TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#OFC #Ethiopia " በአንድ ፓርቲ ፍላጎትና ሙሉ ቁጥጥር በሚመራ መንገድ የ120 ሚሊዮን ህዝብ ቁመት የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በፍጹም አይፈጠርም !! " - ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦ " ዋና የኢትዮጵያ ችግር ፈጣሪ መንግሥት ነው። ይሄ ምንም ጥያቄ የለውም። ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር ሆነን ፣ከዲፕሎማቲክ…
#OromiaRegion

" ችግሮች እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ችግሮቹ እንዲወሳሰቡ እያደረጉ ያሉት እኮ እነሱ ናቸው ( ኦፌኮን ጨምሮ አንዳንድ ፓርቲዎች) " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ (ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል) ፦

" የኢፌዴሪ መንግሥት ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ፣ ያሉትን አለመግባባቶች በሀሳብ ትግል እልባት ለመስጠት ብዙ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል።

ከነዚህ ውስጥ ከሀገሪቱ ታሪክ ፣ ከሀገረ መንግስቱ ግንባታ ጋር ተያይዞ ያደሩ ቅሬታዎች ስላሉ እነዚህ ቅሬታዎች እንዲፈቱ የምክክር ኮሚሽን አቋቁሞ እየሰራ ነው።

በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት ከጠብመንጃ ይልቅ በሀሳብ ትግል እንዲደረግ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ነው የቀጠለው።

ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከማድረግ አኳያ እኛ የምንታማበት ነገር የለም።

አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች
#ኦፌኮን ጨምሮ የድርሻቸውን ባለመወጣት ፤ ችግሮች እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ችግሮቹ እንዲወሳሰቡ እያደረጉ ያሉት እነሱ ናቸው።

አንዱ የኮሚሽኑ ስራ እንዳይሳካ እራሳቸውን በማግለል እየተንቀሳቀሱ መገኘታቸው ነው።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተከሰተውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አንደኛ በሀገር በቀል በገዳ ስርዓት አባገዳዎችን ፣ የሃይማኖት አባቶችን ፣ ሃደሲንቄዎችን በማሳተፍ እርቅ እንዲወርድ ብዙ ጥረት አድርገናል። ጥረታችን አልተሳካም።

ሁለተኛ የሶስተኛ ወገኖችን ባሳተፈ መልኩ ችግሩ ይፈታ በሚል ሀሳብ ስለቀረበ ተቀብለን በሁለት ዙር ከዚህ ከአሸባሪው ቡድን (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን ማለታቸው ነው) ውይይቶችን አድርገናል። ሁኔታው በሰላማዊ መንገድ ሊፈታ አልቻለም።

ነገር ግን በአንድ እና ሁለቴ ብቻ ተስፋ የሚያስቆርጥ ሳይሆን ለሰላም ጠንክረን እንሰራለን። "

#OromiaRegionalGovernment
#VOA

@tikvahEthiopia