TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከ224 ሚሊዮን በላይ!

በዛሬው ዕለት በአገር አቀፍ ደረጃ 200 ሚሊዮን የዛፍ ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ዕቅድ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት በፊት መሳካቱን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በመረጃው መሰረት እስከተጠቀሰው ሰዓት ድረስ ከ205 ሚሊዮን በላይ፤ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ደግሞ ከ224 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡

Via #etv
"በኃይልና በጉልበት #በአመፅና #በሁከት ሰላምን ብንፈልገውም አናገኘውም"- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
.
.
በዛሬው ዕለት በወላይታ ሶዶ በመገኘት የዛፍ ችግኞችን የተከሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በከተማይቱ ስታዲየም ለተሰበሰበ በርካታ ህዝብ ንግግር አድርገዋል።

“በፍትሕና በምህረት አውድ ውለን ልናድር ካልሆነ በቀር በኃይልና በጉልበት በአመፅና በሁከት ሰላምን ብንፈልገውም አናገኘውም” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው።
“በጦርነትና ግጭት ውስጥ ስንመላለስ የምንቀማው ክብር ሕይወታችንን፣ አካላችንን፣ በድካም ያፈራነውን ሀብትና ንብረት ብቻ ሳይሆን ታላቁን የሕሊና ሰላማችንንም ነው የምናጣው” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፡፡

Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከወላይታ ሶዶና አካባቢዋ ነዋሪዎች ጋር እየተወያዩ ነው። #PMO
“በፍትሕና በምህረት አውድ ውለን ልናድር ካልሆነ በቀር በኃይልና በጉልበት በአመፅና በሁከት ሰላምን ብንፈልገውም አናገኘውም::” - ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በወላይታ ሶዶ ታዲየም ባደረጉት ንግግር

#PMOEthiopia
“በጦርነትና ግጭት ውስጥ ስንመላለስ የምንቀማው ክብር ሕይወታችንን: አካላችንን: በድካም ያፈራነውን ሀብትና ንብረት ብቻ ሳይሆን ታላቁን የሕሊና ሰላማችንንም ነው የምናጣው::” - ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ

#PMOEthiopia
#ጎንደር

የኢፌዴሪ ኘሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በጎንደር ከተማ የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶችን ጎበኙ። ፕሬዘዳንቷ የፋሲል ግንብን፣ የደብረ ብርሃን ስላሴ ቤተክርስቲያን አና ጥምቀተ ባህሩን ጎብኝተዋል። በተጨማሪም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህሙማን የተመላላሽ ህክምና አዲሱን የእናቶች እና ህፃናት ማዕከልን ጎብኝተዋል። በጎብኝቱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይ ወደሃዋሳ ያቀናሉ...

በሶዶ የደኢሕዴን አመራሮች ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ፣ ዶ/ር ጌታሁን ጋረደውና የዎላይታ ዞን አስተዳዳሪ ዳጋቶ ኩምቤ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ነበሩ። ዶ/ር አቢይ የደኢሕዴንና የደቡብ ክልል አመራሮች ከሐሙስ ጀምሮ ወደ ተሰበሰቡበት ሐዋሳ ያቀናሉ ተብሏል።

Via Eshet Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ክብረወሰን ሰበረች!

በአለም አቀፍ ደረጃ በህንድ ተይዞ የነበረው 66 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር የመትከል ክብረ ወሰን ዛሬ ኢትዮጵያ ከ234ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በሰፊ ቁጥር መስበሯ ይፋ ሆኗል።

ቢቢሲ በድረገጹ እንዳስነበበው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ በአገር አቀፍ ደረጃ በርሃማነትን ለመቀነስ ያለመ አካሄድ መሆኑን ገልጾ፤ 1 መቶ ሚሊዮን ህዝብ በነፍስ ወከፍ ቢያንሰ ሁለት ይተክላል በሚል የታሳቢ ቢሆንም ሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤቶች ስራቸውን እዚያው በማድረግ እየተከሉ መሆናቸውን ጠቅሷል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/200M-07-29

ፎቶ፦ ከትምህርት ሚኒስቴር/TIKVAH-ETH/
#አረንጓዴ_አሻራ በሀገር ደረጃ እስካሁን በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ቀን 232 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ይህንን ያስታወቁት በወላይታ ሶዶ ከተማ ከአካባቢው የህብረተስብ ክፍሎች ጋር እየተወያዩ ባሉበት ወቅት ነው።

#አሁን በደረሰን መረጃ በማለት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ከተተከሉት ችግኞች ውስጥ በኦሮሚያ 132 ሚሊዮን ፣ በደቡብ 45 ሚሊዮን፣ በትግራይ ስምንት ሚሊዮን 400ሺህ አማራ 38ሚሊዮን እና አዲስ አባባ ከሶስት ሚሊዮን በላይ የተከናወኑ ይገኙበታል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ዛሬ ጥዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ ለመትከል የታቀደው 200 ሚሊዮን ቢሆንም እስካሁን የተከናወነው ከዚህ በላይ መድረሱን ነው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ ለማወቅ የተቻለው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረንጓዴ_አሻራ #ከፍተኛ_ጥንቃቄ_ይደረግ

ፌስታሉን ካልሰበሰብነዉና ካላነሳነዉ ሌላ ዘመቻ ያስፈልገናል 200 ሚሊዮን ፌስታል ለመልቀም ~ የሚተክል ያስተዉል፤ ጉዳዩ ጥንቃቄ ያሻዋል!!

#ሼር #share

Via #ዝንቅ
ፎቶ: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምን ያህል ችግኝ ተተከለ?

√ኦሮሚያ 132 ሚሊዮን
√አማራ 38 ሚሊዮን
√ደቡብ 45 ሚሊዮን
√ትግራይ 8 ሚሊዮን 400 ሺህ
√አዲስ አባባ ከ3 ሚሊዮን በላይ

ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በወላይታ ሶዶ እያደረጉት ባለው ስብሰባ ደርሷቸው የገለፁት ነው። #PMO
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#መግለጫ_ይሰጣል

በዛሬው ብሔራዊ የአረንጓዴ አሻራ ዕለት በአገር አቀፍ ደረጃ በተተከለው የዛፍ ችግኝ መጠን ላይ በደቂቃዎች ውስጥ ይፋዊ መግለጫ እንደሚሰጥ የዘመቻው ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ያሰባሰበውን ዳታ በማጣራትና በማደራጀት ላይ መሆኑን ኮሚቴው ጨምሮ ገልጿል፡፡

Via #ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሶዴፓ

የሶማሌ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ «ከአጋርነት ወደ ሀገራዊ ፓርቲ የሚያሸጋግረውን» የኢሕአዴግ ጥናት ገምገሞ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል። የማዕከላዊ፣ የክትትልና ኦዲት ኮሚቴዎችና አባላቱ ውይይት አድርገው የሚጨመርና የሚቀነስ ይለያሉ ብሏል።

Via #Eshet_Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
353,633,660 ችግኝ ተተክሏል!

#በአረንጓዴ_አሻራ ቀን 353 ሚሊየን 633 ሺህ 660 ችግኝ ተተከለ። ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ በእለቱ የተተከለው ችግኝ ከእቅድ በላይ መሆኑ ተጠቅሷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"መረጃው ትክክል አይደለም"👆

በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት የአምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሹመት ደብዳቤ እስካሁን በኤርትራ መንግሥት ተቀባይነት አላገኝም በሚል ወጣው መረጃ ትክክል አይደለም ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተባብሏል።

ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ከአንድ ዓመት በፊት በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት ሬድዋን ሁሴን የሹመት ደብዳቤያቸው በኤርትራ መንግሥት ተቀባይነትን አላገኝም የሚለው ዜና በስፋት መነጋገሪያ ነበር።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/RD-07-29
#አረንጓዴ_አሻራ

23 ሚሊዮን የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን በዛሬው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ላይ አሻራቸውን አሳርፈዋል። የችግኝ ተከላው አስተባባሪ ኮሚቴ ማምሻውን በሰጠው መግለጫ በተከላው 23 ሚሊዮን የሚገመት የተለያየ የህብረተሰብ ክፍል ተሳትፏል ብሏል። በዛሬው ዕለትም ከ353 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ችግኝ መተከሉን አስተባባሪ ኮሚቴው ገልጿል።

ዕለቱ ህዝቡ የመሪውን ጥሪ ወደ ተግባር ለመቀየር ቀና አመለካከት እንዳለው ያሳየበት መሆኑም ነው በመግለጫው የተነገረው። የችግኝ ተከላው ከልጅ እስከ አዋቂ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍልና የውጭ አገራት ኤምባሲ ሰራተኞች ጭምር የተሳተፉበት ነው።

በእያንዳንዱ የችግኝ ተከላ ቦታ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ መደረጉም ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እንዲተከል እገዛ ማድረጉ ተገልጿል። ዝናብ፣ ጭቃና የቦታ ርቀት እንዲሁም የችግኝ እጥረት በዛሬው ዕለት ያጋጠሙ ችግሮች ሲሆኑ በአጭር ጊዜ ለመፍታት በተወሰደ መፍትሔ ከታሰበው በላይ ማሳካት ተችሏል ነው የተባለው።

Via #ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"እኛም ችግኞች ነን በእውነትና ፍቅር ላይ ትከሉን!" #ማርሲል

ፎቶ: TIKVAH-ETH/#Maste/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረንጓዴ_አሻራ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትላንትናው ዕለት የአረንጓዴ አሻራ ቀን የተመዘገበውን ስኬት አስመልክተው ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ኅብረተሰቡ በዕለቱ ለመከወን የተያዘውን እቅድ በማለፍ ላስገኘው አመርቂ ውጤት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማም የመዲናዋ ነዋሪዎች በትላንትናው ዕለት የአረንጓዴ አሻራ እለት ላበረከቱት ጉልህ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ወላይታ_ሶዶ

የወላይታ ህዝብ ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ አንድነትና ሰላም የከፈለውን መስዋእትነት አሁንም ታላቋን ኢትዮጵያ ለመገንባት ለተጀመረው ጥረት ሊጠቀምበት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ አሳሰቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ከወላይታ ሶዶ ነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ በከተማው ስታዲየም ተገኝቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደማቅ አቀባበል አድርጓል። በዚሁ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የወላይታ ህዝብ የአገሩን ዳር ድንበር በማስጠበቅ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው ብለዋል። ”ዛሬ እኔ እዚህ የተገኘሁት ሰኔ 16 ቀን በአዲስ አበባ በተሞከረው ጥቃት እኔን ለማዳን ሲል ራሱን በሰዋው ዮሴፍ አያሌው ስም ነው” በማለት ገልፀዋል።

ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለከፍተኛ መንግሥት ሹሞች የተመደቡ 3 ተሸከርካሪዎች ሃላፊዎቹ ሥራ ከለቀቁ በኋላ ለመንግሥት እንዳልተመለሱ ሸገር የፌደራል ዋና ኦዲተርን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ 14 ተሽከርካሪዎች ደሞ ከሊብሬያቸው ውጭ መኪኖቹ በአካል በመስሪያ ቤቶቹ አልተገኙም፡፡ በተለያዩ መንግሥት መስሪያ ቤቶች ከ370 በላይ ተሸከርካሪዎች ያለ ሥራ ተበላሽተው እንደቆሙም ደርሸበታለሁ ብሏል፡፡ ያልተመለሱና የጠፉ መኪኖችን አስመልሰው ሪፖርት እንዲያደርጉለትም መስሪያ ቤቶችን አዟል፡፡

Via ሸገር 102.1/wazema
ፎቶ: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia