#ጎንደር
ከቀናት በኃላ ለሚከበረው የጥምቅት በዓል እንግዶች ከወዲሁ ወደ ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ መግባት መጀመራቸው ተሰምቷል።
የጎንደር ከተማ እና አካባቢው ሆቴሎች፣ ሎጂዎችና ሪዞርቶች ማኅበር ፤ ላለፉት ሁለት ዓመታት በኮረና ቫይረስና በጦርነት ምክንያት ተቀዛቅዞ የነበረው የቱሪዝም እንቅስቃሴ አሁን ላይ መልሶ እየተነቃቃ መሆኑን አመልክቷል።
ጎንደር እንግዶቿን በምቾት ተቀብላ ለማስተናገድ ሆቴሎቿ በቂ ዝግጅት እንዳደረጉም ተገልጿል።
ካለው ሀገራዊ የሰላም ሁኔታ ጋር ተያይዞ ለዘንድሮው ጥምቀት በዓል ወደ ጎንደር የሚገባው እንግዳ ቁጥር ከፍተኛ እንደሆነ ይገመታል።
ይህ ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን የማረፊያ እጥረት ለመቅረፍ ታሳቢ ያደረጉ የመፍትሔ ተግባራትን በከተማው ሆቴሌች እየተሰራ ስለመሆኑ ተገልጿል።
በሆቴሎች ደረጃቸውን የጠበቁ ተጨማሪ የድንኳን መጠለያ አገልግሎት ለመስጠት እንደታሰበ ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia