TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጎንደር_አረንጓዴ_አሻራ

የጎረቤት ሀገር ሱዳን ልዑካን ቡድን አባላት የአረንጓዴ አሻራ ቀንን ምክንያት በማድረግ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውሃ ከተማ ችግኝ ተከሉ።
#ጎንደር

"የኃይሌ ሪዞርት-ጎንደር ማኔጀመንት እና ሰራተኞች በጎንደር ገነት ተራራ ላይ የ #አረንጓዴአሻራ ችግኝ ተከላ አካሂደናል!"
#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ

"የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል #ሠራተኞች ዛሬ እንዲህ ነበር በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉት፡፡እናመሰግናለን፡፡"
#ጎንደር

የኢፌዴሪ ኘሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በጎንደር ከተማ የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶችን ጎበኙ። ፕሬዘዳንቷ የፋሲል ግንብን፣ የደብረ ብርሃን ስላሴ ቤተክርስቲያን አና ጥምቀተ ባህሩን ጎብኝተዋል። በተጨማሪም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህሙማን የተመላላሽ ህክምና አዲሱን የእናቶች እና ህፃናት ማዕከልን ጎብኝተዋል። በጎብኝቱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሻሸመኔ
#ሀዋሳ
#ነቀምት
#አሰላ
#አዲስአበባ
#ሽሬ
#ደብረብርሃን
#ወላይታሶዶ
#አርባምንጭ
#ጅግጅጋ
#አዳማ
#ድሬዳዋ
#ባህርዳር
#መቐለ
#ሀረር
#ጎንደር

ከሌሎች በርካታ ከተሞች ከሚገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች የSAT ውጤት ያልጠበቁት እንደሆነ በመግለፅ ቅሬታቸው እያሰሙ ይገኛሉ። የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበትም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ SELAMAWIT TEKLAY በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 618 ያስመዘገበች ጀግኒት! #ኢትዮጵያዊት

#618 #ጎንደር #ፋሲለደስ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ⬆️

5ኛ የTIKVAH-ETH የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ እንደቀጠለ ይገኛል። በቅንድል ኢትዮጵያ አማካኝነት በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ይለው የመፅሃፍ ማሰባሰብ ዘመቻ ጥሩ በሚባል ደረጃ እየሄደ ነው።

#ጎንደር
#ባህርዳር
#አዶላ
#ዲላ የሚገኙና በሌሎችም የኢትዮጵያ ከተሞች የሚገኙትን አስተባባሪዎች ስልክ እንጠቁማለን። ውድ የቤተሰባችን አባላት ቤት ካሉት መፅሃፍቶቻችሁ አንዱን ለሀገራችሁ አበርክቱ!
#GONDAR

የጸጥታ ኃይሉ #ጎንደር ላይ በአጠራጣሪ እንቅስቃሴ ላይ አገኘኋቸው ያላቸውን 38 ወጣቶች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቋል። ከተያዙት ወጣቶች መካከል አንድ ግለሰብ አራት መታዎቂያዎችን፣ ሌላ አንድ ወጣት ደግሞ 7 የውጭ ሀገር ሲም ካርዶችን እንደያዘ አረጋግጫለሁ ብሏል የከተማ አስተዳድሩ የሰላምና ደኅንነት መምሪያ፡፡

‘ሰሊጥ ለመሰብሰብ ሥራ እየሔድን ነው’ በማለት በጉዞ ላይ የነበሩ ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ 38 ወጣቶች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ትናንት ጥቅምት 10/2012 ከቀኑ 10፡00 ጎንደር ከተማ ቀበሌ 15 ላይ በጸጥታ አካላትና በወጣቶች ትብብር እንደሆነ ታውቋል፡፡

https://telegra.ph/ETH-10-22-2

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ #ጎንደር ተቋርጦ የነበረውን የበረራ አገልግሎት እንደገና ይጀምራል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው።

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 6 ሺህ 574 ተማሪዎችን ዛሬ እያስመረቀ ይገኛል፡፡

በ87 የመጀመሪያ እንዲሁም በ67 የድህረ ምረቃ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነው የሚያስመርቀው፡፡

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የውኃ መስኖ እና ኢነርጅ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ተገኝተዋል፡፡

#ደብረታቦር_ዩኒቨርሲቲ

የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያየ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ለስምንተኛው ዙር ነው ተማሪዎቹን እያስመረቀ የሚገኘው።

#ቦንጋ_ዩኒቨርሲቲ

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ 2ኛ Batch ተማሪዎች በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።

#ደብረብርሃን_ዩኒቨርሲቲ

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ13ኛ ዙር በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያስተማራቸውን በ2ኛ ዲግሪ 231 ተማሪዎችን እና በ3ኛ ዲግሪ አንድ ተማሪ እያስመረቀ ነው።

#ኮተቤ_ሜትርፓሊታን_ዩኒቨርሲቲ

የኮተቤ ሜትርፖሊታን በተለያየ የትምህርት ክፍሎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል።

ዩንቨርሲቲው በዛሬው እለት ያስመረቃቸው በመጀመሪያና ሁለተኛ ድግሪ ወንድ 448 ሴት 135 በድምሩ 583 ተማሪዎች ናቸው።

#ቅድስተ_ማርያም_ዩኒቨርሲቲ

የቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 636 ተማሪዎችን በኦሮሞ ባህል ማዕከል አስመርቋል።

አጠቃላይ ከተመረቁት ውስጥ 322 ወንዶች 314 ደግሞ ሴቶች ናቸው።

#ሀራምቤ_ዩኒቨርሲቲ

ሀራምቤ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 3683 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነዉ።

ዩኒቨርሲቲው ለ18ኛ ዙር ነው ተማሪዎችን እስመረቀ የሚገኘው።

ምንጭ፦ ኢፕድ፣ ዋልታ፣ አሚኮ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ገፅ

@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#GONDAR የጥምቀት በዓል እጅግ በድምቀት የሚከበርባት ጎንደር ከተማ ዝግጅቷ በማጠናቀው እንግዶቿን እየተጠባበቀች ነው። በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ የሚገኙ አገልግሎት ሰጪዎች ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል እና በክብር ለማስተናገድ ዝግጅታችንን ሁሉ አጠናቀናል ብለዋል። ዘንድሮ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰው የጥምቀት በዓልን ለማክበር ጎንደር ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። የከተማ አስተዳደሩ " የጥምቀት…
#ጎንደር

ከቀናት በኃላ ለሚከበረው የጥምቅት በዓል እንግዶች ከወዲሁ ወደ ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ መግባት መጀመራቸው ተሰምቷል።

የጎንደር ከተማ እና አካባቢው ሆቴሎች፣ ሎጂዎችና ሪዞርቶች ማኅበር ፤ ላለፉት ሁለት ዓመታት በኮረና ቫይረስና በጦርነት ምክንያት ተቀዛቅዞ የነበረው የቱሪዝም እንቅስቃሴ አሁን ላይ መልሶ እየተነቃቃ መሆኑን አመልክቷል።

ጎንደር እንግዶቿን በምቾት ተቀብላ ለማስተናገድ ሆቴሎቿ በቂ ዝግጅት እንዳደረጉም ተገልጿል።

ካለው ሀገራዊ የሰላም ሁኔታ ጋር ተያይዞ ለዘንድሮው ጥምቀት በዓል ወደ ጎንደር የሚገባው እንግዳ ቁጥር ከፍተኛ እንደሆነ ይገመታል።

ይህ ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን የማረፊያ እጥረት ለመቅረፍ ታሳቢ ያደረጉ የመፍትሔ ተግባራትን በከተማው ሆቴሌች እየተሰራ ስለመሆኑ ተገልጿል።

በሆቴሎች ደረጃቸውን የጠበቁ ተጨማሪ የድንኳን መጠለያ አገልግሎት ለመስጠት እንደታሰበ ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
የካንሰር ህክምና . . . #በኢትዮጵያ

#ጥቁር_አንበሳ

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፤ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ መኖራቸውን አስታውቋል።

የሆስፒታሉ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ክፍል ኃላፊ ኤዶም ሰይፉ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" የተለያዩ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠብቁ ከ2013 መጨረሻ፣ 2014 ዓ.ም. እና 2015 ዓ.ም. ወረፋ ያልደረሳቸው አሉ፡፡

ይሁን እንጂ በየዕለቱ የሚመጡ ድንገተኛ የካንሰር ታካሚዎች በመኖራቸው በቅድሚያ ለእነዚህ ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ይደረጋል።

በሆስፒታሉ ቆይተው መታከም ይችላሉ ተብለው የተለዩት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ሕክምና ለማግኘት እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ ጥረት እየተደረገ ነው።

ለዚህ ወረፋ መብዛት ዋነኛ ምክንያት ብለው ያቀረቡት በሆስፒታሉ የሚገኘው መሣሪያ #አንድ ብቻ መሆኑን ነው።

በዚህ ዓመት ብቻ በተደረገው ማጣራት የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠበባቁ 5,000 ታካሚዎች ሲኖሩ፣ በማዕከሉ በቀን በአማካይ ከ300 በላይ ታካሚዎች ይስተናገዳሉ።

ከእነዚህ የካንሰር ታካሚዎች መካከል 70 በመቶ የጨረር ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ፣ ኬሞ ቴራፒ የሚያስፈልጋቸው የታካሚዎች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም ።

በማዕከሉ አገልግሎት ለማግኘት የ2014 ዓ.ም. እና በ2015 ዓ.ም. ሕክምና ለማግኘት የተመዘገቡ ደግሞ ከ10,000 በላይ ናቸው። "

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ_ስፔሻላይዝድ_ሆስፒታል

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክሊኒካል ኢንኮሎጂስት ዶ/ር አማረ የሺጥላ ምን አሉ ?

"  በሆስፒታሉ የሚሰጠው የካንሰር ሕክምና ኬሞ ቴራፒና ቀዶ ጥገና ነው።

የጨረር ሕክምና ለመጀመር የማሽን ተከላ ላይ እንገኛለን። 60 በመቶ የሚሆነው የካንሰር ታካሚ እስኪጠናቀቅ እየተጠባበቁ ነው።

በሆስፒታሉ ካንሰር ሕሙማን ሕክምና አንዱ የሆነው ኬሞ ቴራፒ ሕክምና ለማግኘት ወረፋ በዛ ከተባለ ከሳምንት አይበልጥም።

ይሁን እንጂ ለካንሰር ሕሙማን የሚሰጠው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለመጠባበቅ ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት ያስፈልጋል። "

#በሐሮሚያ_ዩኒቨርሲቲ_ሕይወት_ፋና_ሆስፒታል

በሐሮሚያ ዩኒቨርሲቲ ሕይወት ፋና ሆስፒታል በካንሰር ሕክምና ረዳት ፕሮፌሰር ሚካኤል ሻውል (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" በሆስፒታሉ የኬሞ ቴራፒና የጨረር ሕክምና ለካንሰር ሕሙማን እየተሰጠ ነው።

የጨረር ሕክምና ከተጀመረ ስድስት ወራት አስቆጥሯል ፤ የታካሚዎች መጠነ መጠበቅ ከሦስት ወራት አይበልጥም።

በሆስፒታሉ በዓመት እስከ 6000 የካንሰር ታካሚዎች ሕክምና ያገኛሉ። በተለይ ደግሞ ጨረር ሕክምና ከተጀመረ በኋላ የታካሚዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።

ሆስፒታሉ በምሥራቅ ኢትዮጵያ እስከ ቅርብ ጊዜያት ብቸኛው የካንሰር ሕክምና መስጫ በመሆኑ ከሶማሌላንድና ከሌሎች አገሮች እየመጡ አገልግሎት የሚያገኙ ነበሩ። "

Via Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቅን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነገ መግለጫ ሰጥተዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ምን አሉ ? - ፈተናው ከኩረጃና ስርቆት በፀዳ መልኩ ተሰጥቶ ተጠናቋል። - ፈተናውን ለመፈተን በአጠቃላይ 868 ሺህ 74 ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን ፤ ከነዚህም ውስጥ 840 ሺህ 859 ፈተናውን…
#ጎንደር

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለፈተና የገቡ 16 ሺህ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የትላንት ሰዓት እና የዛሬውን ፈተና እንዳልወሰዱ የትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

ሚኒስቴሩ ፤ በማራኪ ፣ ቴዎድሮስ ፣ ፋሲል ግቢ ለፈተና የገቡ ተማሪዎች በአካባቢው በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ፈተናቸውን ሳይወስዱ እንደቀሩ አመልክቷል።

በዕለቱ በነበረ የተኩስ ልውውጥም 1 ፈታኝ / የፈተና አስፈፃሚ እና 2 የፌዴራል ፖሊስ አባላት ሲገደሉ ፤ አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል ደግሞ ቆስሏል።

በአጠቃላይ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ፈተናቸውን መፈተን ያልቻሉ 16 ሺህ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በቀጣይ በሚመቻችላቸው መርሐ ግብር ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ጎንደር ካጋጠመው ችግር ውጭ በሌሎች የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉም ፈተና ተሰጥቶ መጠናቀቁን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቅን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነገ መግለጫ ሰጥተዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ምን አሉ ? - ፈተናው ከኩረጃና ስርቆት በፀዳ መልኩ ተሰጥቶ ተጠናቋል። - ፈተናውን ለመፈተን በአጠቃላይ 868 ሺህ 74 ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን ፤ ከነዚህም ውስጥ 840 ሺህ 859 ፈተናውን…
#Update

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አንድ መምህሩ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አስፈታኝነት ተመድበው ባቀኑበት #ጎንደር ህይወታቸው ማለፉን ይፋ አድርጓል።

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ተግባቦት መምህር የነበሩት ታደሰ አበበ ገብረሀና (ረ/ፕ/ር) ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመስጠት ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በፈታኝነት ተመድበው በሔዱበት ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ/ም ህይወታቸው ማለፉን ተቋሙ አመልክቷል።

በ38 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት የተለዩት መምህር ታደሰ አበበ፤ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከህዳር 2009 - 2013 ዓ.ም በእንግሊዘኛ ቋንቋና ስነ-ጽሁፍ ትምህርት ክፍል በመምህርነትና በኃላፊነት ያገለገሉ ሲሆን ከየካቲት 2013 ዓ.ም ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ምክትል ዲን በመሆን እያገለገሉ ነበር፡፡

መምህር ታደሰ አበበ ባለትዳርና የ3 ሴት ልጆች አባት ነበሩ፡፡

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gondar የጎንደር ግጭት ከተማዋን አስከፊ ሁኔታ ላይ እንደጣላት አንድ በጎንደር ሆስፒታል የሚሰራ የቲክቫህ የቤተሰብ አባል የሆነ የሕክምና ዶክተር አሳውቆናል። የጎንደር ሁኔታ #እጅግ_አስከፊ እንደነበር የገለፀልን የህክምና ዶክተሩ " በግጭቱ ምክንያት የመጨረሻ ኢሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሟል ፤ ሰላማዊ ዜጎች እዚህም እዚያም ተገድለዋል " ሲል አስረድቷል። በሆስፒታሉ ውሃ ፣ ኦክስጂን ፣ እንዲሁም ደግሞ…
#GONDAR

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የህክምና ዶክተር የሆነው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በከተማው ስላለው ሁኔታ መረጃዎችን አጋርቶናል።

- ታማሚዎች በኦክስጂን እና ደም እጥረት እየሞቱ መሆኑን ገልጿል።

- ለአምቡላንስ ጨምር ምንምአይነት የትራንስፖርት አማራጭ እንደሌለ ፤ ታማሚዎች በሰው ኃይል በሸክም ወደ ሆስፒታሉ እየመጡ መሆኑን አስረድቷል።

- ወደ 20 (ሰላማዊ ሰዎች) ወደ ሆስፒታሉ ከደረሱ በኃላ እንደሞቱ እንዲሁም ከ200 በላይ ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታል እንደሚጡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች መሆናቸውን ገልጿል።

- በርከታ ሰዎች በቤታቸው ሞተው፣ ቀብራቸውም በአካባቢያቸው በተለይም በቀበሌ 4 ፣ 12 ፣ 11 እና 18 መፈፀሙን አመልክቷል።

- ባለፈው ሰኞ በነበረ ግጭት ከሆስፒታሉ የተወሰኑ ህፃዎች በመሳሪያ ቢመቱትም የተጎዳ ሰው ግን እንዳልነበር ገልጿል።

- ሆስፒታሉ ምግብ እንዲሁም መድሃኒት እያለቀበት መሆኑን አመልክቷል።

ዛሬ ጎንደር እንዴት ናት ?

አሁን ላይ በጎንደር ከተማ ከየትኛውም አቅጣጫ የተኩስ ድምፅ እየተሰማ አይደለም። ጥዋት ላይ ለጥቂት ሰከንድ ፒያሳ እና ቀበሌ 18 አካባቢ ተኩስ ተሰምቶ ነበር።

ከትላንት ማታ አንስቶ ዛሬም ጥዋት በከተማው አብዛኛው ክፍል ላይ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለ ሲሆን ሰራዊቱ በሆስፒታሉ አካባቢም መኖሩን ይኸው ዶክተር ገልጿል።

የህክምና ዶክተሩ ከምንም በላይ በሆስፒታል ያለው የኦክስጅን ፣ የደም እጥረት እንዲሁም የአምቡላንስ ትራንስፖርት ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመግለፅ መፍትሄ እንዲፈለግ ጥሪ አቅርቧል።

ጥንታዊቷ እና ታሪካዊቷ #ጎንደር ባለፉት ቀናት ከፍተኛ የሆነ ግጭት ካስተናገዱ የአማራ ክልል ከተሞች መካከል አንዷ ናት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ባህርዳር #ጎንደር

ባህር ዳር ከተማ ከትላንት ለሊት ጀምሮ ዝምታ ሰፍኖባት እንደምትገኝና ዛሬ የሟቾች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም እንደነበር ነዋሪዎቿ ተናግሩ።

ባለፉት ቀናት በከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ስትናጥ የነበረችው ባህር ዳር ከተማ ከለሊት ጀምሮ ፀጥ ብላ መዋሏን ነዋሪዎች መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

በሌላ በኩል ፤ ዛሬ በባህር ዳር በግጭቱ የሞቱ ሰዎች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም መዋሉን ነዋሪዎቹ አመልክተዋል።

ትላንት በቀበሌ 13 ፣ 14 እና 16 በነበረ ውጊያ በርካታ ሰዎች #መሞታቸው እና #መጎዳታቸው ተነግሯል። እነዚሁ ሟቾች ስርዓተ ቀብራቸው ዛሬ በተለያዩ ስፍራዎች ሲፈፀም ውሏል።

ነዋሪዎቹ በጦርነቱ ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈው አብዛኞቹ ከጦርነቱ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰዎች መሆናቸውን ገልጽዋል።

የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት (AFP) ያነጋገራቸው ሁለት ዶክተሮች በውጊያው ሰላማዊ ሰዎች ስለመገደላቸው ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ የባህር ዳር ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ሬድዮ በሰጡት ቃል ከከተማው ማረሚያ ቤት 2 ሺህ የሚጠጉ ታራሚዎች ሲወጡ መመልከታቸውን ጠቁመዋል።

በጎንደር ዳግሞ ዛሬ ከሰሞኑን የተሻለ መረጋጋት እንዳለ ነዋሪዎች ገልጸዋል። የመንግሥት ጦር በከተማው ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን የተደረደሩ ድንጋዮችን ሲያነሱ መዋላቸውን ነዋሪዎች ጠቁመዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተጨማሪ

የባህር ዳር ፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት ነዋሪዎች ምን አሉ ?

የባህር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዎች ከተማቸው በመከላከያ ሰራዊት ስር እንደሚገኝና ዛሬ ተኩስ እንዳልነበር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

#ባህርዳር

ነዋሪ 1

" ከትለንት ከግማሽ ለሊት በኃላ መከላከያው ተቆጣጥሮታል።

ተኩስም የለም፤ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። አንፃራዊ ሰላም አለ።

መከላከያው ነው እየተንቀሳቀሰ ያለው። ሰውም እንደ ሰሞኑን ሳይሆን መንቀሳቀስ ጀምሯል። ግን አገልግሎት መስጫ ተቋማት ዝግ ናቸው በተረፈ ቁስለኛ እየተነሳ ሃኪም ቤት እየሄደ ነው ፣ የሞተውም እየተቀበረ ነው።

ዘንዘልማ አካባቢ ብዙ ሰው ስለሞት እነሱ እየተነሱ እየተቀበሩ ነው። ከሟቾች ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ የተወሰኑ ናቸው እንጂ በቤተሰብ አማካኝነት እዛው እየተቀበረ ነው። ብዛት ያለው ሰው ደግሞ ከመኮድ ይወረወር የነበረ ከባድ ተወዋሪ መሳሪያ እሱ ነው ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰው። መኖሪያ ቤት ላይ እየወደቀ፤ ህፃናቶችም ሞተዋል።

ቁጥሩን ባልገልፅም ብዙ ሰላማዊ ሰው ሞቷል፣ በተለይ ቀበሌ 14 ላይ ከፍተኛ ውጊያ ነበር፤ በጣም ብዙ ሰው ሞቷል። ዛሬ ብዛት ያለው ሰው ቀብር ነው የዋለው። ህዝቡ እየወጣ መቅበር ጀምሯል። "

ነዋሪ 2

" እኛ ኤርፖርት አካባቢ ነን። ዛሬ ሰላም ነው። ተኩስም የለም። የተረጋጋ ነው። ግን ብዙ ሰው ፍራቻ ስላለው ወደ ከተማ አይሄድም። በጣም ብዙ የሞተ ሰው ስላለ ፍራቻ አለ። ነገር ግን ከንጋት ጀምሮ ምንም ድምፅ የለም።

በአብዛኛው ሲቪልያን ነው የሚሞቱት ካለመሳሪያ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ፣ የሚታኮሱት አይደለም የሚሞቱት በብዛት። ጀሌው አለ አይደል በአጋጣሚ መንገድ ለመዝጋት የሚሄደው ነው። "

#ጎንደር

ነዋሪ 1

" ጎነደር ከትላንት ማታ ጀምሮ ማለት ይቻላል ተኩሱ ቆሟል። መከላከያው ከተማው ውስጥ ያሉትን መንገዶች የማፅዳት ስራ እየሰራ ነው ያለው። መንገዶች በድንጋይም፣ በእንጨትም ተዘጋግተው ስለነበር።

ሌሎች እንቅስቃሴዎች ገና ናቸው። የሰው እንቅስቃሴም የለም። ቤት ውሥጥ ቁጭ ብለን ነው የሰነበትን ዛሬ ሳምንታችን ነው። የሚቀጥለው ምን እንደሚሆን እየጠበቅን ነው።

በትክክል ስለደረሰው ጉዳት ይህ ነው ማለት ባልችልም፤ ሰው ግን ለሳምንት ከገበያ ከሌሎችም አገልግሎቶች ተገልሎ መቆየቱ ብዙ ሰው አላሰበውም እሮብ ማታ ድረስ ጤናማ ስራውን እየሰራ ከዚያ ምሽት በኃላ ግን መውጣት መግባት  የማይቻልበት፣ የጥይት ድምፅ የከባድ መሳሪያ ሲስተናገድ ነበር ወደ ህክምና ለመሄድም ትራንስፖርት የለም ጉዳቱ ቀላል አይሆንም። "

ነዋሪ 2

" ዛሬ ተኩስ የለም። ከተማ ውስጥ ምንም እንቅስቃሴ የለም። ከመከላከያ ውጭ የሚንቀሳቀስ የለም። ሰው ከቤት አልወጣም።

ሰላማዊ ሰዎች ብዙ ተጎድተዋል።

ህክምና ለማግኘትም አልተቻለም። ጉዳቱ ከመብዛቱ አንፃር እንዲሁም አንስቶ የሚወስድም አልተገኘም።

የሞቱ ሰዎች ትላንት አልፎ አልፎ ተቀብረዋል። ከሟች ብዛት አንፃር ያልተቀበሩ አሉ። "

በተመሳሳይ በሸዋሮቢት ከተማ ሀገር መከላከያ የገባ ሲሆን ዛሬ የተረጋጋ ሁኔታ መኖሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በግጭቱ ሳቢያ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውና መቁሰላቸውን የገለፁት ነዋሪዎቹ የሞቱ ሰዎች እየተለቀሙ ተቀብረዋል።

አንድ ነዋሪ እሳቸው ብቻ ባረጋገጡት 13 ንፁሃን እንደሞቱ ገልፀው ሚካኤል ቤተክርስቲያን 10 ሰው፣ ማርያም 2 ሰው፣ ሙስሊም መቃብር 1 ሰው መቀበሩን መረጃ እንዳላቸው ተናግረዋል። በየገጠሩ ያለው ገና አልታወቀም ሲሉ አክለዋል።

ትራንስፖርት አለመኖሩ፣ መንቀሳቀስም አስፈሪ ስለነበር ተጎጂዎችን ወደሆስፒታል ለመውሰድ አስቸጋሪ እንደነበር ነዋሪዎች ለሬድዮ ጣቢያው ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጨማሪ የባህር ዳር ፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት ነዋሪዎች ምን አሉ ? የባህር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዎች ከተማቸው በመከላከያ ሰራዊት ስር እንደሚገኝና ዛሬ ተኩስ እንዳልነበር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል። #ባህርዳር ነዋሪ 1 " ከትለንት ከግማሽ ለሊት በኃላ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። ተኩስም የለም፤ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። አንፃራዊ ሰላም አለ። መከላከያው…
የአማራ ክልል ከተሞች እንዴት ዋሉ ?

በአማራ ክልል በትልልቆቹ ከተሞች በዛሬው ዕለትም ተኩስ ሳይሰማባቸው መዋላቸውን ፤ ነገር ግን መደበኛ እንቅስቃሴ እንዳልተጀመረ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ነዋሪዎች ምን አሉ ?

#ባሕርዳር

ዛሬ  የተኩስ ድምጽ አለመሰማቱን ፤ ግጭትም ይሁን ውጊያ እንዳልነበር ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። ነገር ግን መደበኛ እንቅስቃሴ አልጀመረም።

የንግድና የተለያዩ ቋማት በአብዛኛው ባለመከፈታቸው ከተማዋ ጭር ብላ ነው የዋለችው።

የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ መኪኖች እና ባጃጆች ወደ ሥራ ባለመመለሳቸው የነዋሪው እንቅስቃሴ ተገትቶ ውሏል።

ተቋርጦ የነበረው የ ' ኢትዮጵያ  አየር መንገድ በረራ ' ወደ ባሕር ዳር መጀመሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ነገር ግን ከአውሮፕላን ማረፊያ ወደ ከተማ የሚወስድ ትራንስፖርት ስለሌለ ተሳፋሪዎች በእግራቸው ለመጓዝ ተገደዋል።

አሁንም የተወሰኑ መንገዶች በትላልቅ ቋጥኖች እና ድንጋዮች እንደተዘጉ ስለሆኑ ለትራንስፖርት አስቸጋሪ ነው።

ከተማዋ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴዋ ባትመለስም አንዳንድ ነዋሪዎች በእግራቸው ሲንቀሳቀሱ ውለዋል።

#ደብረ_ማርቆስ

በደብረ ማርቆስ ከተማ ትራንስፖርትም ሆነ የንግድ መደብሮች ወደ ስራ እንዳልተመለሱ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

" ሱቅ፣ ሆቴል ዝግ ነው። " ያሉ አንድ ነዋሪ " ምንም እንኳን በአይኔ ባላይም ጥዋት አንድ ባስ ከማርቆስ ወጥቶ ወደ አ/አ ሄዷል የሚባል ነገር አለ ፤ ከአዲስ አበባ መስመር ግን አንድ ሁለት ባሶች ማርቆስ ገብተዋል። " ሲሉ ገልጸዋል።

በደብረ ማርቆስ ወደ ጎንደር፣ ወደሌሎችም ቦታዎች የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች እንደቆሙ ናቸው ፤ መደበኛ እንቅስቃሴም አልተጀመረም።

#ደጀን

ከተማዋ አሁን ላይ የተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ ብትሆንም ሰሞኑን ከተፈጠረው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አገልግሎቶች ተስተጓጉለዋል።

የውሃ እንዲሁም መብራት አገልግሎት ከተቋረጠ ቀናት እንደተቆጠሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ አስተያየት ሰጪ ፤ በብቸና መስመር ወደ ሞጣ የሚያልፍ በርካታ የመከላከያ ኃይል እንደተመለከቱ ገልጸዋል።

ብቸና ላይ ግጭት እንደነበር የሚጠርጥሩት ነዋሪው ሥፍራው ከደጀን ከ35 ኪሎ ሜትር ርቀት በላይ ቢሆንም የከባድ ተኩስ ድምፅ ግን ይሰማ እንደነበር ጠቁመዋል።

#ጎንደር

ከትላንት #ረቡዕ ጀምሮ ተኩስ እንደማይሰማና አሁን ላይ ሰላም መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ሰዎች በእግር ይንቀሳቀሱ እንጂ፣ ተሽከርካሪ የለም።  በብዛት ሱቆች እና ወፍጮ ቤቶች አገልግሎት እየሰጡ አይደለም።

በከተማው የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲከፈቱ ቢታዘዙም ሁሉም ሙሉ በሙሉ እንዳልተከፈቱ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በጎንደር የመከላከያ ሠራዊት አባላት እና ታንኮች በተለይ ደግሞ አድማ በታኞች በስፋት እንደሚታዩ ተነግሯል።

ዛሬ ወደ ጎንደር ከተማ በረራ ይጀመራል ቢባልም ወደ ከተማው አውሮፕላን እንዳልገባ ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል።

#ደብረብርሃን

በደብረ ብርሃን ሱቆች እና ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ወደ አገልግሎት እየተመለሱ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ አስተያየት ሰጪ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ባጃጅ መንቀሳቀስ መጀመሩን ጠቁመዋል። ዛሬ ደግሞ ሱቆች መከፈታቸውንና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች ፍተሻ እያደረጉ መሆኑ ተመላክቷል።

#ላሊበላ

" ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ባይሆንም " የመንግስት ሰራተኞች ወደ ስራ መግባታቸው ፣ ተቋማት እና ተሽከርካሪዎች በተወሰነ ደረጃ ስራ እንደጀመሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ከወትሮው የተለየ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳልታየ የገለፁት ነዋሪዎች የአውሮፕላን በረራ እንዳልተጀመረና የበረራው መጀመር እየተጠበቀ መሆኑን ጠቁመዋል።

በላሊበላ በረራ ለመጀመር ቀናት ሊፈለግ እንደሚችል ተነግሯል።

#ደብረታቦር

የከተማዋ እንቅስቃሴ በጣም ቀዝቃዛ ነው። ነዋሪው በጊዜ  ነው ወደ ቤቱ እየገባ ያለው።

አሁን ላይ በከተማዋ ፤ ምንም ዓይነት የተኩስ ድምፅ ባይሰማም  በከተማዋ የጦር መሣሪያም ሆነ ስለት ያለው ቁስ ይዞ መንቀሳቀስም ሆነ መገኘት አደጋ እንደሆነ ነዋሪዎች ገልጻዋል። ይህን ይዞ የተገኘ ሰው እርምጃ ይወስድበታል ብለዋል።

ሆቴሎችና ባንኮች ዝግ እንደሆኑ ይገኛሉ።

ምንም እንኳን በከተማው ላይ የተረጋጋ ሁኔታ ቢኖርም 800 መቶ ብር የነበረ የምግብ ዘይት እስለ 1500 ብር ድረስ እየተሸጠ እንዳለ ፤ ይሄም ቢሆን ሱቆች አሁንም ዝግ ስለሆኑ በሰው በሰው የሚገኝ እንደሆነ ተጠቁሟል።

መረጃው ከኤኤፍፒ፣ ዶቼቨለ፣ ቢቢሲ የተሰባሰበ ነው።

NB. የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ፦
- በባህር ዳር ፣
- በደብረ ማርቆስ፣
- በደብረ ብርሃን፣
- በላሊበላ ፣
- በጎንደር ፣
- በሸዋሮቢት ከባጃጆችና ከሞተር ሳይክሎች በስተቀር ሌሎች የከተማ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ከነሐሴ 4 ጀምሮ ወደ ሥራ የመመለስ እና አገልግሎት የመስጠት #ግዴታ_እንደተጣለባቸው ማሳወቁ ይታወሳል።

ከዚህም በተጨማሪ ፤ የሕዝብ የአገልግሎት ሰጪ ፣ የመንግሥት፣ የማኅበረሰብና የንግድ ተቋማት ከነሐሴ 4/2015 ጀምሮ ክፍት እንዲሆኑ ማዘዙ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#ጎንደር

° " የሽንኩርት ሽያጭ ዋጋ በኪሎ 60 ብር ነበር አሁን በእጥፍ አድጎ እስከ 120 ብር ድረስ እየተሸጠ ነው " - የጎንደር ነዋሪ

° " በሚታየው የዋጋ ጭማሪ ምክንያት የዕለት ከዕለት ኑሮን መግፋት አስቸጋሪ ሆኖብኛል " - የጎንደር ነዋሪ


በጎንደር ከተማ ተከስቶ የነበረውን ግጭት መነሻ በማድረግ በኢንዱስትሪና በግብርና ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ በመከሰቱ የዕለት ከዕለት ኑሯቸውን ለመምራት መቸገራቸውን ያነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡

ካነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወጣት አስተሪዮ አስማረ በሰጠው አስተያየት ቀደም የሽንኩርት ሽያጭ ዋጋ በኪሎ 60 ብር ነበር አሁን ዋጋው በእጥፍ አድጎ እስከ 120 ብር ድረስ እየተሸጠ ነው፡፡

የዘይትና የሌሎች የሸቀጥ ምርቶችም ላይም የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል፡፡

ታዲያ የዋጋ ንረት በመከሰቱ " የዕለት ከዕለት ኑሮዬን ለመምራት ተቸግሪያለሁ " ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡

ሌላው በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡት የከተማዋ ነዋሪ አቶ ጎበዬ መኩሪያው ደግሞ በአካባቢው ተከሰቶ የነበረውን ግጭት ምክኒያት በማድረግ በግብርና ምርቶችና በሸቀጥ ምርቶች ላይ የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ተደርጓል ይላሉ፡፡

የጤፍ ዋጋ በኪሎ 65 ብር ይሸጥ የነበረው አሁን ወደ 110 ብር አሻቅቧል፡፡

" በእያንዳንዱ የሸቀጥ ምርቶችም ላይም በተመሳሳይ የሽያጭ ዋጋቸው እየጨመረ ነው፡፡ ነጋዴዎች ያላግባብ ምርት ያከማቻሉ፡፡ ያላግባብ ዋጋ ይጨምራሉ፡፡ ነዋሪዎች ግጭት ይነሳል በሚል ስጋት እህል እየገዙ ያከማቻሉ፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ የዕለት ከዕለት ኑሮን መግፋት አስቸጋሪ ሆኖብኛል " ሲሉ አስተያየት ሰጭው ይናገራሉ፡፡

እየተደረገ ያለው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ተገቢ ባለመሆኑ የሚመለከተው አካል ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ ከሰሞኑን በነበረ አንድ መድረክ ላይ ፤ " በከተማዋ በኢንዱስትሪና በግብርና ምርቶች ላይ ያላግባብ የዋጋ ጭማሪ ተደርጓል፡፡ ይህ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ነዋሪዎችና የመንግሰት ሰራተኞችን አስመርሯል፡፡ በቀጣይ ችግሩን ለመፍታት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በትኩረት ይሰራል " ብለዋል፡፡

" የከተማ አስተዳደሩ ለዳሽን የሸማቾች ህብረት ስራ ዩኔን 20 ሚሊየን ብር ያለ ወለድ ብድር ሰጥቶ በመሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት የግብርና ምርቶችን የማሰራጨት ስራ እየተሰራ ነው " ያሉት ከንቲባው በቀጣይ ለመሰረታዊ የሸማቾች ህብረት ሰራ ማህበራት የሚደረገው ያለ ወለድ የገንዘብ ብድር ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ፤ የማህበራትን አቅም የማሳደግ ስራም በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል።

ያለ አግባብ ምርት በሚያከማቹ ግለሰቦች ላይም ክትትልና ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል፡፡     

መረጃውን የጎንደር የቲክቫህ-ኢትዮጵያ የቤተሰብ አባል ነው የላከው።

@tikvahethiopia
#ጎንደር

° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” - የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች

° “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ 


በአማራ ክልል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች፣ የውሃ ችግር እንደፈተናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የከተማው ነዋሪዎች በሰጡት ቃል፣ “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም። በአፋጣኝ መፍትሄ እንሻለን ” ብለዋል።

በከተማው የውሃ አቅርቦት እንደሌለ፣ በተለይ ህፃናት የውሃ ጥሙን መቋቋም እንዳልቻሉ፣ ሰው የክረምት ውሃ ለመጠጣት መገደዱን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል። 

ከዚህ ባለፈ ነዋሪዎች የጉርጓድ ውሃ በሰልፍ የመጠቀም ደረጃ እንደደረሱ አመልክተዋል።

ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አያል ፤ “ እውነት ነው። እንዲያውም ማህበረሰቡ ታጋሽ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ አሁን ዝናብ ስለዘነበ ትንሽ ይቀንሳል እንጂ በአንድ ወር ነው ሰው ውሃ ሲያገኝ የነበረው። ግድቡ ሙሉ ለሙሉ ቆሞ ነበር። አሁን ትንሽ ውሃ ስለያዘ ምርት ስለጀመርን አሁን ወደ 25 ቀን እየወረደ ነው ” ብለዋል።

የኢንተርን ሀኪሞቹን ቅሬታ በተመለከተ፣ “ ሆስፒታል ላይ ግን 24 ሰዓት ነው የምንሰጠው። መብራትና አጠቃላይ ምርት ቆሞ ካልሆነ አይቋረጥም ” ነው ያሉት።

“ የማህበረቡ ቅሬታ ግን እውነቱን ለመናገር ከቅሬታ ባለፈ ሌላ ነገር ቢሉም አይፈረድባቸውም ትክክል ናቸው ” ያሉት አቶ ወርቅነህ፣ “ እንደዚህ ትዕግስተኛ የሆነ ማህበረሰብ የለም ” ሲሉ ተናግረዋል።

ችግሩ ከቆዬ ለምን በወቅቱ መፍትሄ እንዳልተቸረው ሲያስረዱም፣ “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል። እንደዚህ አይነት ቻሌንጆች አሉብን ” ብለዋል።

ችግሩን ለመቀረፍ የገጠማችሁ ዋናው ችግር ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄ የፋይናንስ ችግር እንዳለባቸው ገልጸው፣ ምን ያህል በጀት እንደሚያስፈልግ ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

“ ችግሩን መነሻ ተደርጎ የአጭር፣ የአስቸኳይ፣  የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜያት ተብሎ ስራዎች እየተሰሩ ነው። አንዳንዶቹን ቶሎ እናጠናቅቃቸዋለን ” ብለዋል።

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚበጀውን በተመለከተ፣ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበው፣ ማህበረሰቡ ላሳየው ታጋሽነት ምስጋና አቅርበዋል። 

ለነዋሪዎቹ ከሚያስፈልገው የውሃ መጠን እየቀረበ ያለው ምን ያህሉ እንደሆነ፣ ምን ያህል ጉድጓድ እየተቆፈረ እንደሆነ፣ ችግሩን በተጨባጭ እስከ መቼ ለመቅረፍ እንደታሰበ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ  ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia