TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

" ኮንስታብል ማክቤል ሮባ የተባለ የፖሊስ አባል ለስራ በታጠቀው ታጣፊ ክላሽ በተኮሰው ጥይት ነው የዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ህይወት ያለፈው " - ፖሊስ

ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን የተባለ የጤና ባለሞያ በተተኮሰበት ጥይት ተመቶ #ተገድሏል

ግድያው የተፈፀመው #በፖሊስ_አባል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል።

ፖሊስ ስለጉዳዩ ምን አለ ?

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰሞኑን " ቦሌ አትላስ " አካባቢ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን በተባለ ግለሰብ ላይ ተፈፅሟል ከተባለው የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።

ፖሊስ ምርመራ መዝገቡን ዋቢ አድርጎ እንዳስረዳው በቀን 28/3/2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11:20 ሰአት ላይ ነው ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ወንጀሉ የተፈጸመበት።

ወንጀሉ የተፈፀመው ወረዳ 4 ልዩ ስሙ " አዲስ ህይወት ሆስፒታል " አካባቢ ነው ብሏል።

ዶክተር እስራኤል ያሽከረክራት የነበረችው ተሽከርካሪ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 36734 አ.አ ሲሆን፤ በወቅቱ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 የሰሌዳ ቁጥር 28177 የሆነ #ቪትስ ተሽከርካሪ የያዘ ግለሰብ የመኪና " መስታወት - ስፖኪዮ ገጭቶ አመለጠኝ " በሚል ከፍተኛ ድምጽ እያሰማ ከኋላ ይከተለው ነበር፡፡

ወደ 11፡20 አካባቢም " ፋሲካ የመኪና መሸጫ " የሚባል ቦታ ሲደርስ፤ በአካባቢው ያሉ ኑሯቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ዜጎች " ያዘው ያዘው " የሚል ድምጽ በማሰማት ከፍተኛ ግርግርና ወከባ ሲፈጥሩ፤ በዚያን ሰአት #ኮንስታብል_ማክቤል_ሮባ የተባለ የፖሊስ አባል፤ ለስራ በታጠቀው ታጣፊ ክላሽ " የመኪናውን ጎማውን መትቼ ለማስቆም " በሚል በተኮሰው ጥይት የዶ/ር እስራኤል ህይወት ሊያልፍ ችሏል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስረድቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ አንዳንድ ግዜ ወዲያውኑ መረጃ የማይሰጠው #ከምርመራ_ሂደቱ ጋር በተያያዘ የሚበላሹ ነገሮች ስለሚኖሩ ነው ያለ ሲሆን ቀጣይ የምርመራ መዝገቡ እየታየ መረጃዎችን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የትርታ ኤፍ ኤም 97.6 ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ መሆኑን ያሳውቃል።

* በጉዳዩ ላይ ከሟች ቤተሰቦች / ከቅርብ ጓደኞች መረጃ የሚገኝ ከሆነ ተከታትለን እናቀርባለን።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Kenya

ጎረቤት ኬንያ ታቃውሞ እየናጣት ነው።

መንግሥት በታክስ ላይ ጭማሪ ሊያደርግ ማቀዱን ተከትሎ በተለይም ወጣቱ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥቷል።

ከወጣቶቹ ሰልፍ ጋራ በተያያዘ ትላንት አንድ ሰው #ተገድሏል፡፡

ግድያው የተፈጸመው በፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ነው ተብሏል።

ዛሬም በናይሮቢና የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲካሄድ ውሏል።

ተቃዋሚዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሔድ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራታቸው ተነግሯል።

ይህ በኬንያ ወጣቶች መሪነት የተነሳው እና ባለፈው ማክሰኞ በናይሮቢ ከተማ ተጀምሮ በመላው አገሪቱ የተሰራጨው ተቃውሞ በመጭው ማክሰኞ ብሔራዊ የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

ተቃዋሚዎቹ ለምን አደባባይ ወጡ ?

ተቃዋሚዎች በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደስተኛ አይደሉም።

አካሄዳቸውም ለብዙ ኬንያውያን ኑሯቸውን አስቸጋሪ ማድረጉን ይገልጻሉ።

በተለይም መንግሥት አሁን ያዘጋጀው የታክስ ጭማሪ ረቂቅ አዋጅ የህዝቡን ኑሮ የሚያመሰቃቅል እንደሆነ በመግለጽ እየተቃወሙ ነው።

የታክስ ጭማሪውን በመቃወም ለወራት በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ሲደረግ ቆይቶ ነው ወደ ተቃውሞ ሰልፍ የተቀየረው።

የኬንያ መንግሥት ምን ይላል ?

መንግሥት የታክስ ጭማሪ ሊያደርግ ያቀደው ብድር ለመክፈል እና ለልማት ሥራዎች እንደሆነ ገልጿል።

ተቃውሞውን ተከትሎ ከረቂቅ አዋጁ ላይ የተወሰኑትን እንደሚተው ቢያስታውቅም ተቃውሞው ግን ዛሬም ቀጥሏል።

የታክስ ጭማሪው ምን ላይ ነው ?

መንግሥት በያዘው እቅድ የታክስ ጭማሪው በተለያዩ ሸቀጦች ላይ የሚደረግ ነው።

በነዳጅ ላይ ሊጨመር የታሰበው 9 ሺልንግ ሲሆን ጭማሪው ለፈረሱ መንገዶች መጠገኛ እንደሚሆን የአዋጁ አርቃቂዎች አስታውቀዋል።

መንግስት በተጨማሪ አካባቢን ለመጠበቅ በሚል ታክስ ለመጣል ያቀደ ሲሆን ይህም ደግሞ የፕላስቲ ውጤቶች የሚያስከትሉትን ብከላ ለመከላከል እንደሆነ አስታውቋል።

ብሔራዊ ሸንጎው ረቂቅ አዋጁን ሚቀጥለው ሳምንት እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ለተቃውሞ የወጡት ኬንያውያን ግን በተቃውሟቸው እንደሚገፉበት አስታውቀዋል።

#AFP
#VOA
#Kenya

@tikvahethiopia