TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

በአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የዋጋ ጭማሪ የተደረገባቸው አገልግሎቶች ምን ምን ናቸው ?

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ ጭማሪ አድርጓል።

ተቋሙ በአንዳንድ አገልግሎቶች ላይ ያደረገው የዋጋ ጭማሪ ከፍ ያለ ነው።

ለአብነት ፦

° የተሽከርካሪ የዋጋ ግምት ማሳወቅ አገልግሎት 500 ብር የነበረው 1,000 ብር ገብቷል።

° የተሽከርካሪ የዋጋ ግምት ለሽያጭ አገልግሎት 2,310 ብር የነበረው 4,000 ብር ገብቷል።

° የተሽከርካሪ የባለቤትነት ስም ዝውውር አገልግሎት 3,000 ብር የነበረው 5,000 ብር ገብቷል።

° ለዓመታዊ ምርመራ ተለጣፊ ምልክት (ቦሎ) ግልባጭ ለመጀመሪያ ጊዜ 1,010 ብር የነበረው 2,500 ብር ተደርጓል።

° የተሽከርካሪ ባለቤት ማረጋገጫ ሊብሬ 300 ብር የነበረው 1200 ብር ተደርጓል።

° ሊብሬ ሲበላሽ ወይም ሲጠፋ ምትክ ፣ የማደሻ ቦታው ሲያልቅ መስጠት 3,000 ብር የነበረው 3,500 ብር ሆኗል።

° መረጃ መስጠት 300 ብር የነበረው 700 ብር ተደርጓል።

° አዲስ መንጃ ፍቃድ መስጠት 680 ብር የነበረው 1500 ብር ተደርጓል።

° ለጠፋ መንጃ ፍቃድ ማፈላለጊያ ለፖሊስ ወይም ለፕሬስ የሚሰጥ መረጃ 100 ብር የነበረው 700 ብር ተደርጓል።

° ከ3 ጊዜ በላይ የፅሁፍ ፈተና ለወደቁ በየወሩ ለመፈተን የሚሰጥ አገልግሎት 100 ብር የነበረው 300 ተደርጓል።

° ከ3 ጊዜ በላይ የተግባር ፈተና ለወደቁ በየወሩ ለመፈተን የሚሰጥ አገልግሎት ከ300 ብር ወደ 600 ብር ጨምሯል።

° የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ እድሳት ከ620 ብር ወደ 1000 ብር ገብቷል።

° ለጠፋ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ምትክ መስጠት 620 ብር የነበረው 5,000 ብር ገብቷል።

(ተጨማሪ በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ የተደረገውን የታሪፍ ጭማሪ ዝርዝር ከላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia

ማንቸስተር ዩናይትድ እሁድ ከምሽቱ 12፡30 ወደ ሜዳ ይመለሳል🔥
Man United vs Tottenham በSS Premier League ቻናል 223
🤔ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት መንገድ ይመለሳል?

እንዳያመልጥዎ…
👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት በቀጥታ ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በጥራትም፣ በብራንድም፣ በባትሪ ቆይታም  አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ  ሞዴል ያላቸዉ  በፈለጉት ስክሪን መጠን ኮር እና ጀነሬሽን   አሉን።

ላፕቶፕ  ከመገዛቶ በፊት ማወቅ ያለባቹሁን ወሳኝ ነገሮች እናስረዳለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ ሁሉም አሉን ። በላፕፖቻችን ጥራት ላይ አንደራደርም!
!
የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

@sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray ° " እርባና የሌለው ልዩነታችንን ትተን ለህዝባችን ሰላምና እፎይታ እንስጠው " - አቶ ጌታቸው ረዳ   ° " ሰላማዊ ፓለቲካዊ ትግላችን ማጠናከር ይገባል " - የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የ2017 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል ዛሬ በትግራይ ፣ መቐለ ጮምዓ ተራራ ሲከበር የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ እና ምክትላቸው ሌ/ጄነራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ተገኝተው…
#Tigray

" ስም በማጥፋት የሚፈታ የትግራይ ችግር የለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ መስከረም 19/2017 ዓ.ም ከትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ተወካዮች ጋር  በመቐለ የሰማእታት ሃወልት አዳራሽ ተወያይተዋል።

ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ተልእኮዎቹ በአግባቡ እንዳይወጣና እንዳይፈፅም ከቅርብና ከሩቅ የሚያጋጥሙት መሰናክሎች በመመከት በትኩረት ይሰራል "
ብለዋል።

" ስም በማጥፋት የሚፈታ የትግራይ ችግር የለም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የህዝብ ህልውና ለማረጋገጥ የምንሰራዎች የጋራ ስራዎች በአንድነት መፈፀም አለባቸው " ሲሉ አክለዋል።

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ዛሬ ከደቡባዊ ምስራቅ ዞን ተወካዮች በመቐለ የሰማእታት ሃወልት አዳራሽ ያካሄዱት ህዝባዊ ውይይት የነበረው መልክ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ታዝቧል።

" በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና በአቶ  ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት " ተብሎ ለሁለት ከተከፈለ በኋላ ዛሬ በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው መሪነት በመቐለ የተካሄደው ህዝባዊ ውይይት ከባድ ድባብ ነበረው።

ውይይቱ መስከረም 13/2017 ዓ.ም ሊካሄድ  ታቅዶ ይፋ ባልሆነ ምክንያት ወደ መስከረም 19 / 2017 ዓ.ም የተሸጋገረ ነድ።

ዛሬ በህዝባዊ ውይይቱ ለመሳተፈ በመቐለ ዙሪያ ከሚገኙ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ወረዳዎች ዶግዓ ተምቤን ፣ እንደርታ ፣ ሕንጣሎ ወጀራት ፣ ሳምረ ሳሓርቲ የተውጣጡ የህዝብ ተወካዮች በአራት አቅጣጫ ወደ መቐለ ሲገቡ በከተማዋ መግብያ የፓሊስ ፍተሻ ገጥሟቸው ነበር።

በተያያዘ ህወሓት ለዓመታት በብቸኝነት ለፓለቲካዊ ስብሰባዎቹ ሲጠቀምበት የነበረውን የሰማእታት ሃወልት አዳራሽ ለመግባት የተሰበሰበው ህዝብ የአዳራሹ ቁልፍ በሰአቱ ባለመከፈቱ ከአዳራሹ ውጭ ፀሐይ ላይ እንዲቆይ ተገዷል።

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ከተምቤን ፣ ዓዲግራት ፣ ማይጨውና ፣ መኾኒ ቀጥለው በእንዳስላሰ ሽረ ሊያካሂዱት ያቀዱት ህዝባዊ ውይይት በአዳራሽ ውስጥ በተፈጠረ አለመደማመጥና ግርግር ተቋርጦ ነበር።

ዛሬ በመቐለ ከደቡባዊ ምስራቅ ዞን ተወካዮች ያካሄዱት ውይይት " ተጨማሪ ድጋፍ ያስገኝላቸዋል ፤ የሚታየው ህዝባዊ መነቃቃት ሃሳብን በነፃነት የመግለፅና የመሰብሰብ ዴሞክራሲ መብቶች ያጎለብታል " የሚሉ ብዙሃን አስተያየት ሰጪዎች ጎን ለጎን " ፕሬዜዳንቱ የሚታይ የሚዳሰስ  ነገር ሳይሰሩ በህዝብ ደጋፍ እየሰከሩ ነው " የሚሉ አልታጡም።   

በመቐለ ዙሪያ የሚገኘው የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዶ/ር ደብረፅዮን በሚመሩት ህወሓት የፓሊት ቢሮ አባል የሆኑት ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ አቶ ፀጋይ ገብረተኽለ ዋና አስተዳዳሪ ሆኖው እንዲሰሩ በጊዚያዊ አስተዳደሩ በቅርቡ መሾማቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ መሪነት ከትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ተወካዮች  በተከናወነው ህዝባዊ ውይይት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች መገኘታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

@tikvahethiopia 
የዓመታት የቤት ጥያቄ ...

" ለልማት ተነሽዎች ለምን ቤት ተሰጣቸው አንልም ፤ ለረዥም ዓመታት ፍትሐዊነት በጎደለው መንገድ ለእኛ ሳይሰጥ መቅረቱ አሳዝኖናል " - ቅሬታ አቅራቢዎች

ለ21 ዓመታት ኮንዶሚኒየም ይደርሰናል ብለው ሲቆጥቡ የቆዩ የኮንዶሚኒየም ነባር ተመዝጋቢዎች ዕጣ ሳይወጣላቸው፣ ቤቶቹ ለልማት ተነሽዎች በመሰጠታቸው ቅሬታ አቀረቡ፡፡

ከ1997 ዓ.ም. ጀምሮ የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በዕጣ ለማግኘት ሲጠባበቁ የቆዩ በርካታ ተመዝጋቢዎች እያሉ፣ ለልማት ተነሽዎች ቤቶች መሰጠታቸው ኢፍትሐዊ እንደሆነ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል፡፡

ይህን ቅሬታ ያቀረቡት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ነው።

" ለልማት ተነሽዎች ለምን ቤት ተሰጣቸው አንልም " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎች " ለረዥም ዓመታት ፍትሐዊነት በጎደለው መንገድ ለእኛ ሳይሰጠን መቅረቱ አሳዝኖናል " ብለዋል።

ለልማት ተብሎ ቤታቸው የፈረሰባው ዜጎች ቤት ሲሰጣቸው የ1997 እና የ2005 ዓ.ም. የኮንዶሚኒየም ቤቶች ተመዝጋቢዎች ጉዳይ በዝምታ መታለፉ ቅሬታ እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል፡፡

የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ እስኪያልቅ ድረስ ለምን በመንግሥት የተሠሩ ቤቶች አይሰጡንም ? ያሉት ተመዝጋቢዎቹ፣ ለሁለት አሠርት ዓመታት ቤት ለማግኘት በመጠበቃቸው በተለየ ሁኔታ በከተማ አስተዳደሩ ሊስተናገዱ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ የቤት ኪራይና የልጆች ትምህርት ቤት ክፍያዎች ጣራ በመንካታቸው፣ ለችግር ተዳርገናል ያሉት ተመዝጋቢዎች፣ የኢትዮጵያ ዜጋ አይደለንም ወይ ሲሉም ቅሬታቸውን  አሰምተዋል፡፡

ለዓመታት ምላሽ በተነፈገው ጥያቄያቸው ምክንያት በመንግሥት ላይ ያላቸው እምነት መሟጠጡን ገልጸዋል፡፡

ተመዝጋቢዎቹ ለሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና ሌሎች ተቋማት ቅሬታቸውን ቢያሰሙም እስካሁን መፍትሔ እንዳላገኙ አክለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት ምን ምላሽ ሰጡ ?

- አጠቃላይ የቤቶች ግንባታ ከሁለትና ከሦስት ዓመት ተኩል በኋላ የብድር አቅርቦት ችግር ተጨማሪ ግንባታ ማድረግ አላስቻለም፡፡

- ችግሩ እስኪፈታ ድረስ ግንባታ አይካሄድም ፤ ኮርፖሬሽኑ ያለበትን ውዝፍ ዕዳ እስኪከፈል ድረስም ሲያገኝ የነበረው ብድር ተከልክሏል።

- ኮርፖሬሽኑ ካለበት ዕዳ ውስጥ 36 ቢሊዮን ብር ተመላሽ አድርጓል ፤ ቀሪ 37.7 ቢሊዮን ብር ያልተከፈለ ውዝፍ ዕዳ አለበት ፤ ለመክፈልም የተለያዩ አማራጮችን እያጤንን ነው።

- በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር የሚሰጠው ለማጠናቀቂያ ሥራ ብቻ ነው። ለሰፊ የቤት ግንባታ ግን ተጨማሪ ብድር አይሰጥም።

-  ለልማት ተነሽዎች ቅድሚያ መስጠትን መመርያው የሚያዝና የሚደግፈው ነው። ነገር ግን የኮንዶሚኒየም ዕጣ ጠባቂዎችን ወደ ጎን ከመግፋት ጋር መገናኘት የለበትም።

- የቤት አቅርቦት ጉዳይ የ1997 እና የ2005 ዓ.ም. የቤት ተመዝጋቢዎች ችግር ብቻ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ በቤት አቅርቦቱ በአማራጭ የቤት ልማት ላይ እየተሠሩ ነው።

- ከተለመዱት 40/60 እና 20/80 ቤቶች በተጨማሪ በ70/30 ፕሮግራምና በማኅበር ቤቶች አቅም ያላቸው እንዲገነቡ የሚያስችል አሠራር ተዘርግቷል።

- ኮርፖሬሽኑ እስካሁን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ሲገነባ የነበረው በቦንድ ግዥ ነበር፤ አሁን ግን የከተማ አስተዳደሩ ካለው በጀት ላይ እየመደበ ብድሩን እየከፈለና ለኪራይ የሚሆኑ ቤቶች እየገነባ ነው።

- ከዚህ በተጨማሪ መንግሥትና ባለሀብቶች ተቀናጅተው የሚገነቧቸው ቤቶች አሉ ፤ ለዝቅተኛ የኅብረተሰብ ክፍሎች እየተሰጡ ነው።

- የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎችን በተመለከተ ቁጠባ ያቋረጡ አሉ። ነገር ግን አሁንም ኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች የሉም ወይም ጨርሰን ሰጥተናል አላልንም።

- የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች ቅሬታ ትክክል ነው። ነገር ግን ከተማው ያለበትን የቤት አቅርቦት ችግር ሲፈታ የተመዝጋቢዎቹን ችግርም በዚያው ይፈታል።

- የነባሩ የዕጣ አወጣጥ ሒደት ቆሟል ወይም አልቆመም ብለን መናገር አንችልም፤ ምናልባት የባንክ ብድር ከተመለሰ እንደገና በሌላ ብድር ቤቶች ተገንብተው ለዕጣ ጠባቂዎች ለመስጠት ጥረት ይደረጋል።

- የተመዝጋቢዎች ዕጣ የማውጣት ሒደት ይቀጥላል ወይም አይቀጥልም የሚለው በቤት አቅርቦት ሁኔታው ይወሰናል።

- ከኮሪደር ልማት ተነሺዎች በአንድም በሌላም መንገድ ቢጣራ ተመዝጋቢዎች አሉ፡፡ ለኮሪደር ልማት ተነሽዎች የ40/60 እና የ20/80 ቤቶች ተሰጥተው አልቀው ወደ ኪራይ ቤት እየተገባ ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የሕግና የአስተዳደር በደል ምርመራ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ቀና በበኩላቸው፣ በ1997 ዓ.ም. ኮንዶሚኒየም ለማግኘት ተመዝግበው ዕጣ ያልወጣላቸውን በተመለከተ ኮርፖሬሽኑ በደብዳቤ መጠየቁን ገልጸዋል፡፡

ይሁን እንጂ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢቀርብም ምላሽ አለመገኘቱን አቶ መንግሥቱ ገልጸው፣ እንደገና በደብዳቤ ተጠይቆም ምላሽ ካልተገኘ ወደ  የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለማምራት መታቀዱን ተናግረዋል። #ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia