲ መዋቅርን የማጠናከር ሥራዎችን ለማከናወን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ክልሉን በአራት ኮማንድ ፖስቶች ማዋቀሩን አስታውቀዋል።

• የመጀመሪያው የምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ምሥራቅ እና ምዕራብ ጎጃም
- ደብረ ማርቆስ ከተማ፣
- የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን
- ባሕር ዳር ከተማ ያሉበት ነው።

• ሁለተኛው የሰሜን ምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ሰሜን፣ ምዕራብ፣ ማዕከላዊ እና ደቡብ ጎንደር
- ጎንደር ከተማ
- ደብረታቦር ከተማ የሚገኙበት ነው።

• ሦስተኛው ኮማንድ ፖስት ማዕከላዊ ሸዋ ፦
-  ሰሜን ሸዋ፣
- የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን
- ደብረ ብርሃን ከተማን ያካተተ ነው።

• አራተኛ የምሥራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ኮምቦልቻ እና ወልዲያ ከተሞች - ሰሜን እና ደቡብ ወሎ
- ዋግ ኽምራን ያካተተ መሆኑን የዕዙ ሰብሳቢ ገልጸዋል።

አቶ ተመስገን ፤ በክልሉ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር እና የሚነሳ የትኛውንም ጥያቄ መንግሥት #በሰላም_ምላሽ_ማግኘት_አለበት ብሎ በጽኑ እንደሚያምን የገለፁ ሲሆን ሕግ እና ሥርዓት የማስከበሩ ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በአማራ ክልል ፤ ባለፉት ጥቂት ወራት ተቃውሞና ግጭቶች የነበሩ ሲሆን ከሰሞኑን ግን ግጭቶቹ ተስፋፍተው ወደ ትልልቅ ከተሞች ደርሰዋል።

ከመንግሥት ፀጥታ ኃይል ጋር ግጭት ውስጥ የገቡት የፋኖ ታጣቂዎች ፤ በተለይ " ከአማራ ልዩ ኃይል መፍረስ ጋር በተያያዘ የ #አማራ_ህዝብ እና #ክልልን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ውሳኔ ነው የተወስነው ፤ ሌሎችም የህልውና ጥያቄዎች አሉብን " በማለት ወደ ግጭት መግባታቸው ይነገራል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ይጎብኙ 🖼  . . .  #ይምረጡ

በ13 ቡድን የተከፈሉና 80 ወጣቶች #በሰላም ዙሪያ ያላቸውን ሀሳብ ክህሎታቸውን ተጠቅመው የገለጹበት የስዕል ኤግዚቢሽን ለተመልካቾች ክፍት ተደርጓል።

ጎብኚዎች የስዕል ሥራዎቹን፣ የተወዳዳሪዎቹን ሀሳብ እንዲሁም የወደዱትን ሥራ ላይ ድምጽ የሚሰጡበት የዲጂታል ኤግዚቢሽን ሲሆን በተመልካች እና በዳኞች በሚሰጥ ድምጽ አሸናፊዎች የሚለዩ ይሆናሉ።

ሪድም ዘ ጀኔሬሽን ባዘጋጀው በዚህ የስዕል ውድድር ፦
- አንደኛ ለሚወጣው ቡድን የ60,000 ብር፤
- ሁለተኛ ለሚወጣው ቡድን የ40,000 ብር፤
- ሦስተኛ የሚወጣው ቡድን ደግሞ የ25,000 ብር 
- በማኅበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላገኘው የሥዕል ሥራ የ10,000 ብር ሽልማት ያገኛሉ።

የሥዕል ስራውን ይጎብኙ፤ ለወደዱት ሥዕል ድምጽ ይስጡ 👉 https://redeem.tikvahethiopia.net/
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በዓሉ #በሰላም ተጠናቋል " - ግብረ ኃይሉ

የ2016 የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርአቱን በጠበቀ መልኩ #በሰላም መከበሩን የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል።

ግብረ ኃይሉ ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል ያለድ የዘንድሮው የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተከብሮ #መጠናቀቁን ገልጿል።

የነገው የሆራ አርሰዴ ኢሬቻ በዓለም በተመሳሳይ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ እና ለፀጥታ ኃይሉ እገዛውን እንዲያጠናክር ተጠይቋል።

@tikvahethiopia
ቪድዮ፦ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን በረራ ላይ ሳለ #መስኮቱ_መገንጠሉን ተከትሎ አንድ የአሜሪካ አየር መንገድ አውሮፕላኑን ከበረራ አግዶታል።

የአሜሪካው አላስካ አየር መንገድ በቁጥር 65 የሆኑ 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖቹን አግዷል።

እገዳው በበረራ ወቅት የአንደኛው አውሮፕላን መስኮት ተገንጥሎ አውሮፕላኑ በአስቸኳይ ለማረፍ ከተገደደ በኋላ ነው።

አርብ ዕለት በኦሬጎን ግዛት ከፖርትላንድ ከተማ ተነስቶ ወደ ካሊፎርኒያ ሲበር የነበረው አውሮፕላን የገጠመውን አደጋ ተከትሎ ከ35 ደቂቃዎች በረራ በኋላ በመነሻው ለማረፍ ተገዷል።

አየር መንገዱ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩት 177 ተሳፋሪዎች እና ሠራተኞች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው አውሮፕላኑ #በሰላም አርፏል ብሏል።

የአደጋው መንስዔ እስኪጣራ ድረስ ሁሉንም 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖች በጊዜያዊነት ከበረራ እንዳገደ አየር መንገዱ አስታውቋል።

ይህ ቦይንግ ሰራሹ አውሮፕላን ባለፉት ዓመታት መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።

ከአምስት ዓመት በፊት #በኢትዮጵያ እና #ኢንዶኔዢያ ባጋጠመ አደጋ ምክንያት ከበረራ ታግዶ የነበረው ይህ ማክስ 737 ዝርያ መሆኑ ይታወቃል። #BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፥ " በወረራ " ተይዘዋል ያሏቸውን የትግራይ ክልል ግዛቶችን በሰላም ስምምነቱ መሰረት ነጻ እንዲወጡ እና የአካባቢዎቹ ሰላምና ደህንነት ተረጋግጦ ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ኃላፊነት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት…
" ስጋት ፈጥሮብናል " - ኤምባሲዎቹ

ሰሞነኛውን የሰሜን ኢትዮጵያን ጉዳይ አስመልክቶ በአዲስ አበባ የሚገኙት ፦
- የካናዳ፣
- የፈረንሳይ፣
- የጀርመን፣
- የጣሊያን፣
- የጃፓን፣
- የእንግሊዝ እና የአሜሪካ ኤምባሲዎች የጋራ አጭር መግለጫ አውጥተዋል።

በዚህም ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ " #አወዛጋቢ " በሆኑት አካባቢዎች ከሰሞኑን የተፈጠረው ግጭት " ስጋት ፈጥሮብናል " ብለዋል።

ሁሉም ወገኖች የታጣቂ ኃይሎች ትጥቅ ማስፈታት ፣ ብተና እና መልሶ ማቋቋም /#DDR / እንዲሁም ተፈናቃዮችን #በሰላም ወደ ነበሩበት መመለስ ላይ አበክረው መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

" ውጥረቱ እንዲረግብ እና #ሰላማዊ_ሰዎች ጥበቃ እንዲደረግላቸው እናሳስባለን " ብለዋል።

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የተወሳሰቡ የፖለቲካና የጸጥታ ቀውሶችን ለመፍታት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት ማድረግ ብቸኛው መንገድ ነው ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #EOTC " የቤተ ክርስቲያን መከራ ከውጭ ብቻ አይደለም ከውስጥም እንጂ፤ ከባዕድ ብቻም አይደለም ከወዳጅም እንጂ ፤ የወዳጅ ፈታኝ እንደሚብስም ታውቆ ያደረ ነገር ነው " - ቅዱስነታቸው ግንቦት ወር ላይ የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተጀመረ።   የጉባኤውን መጀመር አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ…
#EOTC #ETHIOPIA

ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፦

" የማኅበረሰባችን ችግር በቤተ ክርስቲያን ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ በሀገር ደረጃ እየቀጠለ ያለው አለመግባባትም ለጠቅላላ ማኅበረ ሰባችን ፈተና ከሆነ ውሎ አድሮአል፤ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተና ምንጭ ከሆኑትም አንዱና ዕድል ሰጩ ይህ ሀገራዊ አለመግባባት ነው።

በዚህ አለመግባባት ምክንያት ገዳማውያን መነኮሳት፤ መምህራን ካህናት ምእመናን አብያተ ክርስቲያናት ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ #በሰላም_ወጥቶ_መግባትም_አጠራጣሪ_ሆኖአል ፤ ይህንን ችግር ለመፍታት የሚደረግ ጥረትም ጎልቶ አይታይም፡፡

በመሆኑም ይህ ክሥተት እውን ኢትዮጵያውያን የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት የማንችል ሰዎች ነን ወይ ? ለኛስ ከኛ የበለጠ ማን ይመጣልናል ? የሚለውን ጥያቄ ልናነሣ ግድ ነው። ስለዚህ ለሀገር ህልውናና ድኅነት የሚበጅ ነገር እንዲመጣ ቤተ ክርስቲያን ባላት ሃይማኖታዊና ሰብአዊ ኃላፊነት ጠንክራ መስራት ይጠበቅባታል። "

#ኦርቶዶክስተዋሕዶ #ኢትዮጵያ
#የግንቦት_ርክበ_ካህናት_ቅዱስ_ሲኖዶስ_ምልአተ_ጉባኤ

@tikvahethiopia
#OROMIA #PEACE

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ... ለሰላም ክፍት ነን ድርድሮችም እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም ቢሆን ያሉ ችግሮች #በሰላም እንዲፈቱ መንግሥት #ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

የክልሉ መንግሥት አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በአዲስ አበባ እንደመከሩ ተነግሯል።

በምክክሩ ላይ የተገኙት የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ውይይቱ ልማትና ጸጥታ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ሲሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

በውይይቱ ፦

- የልማት ስራ ያለ ሰላም ውጤት አልባ እንደሆነ / ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት እንደሆነ ፤

- ሰው ሰርቶ የሚበላው ፣ ወልዶ የሚስመው ሰላም ሲኖር እንደሆነ አጽንኦተ ተሰጥቶበታል ብለዋል።

" ሰላም ለመንግሥት ብቻ የተተወ ስላልሆነ እንዴት ነው አብሮ መስራት የሚቻለው ? " የሚለውም መነሳቱን አስረድተዋል።

" መንግሥት እና ሸኔ የጀመሩት ድርድር ፤ በተለያየ ምክንያት አኩርፈው ጫካ የገቡ ነፍጥ ያነገቡ ጓዶች አሉ ፤ መንግሥት በሆደ ሰፊነት ዛሬ ነገ ሳይል እነዚህን አካላት ጠርቶ በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር አለበት ይህ ሲደረግ ደግሞ ለሰዎቹ እውቅና ተሰጥቶ የህግ ከለላ ተሰጥቶ ነው ውይይት መደረግ ያለበት " የሚለውም መነሳቱን ገልጸዋል።

" በመንግሥት በኩል ' ዛሬም ቢሆን ክፍት ነው እንነጋገራለን ፣ ችግሮችን በጋራ ተነጋግረን እንፈታለን ' የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አሁንም ቢሆን የክልሉ መንግሥት በውይይት ያምናል ብለዋል።

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ሙሉ ትኩረታችን ወደ ሰላም ማምጣት ነው ያለብን። የፈለግነውን ነገር በአዳራሽ መወያይት ይቻላል። ጥረቶች ብዙ ነው ያደረግነው አሁንም ለሰላም ክፍት ነን እኛ 3ኛ ዙር ይሁን፣ 5ኛ ዙር ይሁን ፣ 10ኛ ዙር ድርድሮች እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " ብለዋል።

#Ethiopia
#Oromia #VOA

@tikvahethiopia