TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከቆሼ...

"ፀግሽ ረጲ ቆሻሻ ማከማቻ በተለምዶው "ቆሼ" የሚባለው ከእንደገና ፈርሷል። የእሳትና ድንገተኛ አደጋም ቦታው ይገኛል። በአሁን ሰዓት የፈረሰውን የሚያነሳ እስካቫተር እየተጠበቀ ነው። የጉዳቱ መጠን ገና አልታወቀም።" ሳሚ ከአ/አ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሰበር_ዜና በቆሼ መደርመስ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ፡፡ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዳግም በተከሰተ የቆሻሻ መደርመስ አደጋ እስካሁን የአንድ ሰው አስክሬን መገኝቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳት እና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለአሀዱ ሬዲዮ አስታውቋል፡፡

Via Ahadu Radio
ፎቶ ፦ ሳሚ/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክሱም...

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከአክሱም ከተማ ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል። ነዋሪዎቹ ጠ/ሚሩ ጥያቄያቸውን ተቀብለው ሐውልቱን በማደስ ዙሪያ ለመነጋገር መምጣታቸውን አድንቀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ጠ/ሚሩ በበጀት ምደባ፣ በውኃ እጥረት፣ በመሠረተ ልማት ጥያቄዎችና በሰላምና ጸጥታ ዙሪያ ከነዋሪዎቹ ጋር ተወያይተዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ረጲ አካባቢ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በዛሬው ዕለት በደረሰ የቆሻሻ መደርመስ አደጋ የአንድ ሰው ህይዎት ማለፉ ተገለፀ።

አደጋውን ተከትሎ በአካባቢው በተደረገ ቁፋሮ አንድ የ70 ዓመት አዛውንት በህይወት ማውጣት ቢቻልም አለርት ሆስፒታል ከደረሱ በኋላ ህይወታቸው ማለፉ ተገልጿል።

አደጋው የደረሰው ቆሻሻ ከተጠራቀመበት አካባቢ ላይ ከተሰሩ የፕላስቲክ ቤቶች እና መንገድ ዳር በመሆኑ እስካሁን ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ቁጥር ማወቅ አልተቻለም።

አሁን ላይም የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቆሻሻው በተደረመሰበት አካባቢ የሰው ህይወት ለማዳን በኤክስካቫተር የታገዘ ቁፋሮ እያካሄዱ ይገኛሉ።

በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ረጲ አካባቢ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከሁለት ዓመት በፊት በደረሰ ተመሳሳይ አደጋ ከ100 በላይ ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።

Via #fbc
Photo: TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከASTU...

"ፀግሽ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር የተማሩ ወጣቶችን በመስኖ ልማት ለማሰማራት ከኦሮሚያ ክልል ለተውጣጡ የተማሩ ወጣቶች በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።" #ፋንታሁን

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር ማሊ እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙት በሃገሪቱ ዶጎን የሚባሉ የጎሳ አባላት መኖሪያ በሆነች መንደር በተፈጸመ ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ ተገድለዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በመካከለኛ ማሊ ሶብሌ ኮው በምትባል አንስተኛ መንደር ውስጥ መሆኑን 'አርኤፍአይ' የተሰኘው የፈረንሳይ የዜና ወኪል ዘግቧል።

የአከባቢው ባለስልጣናት እንደሚሉት ከሆነ ደግሞ የሟቾች አስክሬን እንዲቃጠል ተደርጓል። ተጨማሪ የሟቾች እስክሬን እየተፈለገ መሆኑን የአከባቢው ባለስልጣናት ጨምረው ተናግረዋል።

ከቅርብ ወራት ወዲህ በማሊ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እየተበራከቱ መጥተዋል። ከዚህ ቀደም የነበሩት ጥቃቶች ብሄረ ተኮር አልያም በጽንፈኛ ቡድኖች የሚፈጸሙ ናቸው።

በእዚሁ አከባቢ የዶንጎ ጎሳ አባላት በሆኑ አዳኞች እና የፉላኒ ጎሳ አርብቶ አደሮች መካከል ግጭት የተለመደ ነው።

ከሶስት ወራት በፊት 130 የሚሆኑ የፉላኒ ጎሳ አባላት የዶንጎ አዳኞችን ልብስ በለበሱ ሰዎች በአንዲት አነስተኛ መንደር ውስጥ ተገድለው ነበር።

በእነዚህ ሁለት ጎሳዎች መካከል ግጭት እየተበራከተ የመጣው ከአራት ዓመታት በፊት ጸንፈኛ እስላማዊ ቡድኖች በቀጠናው መንቀሳቀስ ከጀመሩ ወዲህ ነው።

Via #bbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የፌዴራል ፖሊስ ለነጌታቸው አሰፋ መጥሪያ ሊያደርሳቸው እንዳልቻለ ለፍርድ ቤት አስታወቀ። የፌዴራል ፖሊስ ትግራይ ክልል ለሚገኘው ቅርንጫፉ የፍርድ ቤት ትእዛዙን በፋክስ ቢልክም በመጥሪያው ላይ የተከሳሾቹ የመኖሪያ አድራሻ ባለመጠቀሱ ለማድረስ አለመቻሉን አስታውቋል፡፡

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድቤት 1ኛ የወንጀል ችሎት ግንቦት 16/2011ዓ.ም በነጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ ላይ ሰጥቶ የነበረውን ትዕእዛዝ ውጤት ለመከታተል ነበር ለዛሬ ቀጠሮ የያዘው፡፡

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን ትክክለኛ አድራሻ የያዘ መጥሪያ በድጋሚ ተዘጋጅቶ ለተግባራዊነቱም የትግራይ ክልል ፖሊስ እንዲተባበር የሚያስችል ትእዛዝ እንዲፃፍ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ በፃፈው ማመልከቻ ጠይቋል፡፡
ፍርድ ቤቱም አቃቤ ህግን የተከሳሾቹ አድራሻ ለምን በክስ ማመልከቻው ላይ አልተጠቀሰም በማለት ጠይቋል፡፡

ፌዴራል አቃቤ ህግም ትግራይ ክልል ከማለት ውጪ የተከሳሾችን ትክክለኛ አድራሻ እንደማያውቅ ገልጿል፡፡

ይህን ተከትሎ አቃቤ ህግ ለተከሳሾቹ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው ክሳቸው በሌሉበት እንዲታይ ጠይቋል፡፡

ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ በድጋሚ በትክክለኛ አድራሻ መጥሪያ ይላክልቸው ወይንስ በጋዜጣ ይጠሩ የሚለው ላይ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 12/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡

በተጨማሪም ችሎቱ የአቃቤ ህግ ምስክሮች ማንነታቸው ሳይገለፅ ከመጋረጃ በስተጀርባ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ይደረግልኝ በማለት ባቀረበው አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 12/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update 5ተኛው የህዝብ እና የቤቶች ቆጠራ በአንድ ዓመት ተራዘመ። ዛሬ የተካሄደው 5 ተኛው የህዝብ ተወካዮች እና የፌደሬሽን ምክር ቤት 4ተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ልዩ የጋራ ስብሰባ የህዝብ እና ቤት ቆጠራ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም ወሰኗል። ሁለቱም ምክር ቤቶች ከዚህ ቀደም ቆጠራው ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ወስነው ነበር። ሆኖም ዛሬ የጋራው ምክር ቤት ቆጠራው ከአንድ ዓመት በላይ ላልተወሰነ ጊዜ ይራዘም የሚልና ሰላሙ በመሻሻሉ ለ6 ወር ብቻ ይራዘም በሚሉ የመከራከሪያ ሃሳቦች ላይ ከተነጋገረ በኋላ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም በአብላጫ ድምጽ ተወስኗል።

በስብሰባው ላይ በተካሄደው ውይይት የሰላሙ ሁኔታ መሻሻል ቢያሳይም ቆጠራውን ማካሄድ የሚያስችል አለመሆኑ፣ በርካቶች በተፈናቀሉበት የቆጠራ ሠራተኞችም ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር በማይችሉበት ሁኔታ ቆጠራውን ማካሄድ አግባብ እንዳልሆነ መነሳቱ ተዘግቧል። ውሳኔው በ30 ተቃውሞ እና በ3 ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው ያለፈው።5ተኛው የህዝብ እና የቤቶች ቆጠራ ሲገፋ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን ነው።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኦሮሚያ ክልል መቱ ከተማ በአብዲ ቦሩ የፈተና ማእከል የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆነችው ተማሪ አልማዝ ደረሰ ዛሬ ጠዋት 1፡30 ላይ ከወለደች በኋላ ፈተናዋን እዛው በወለደችበት ሆስፒታል ተፈትናለች፡፡

ተማሪዋ ለፈተናዋ ስትዘጋጅ መቆየቷን በመግለፅ በፈተናው እለት ብትወልድም ፈተናውን መፈተን አለብኝ በማለት ጥያቄ አቅርባለች፡፡

ተማሪዋ ያቀረበችው ጥያቄ በሚመለከተው አካል ተቀባይነት በማግኘቱ አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግላት በማድረግ ልጇን በተገላገለችበት ካርል ሆስፒታል ፈተናዋን ተፈትናለች፡፡

“የወለድኩበትና የፈተናው እለት መገጣጠሙ አስቸጋሪ ቢሆንም ለፈተናው በቂ ዝግጅት በማድረጌ እንዲያልፈኝ አልፈለኩም”ብላለች።

የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት የሚመለከታቸው አካላትም ወጣቷ ወልዳ በተኛችበት መቱ ካርል ሪፈራል ሆስፒታል አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላት እንድፈተን ማድረጋቸው እንዳስደሰታት ተናግራለች።

ወጣቷ በሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎችና ለዚሁ ስራ በተመደቡ የፈተና ጣቢያ ሰራተኞች ድጋፍም በሆስፒታሉ ውስጥ ፈተናዎቹን እየወሰደች ትገኛለች።

ምንጭ፡- የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ኢሕአዴግ-መራሹ መንግሥት የመንግሥት ልማት ድርጅቶችን ለመሸጥ ሕዝባዊ ይሁንታ የለውም ሲል ተቃውሟል፡፡ ንቅናቄው ዛሬ በአዲስ አበባ ጽሕፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት ከሀገር የሸሸውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ አስመልሳለሁ ያሉትን ቃል ሳያከብሩ መንግሥታቸው ሀገሪቱ ያፈራቻቸውን አንጡራ ሃብቶች ለመሸጥ መዘጋጀቱ ፈጽሞ ተቀባይነት እንደሌለው ገልጧል፡፡ ይህ አካሄድ ሌዛ ዙር መንግሥታዊ ዝርፊያ መዘጋጀትነ ነው በማለትም አስጠንቅቋል፡፡ መንግሥት ስር ነቀል የኢኮኖሚ ለውጥ ማድረግ የሚችለው ከቀጣዩ ምርጫ በኋላ እንደሆነም ጠቁሟል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ የተጀመረው የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የመጀመሪያው ቀን መርሀ ግብር በሰላም መጠናቀቁን ለመስማት ተችሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቴሌግራም ተቋርጧል...

#በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ የተለያዩ #ከተሞች የሚገኙ የTIKVAH-ETH አባላት የቴሌግራም አገልግሎት እንደተቋረጠባቸው ገልፀዋል። በምን ምክንያት የቴሌግራም አገልግሎት ሊቋረጥ እንደቻለ ለማጣራት እንሞክራለን።

እንደ አማራጭ የቤተሰባችን አባላት #Psiphon ይህን መተግበሪያ በመጠቀም ቴሌግራምን በቀጥታ መጠቀም ትችላላችሁ!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Telegram በኢትዮጵያ...
/አገልግሎቱ ለተቋረጠባችሁ/

√Settings
√Connection Type ~ socket5
√Host: 192.169.197.146
√Port: 12792

ለTIKVAHETHIOPIA ቤተሰብ አባላት በሙሉ!

Via John
@tsegabwlolde @tikvahethiopia
ጥንቃቄ...

የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሀሰተኛ የፈተና መልሶች እየተሰራጩ በመሆኑ ጥንቃቄ ታደርጉ ዘንድ እንደ TIKVAH-ETH መልእክት ለማስተላለፍ እንወዳለን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከጥዋት ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ የነበረው የኢንተርኔት አገልግሎት #መስራት ጀምሯል! #ETHIOPIA
የ10ኛ ክፍል ፈተና...

የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በጥቁር አንበሳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት የ10ኛ ክፍል ፈተና ሂደትን ጎብኝተዋል። የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና መሰጠት ከጀመረ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።

Via Mayor Office AA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢንተርኔት የተቋረጠው "ለሀገራዊ ጥቅም" ነው...
/ከኤልያስ መሰረት/

ኢንተርኔት ለበርካታ ሰአታት #ተቋርጦ የነበረው "ለሀገራዊ ጥቅም" ሲባል እንደሆነ የኢትዮ ቴሌኮም ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አሳውቀዋል። ይህም እየተሰጠ ካለው ሀገር አቀፍ ፈተና ጋር ይያያዛል ተብሎ ቢገመትም "እኛ ይሄ ነው ማለት አንፈልግም፤ የሚመለከተው አካል ያሳውቃል ብለን እናምናለን" ብለዋል። ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት አረጋግጫለሁ እንዳለው መቋረጡ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተከስቶ ነበር።

Via Ethio NewsFlash/@eliasmeseret/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከታዋቂው ዓለምአቀፍ የፖለቲካ ሳይንስ ሊቅ ዶ/ር ፍራንሲስ ፉኩያማ ጋር ዛሬ ጠዋት በጽ/ቤታቸው ተገናኙ። ሁለቱ ወገኖች ከምክትል ጠ/ሚር ደመቀ መኮንንና ከኢሕአዴግና አጋር ድርጅቶች አመራሮች ጋር በመሆን በጠ/ሚር ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ የዛፍ ችግኞች ተክለዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ህገ ወጥ መድሃኒት አገልግሎት ላይ ከመዋሉ በፊት በቁጥጥር ሥር ውሏል። የኢትዮጵያ የምግብና የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገር እንዲገቡ የተደረጉ መድሃኒቶችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል። መድኒቶቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉትም በሞያሌ ከተማ በአራት የመድሃኒት መደብሮች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ መሆኑ ነው የተገለፀው። ህገ ወጥ መድሃኒቶቹም ከ4 ሚሊየን 214 ሺህ 175 ብር በላይ ዋጋ የተገመተላቸው መሆኑ ተገልጿል።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia