TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በሙከራ ላይየሚገኘው የTIKVAH-ETH የሞባይል መተግበሪያ አሁንም ችግሮችን ለመታት እየተሞከረ ነው።

ተጨማሪ የተስተካከሉ ችግሮች፦

- Android 5 ላይ “Unfortunately TIKVAH-ETH stopped working" የሚለው ችግር ተቀርፏል
- የሚጠቀመው የዳታ መጠን ቀንሷል ስለዚህም ካርድ ፍጆታው በደንብ ቀንሷል
- ፍጥነቱ ጨምሯል
- landscape mode ሲሆን crash አያረግም
- ሌሎችም

ይህ ለህዳር ወር የመጨረሻው update ነው። ቀጣዩ update በታህሳስ የሚለቀቅ ይሆናል።

ማን ኛውም አስተያየት ካለ @tikvahethbot
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ🔝

ክቡር ጠ/ሚር #ዐቢይ_አህመድ ከኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ: ከደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ: ከጊኒው ፕሬዝዳንት አልፋ ኮንዴ እና ከጋናው ፕሬዝዳንት ናና አኩፎ አዶ ጋር ዛሬ በጽ/ቤታቸው ተገናኝተው ተወያዩ። ውይይቱም በአህጉራዊ ጉዳዮችና የጋራ የትብብር አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ በኢትዬጵያ ስላለው የለውጥ ሂደትና ለአህጉሪቱ ስለሚኖረው የልማት አስተዋፅኦ ተወያይተዋል።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ታላቁ ሩጫ‼️

ነገ እሁድ የሚካሄደው ታላቁ ሩጫ በሚያካልላቸው አካባቢዎች የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች የሚጠቀሙባቸው #ተለዋጭ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።

44 ሺህ ሯጮችን የሚያሳትፈው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከነገ በስትያ መነሻና መድረሻውን ስድስት ኪሎ የሰማዕታት ሐውልት አድርጎ ይከናወናል።

ሩጫው ከስድስት ኪሎ አደባባይ ተነስቶ ምኒሊክ ሆስፒታል-ቀበና-እንግሊዝ ኤምባሲ-በሾላ ገበያ ዞሮ በሱመያ መስጊድ-ሲግናል-አቧሬ-ራስ አምባ ሆቴል አድርጎ ወደ አራት ኪሎ በመሄድ ፍጻሜውን ስድስት ኪሎ አደባባይ ያደርጋል።

ይህን ተከትሎም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዚህ አካባቢ የሚያልፉ አሽከርካሪዎች የሚጠቀሟቸውን ተለዋጭ መንገዶች ይፋ አድርጓል።

በዚህ መሰረት ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ወደ ሽሮ ሜዳ ፈረንሳይ ለጋሲዮን የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ከጊዮርጊስ- በአፍንጮ በር-በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በአልአቅሳ መስጊድ ወደ መነን አቅጣጫ መጠቀም ይችላሉ።

ከሽሮ ሜዳና ፈርንሳይ መስመር ተነስተው ወደ ስድስት ኪሎ፣ አራት ኪሎና መስቀል አደባባይ የሚጓዙ ደግሞ በተለዋጭነት በአፍንጮ በር- ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን-ቸርችል ጎዳናን ይጠቀማሉ።

እንዲሁም ከሽሮ ሜዳ ተነስተው ወደ መገናኛና ቦሌ አቅጣጫ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች በአፍንጮ በር-ጊዮርጊስ አድርገው በቸርችል ጎዳና ኢሚግሬሽን-በካሳንቺስ-ኡራኤል ቤተክርስቲያን አድርገው ወደ መገናኛ መጓዝ ይችላሉ ብሏል።

በተጨማሪም ከነገ ህዳር 8 ቀን 2011 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ሩጫው በሚካሄድባቸው መንገዶች ላይ አሸከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ግጭት‼️

በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭት የሟቾች ቁጥር 24 መድረሱ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ በ167 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው አስተዳደር ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭት የሟቾች ቁጥር 24 መድረሱ ተሰምቷል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ በ167 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው አስተዳደር ዛሬ ለDW ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የጸጥታ አካላት ወደ ሥፍራው መግባታቸውን ተከትሎ ግጭቱ #እየተረጋጋ መምጣቱን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች መካከል ባለፈው ረቡዕ ግጭቱ የተቀሰቀሰው በመሬት ይገባኛል በተፈጠረ አለመግባባት ነበር። ግጭቱ የተከሰተበት ቦታ በጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ሰሜን ዲዳ እና ባቶ ፎቶ በተባሉ ሁለት ቀበሌዎች የነበረ ሲሆን በዚህም ምክንያት በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችም መፈናቀላቸውን የዓይን እማኞች ለDW ተናግረዋል።

 በደቡብ ክልል መስቃን ወረዳ መሰል ግጭት ሲከሰት የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ባለፈው መስከረም በደረሰው ግጭት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን እና ንብረት መውደሙ ይታወሳል።

ምንጭ፦ DW አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሲአን‼️

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ/ሲአን ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ለሲዳማ መብት መከበር የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስታወቀ።

በውጭ የሚኖሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት የንቅናቄው አባላት ሀዋሳ ከተማ ሲገቡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በአቀባበሉ ላይ የሲዓን ሊቀመንበር ዶክተር #ሚሊዮን_ቱማቶ እንደተናገሩት ንቅናቄው ዘመን ተሸጋሪ ጭቆና፣የፍትህ እጦትና የአስተዳደር በደሎች የወለዱት ነው።

ከ1970 ጀምሮ የሲዳማ ህዝብ መብት እንዲከበር ንቅናቄው ረጅምና አድካሚ ትግል ማድረጉንም ገልጸዋል።

የተፈጠረውን እድል ገቢራዊ እንዳናደርግ የሚጥሩና የህዝቦችን ጥቅም በመቃወም አንድነትን የሚፈታተኑ የፖሊቲካ ሃይሎችን መታገል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ትላንት የገባውን የልኡካን ቡድን የመሩት ዶክተር በዛብህ በራሳ በበኩላቸው ንቅናቄው በዴሞክራሲ ግንባታ ውስጥ  ሰላማዊ ትግል በማድረግ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።

ከጄኔቫ የመጡት አቶ ደጀኔ ወልደአማኑኤል በፌዴራልና በክልል መንግስት እንዲሁም በአባሎቻቸውና በደጋፊዎቻቸው የደረገላቸው አቀባበል እጅግ እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል።

በፖሊቲካው ዓለም ያለውን ልዩነት በማስወገድ ለሲዳማ የሚታገል አንድ አውራ ፓርቲ እንደሚገነቡና የግለሰብና የቡድን መብቶችን ህዝቡ እንዲረዳ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የክልሉን ርዕስ መስተዳዳር ወክለው የተቀበሏቸው የርዕሰ-መስተዳደሩ አማካሪ አቶ አኒሳ መልኮ እንኳን ወደ ምድራችሁ በደህና መጣችሁ ብለዋቸዋል፡፡

በሀገሪቱ የመጣውን የፖለቲካ ለውጥ ተከትሎ በውጭ ሀገር ሆነው ለዜጎች ነፃነት፣ ክብርና እኩልነት ሲታገሉ የነበሩ ፓርቲዎች ከበርካታ ዓመታት በኋላ እየተመለሱ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

“የሲዳማ አርነት ንቅናቄም በሀገሪቱ የታየውን ለውጥ በመጠቀም ራሱን እንዲያጠናክርና ለሲዳማ አንድነት በመስራት ኢኮኖሚያዊና ፖሊቲካዊ ለውጥ እንዲመጣ በጋራ እንሰራለን” ብለዋል፡፡

ከአውስትራሊያ፣ ከስዊዘርላንድና አሜሪካን የመጡት የንቅናቄው አመራሮች ትላንት ሃዋሳ ሲገቡ ደጋፊዎቻቸው፣ አባሎቻቸው፣ የዞንና የክልል ባለስልጣናት ተገኝተዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ እና አዲስ አበባ!!

ድምፃዊ #ቴዎድሮስ_ካሳሁን በአዲስ አበባ ስታዲየም #በነፃ የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማቅረብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ተሰምቷል። ለአዲስ አበባው ኮንሰርት ምንም አይነት ክፍያ እንደማይቀበል የተነገረ ሲሆን ለሙዚቃው ዝግጅት ከአዘጋጆቹ በተጨማሪ የተወሰነውን ወጪ እራሱ ይሸፍናልም ተብሏል። ህዝቡም ኮንሰርቱን በነፃ እንደሚታደምበት ነው የተገለፀው። ከአዲስ አበባው በአይነቱ የተለየ የሙዚቃ ዝግጅት በተጨማሪ ድምፃዊው #በሀዋሳ ከተማ የሙዚቃ ዝግጅት ለማቅረብ እቅድ እንዳለው ለመስማት ተችሏል። የሙዚቃ ዝግጅቶቹ መቼ ይካሄዳሉ?? የሚለው ግን የታወቀ ነገር የለም።

ምንጭ፦ ኢትዮፒካሊንክ የሬድዮ ዝግጅት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በምዕራብ ወለጋ ለ490 የተለያዩ የህብረተሰብ የቤት መስሪያ ቦታ #መሰጠቱን የዞኑ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ከተሰጣቸው መካከል መምህራንና ሌሎች የመንግስት ሰራተኞች ይገኙበታል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
200,000ለቤተሰባችን አባላት ቁጥር መጨመር ከፍተኛ ስራ እየሰራችሁ የምትገኙ ሁሉ ትልቅ ምስጋና ይገባችኃል።

🔹እኔ የትም ቦታ የTIKVAH-ETH ማስታወቂያን ሳላስነግር እና ግቡልኝ ፤እወቁልኝ ሳልል እናተው ናችሁ ቻናሉን እዚህ ያደረሳችሁት!! ሁላችሁም ትልቅ ክብር ይገባችኃል!!

ምስጋናዬን ተቀበሉኝ!! ምንም ባላደርግላችሁ እንኳን ሁሌም ለናተ ረጅም እድሜና ጤና እመኝላችኃለሁ🙏

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

የአሜሪካ ማዕከላዊ የስለላ ድርጅት (CIA) በእጁ ከገቡት ማስረጃዎች ተነስቶ የጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጂን ግድያ #ያዘዘው አልጋወራሹ መሀመድ ቢን ሳልማን ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረሱ ተዘገበ። ካሾጂ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢስታንቡል ቆንስላ ጽ/ቤት የገባው ከሞቱ አራት ቀን በፊት በኢትዮጵያ የመስቀል በዐል ዕለት ነበር።

ምንጭ፦ አልጀዚራ(በአለምነ ዋሴ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህፃን በናያስ ህክምና ...🙏

ከሳምንት በፊት ከብዙ ውጣ ውረድ በኃላ ህፃን በናያስ በህንድ ሙባይ SRCC የህፃናት ሆስፒታል ደርሶ ቀዶ ጥገና ተደርጎለታል። ህፃን በናያስን ቀዶ ጥገና ያደረገው ዶክተር ፕራዲፕ ካውሺኪ ሁሉም ነገር በስኬት መጠናቀቁን ለህፃን በናያስ አባት መምህር በድሉ ተናግረዋል። ለህፃን በናያስ የህክምና ውጪ ለማገዝ ቻናላችን ሲሞክር ነበር። ዘመቻ በተጀመረ ሁለት እና ሶስት ቀናት 50 ሺ ብር ለማግኘት ተችሏል። (የመምህር በድሉ የስራ ባልደረቦች የሆኑ የአአዩ መምህራን ጨምሮ) ከዚህ በኋላ ያለውን 100 ሺ ብር ገደማ ቤተሰቦቹ በብድር እንዳገኙ ነግረው ኛል።

የህፃን በናያስ አባትም ይህን ብለዋል፦

"ፀግሽ ቢያንስ የኛ ልጅ በምንም ቢሆን ህክምናውን አግኝቷል። ሌሎች እንደዚህ እድል ያላገኙ በጣም ብዙ ህፃናት እንዲያገኙ ለሌሎች ብትጀምር በጣም ደስ ይለናል። እኛ ብድሩን ሰርተን መክፈል አያቅተንም ጤናውን ይስጠን እንጂ። ያላቸውን ሁሉ ለማድርግ እጃቸውን ለዘረጉልን በፀሎትም ከኛ ጋር ለነበሩ ለመላው የኢትዮጽያ ህዝቦችን የከበረ ምስጋናችንን እቅርብልን። እግዜር ይስጥልን።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ጀማል ኻሾግጂ‼️

የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲአይኤ መሐመድ ቢን ሰልማን ከጋዜጠኛ ጀማል ኻሾግጂ ግድያ ጀርባ እጃቸው መኖሩን አረጋገጥኩ ብሏል። አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን ምንጭ አድርጎ የዘገበው ሲ ኤን ኤን አልጋ ወራሽ #መሐመድ_ቢን_ሰልማን በቱርክ የሳዑዲ ኤምባሲ ውስጥ ጋዜጠኛው እንዲገደል ቀጥተኛ ትእዛዝ መስጠታቸውን አጋልጧል። የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሐመድ ቢን ሰልማን «ኻሾግጂ እንደ አደገኛና አክራሪ ኢስላሚስት ነው የማየው» ብለው ለአሜሪካ መናገራቸው በቅርብ መዘገቡ ይታወሳል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ADI 2 በኔ እምነት ጥላችሁ በTsegab Wolde ባዶ አካውንት እንዲከፈት የጠየቃችሁ #ብቻ ይህን ተቀላቀላቀሉ @tikvahaid2 በአሁን ሰዓት ለአንድ የአፋር ሎጊያ ልጅ የእገዛ ስራ እየሰራን ነው።

እናቱን በስልክ ሳወራቸው እንዲህ አሉኝ "ዝም ብሎ ከቤት እየወጣ ስለሚሄድ ልጄን መኪና እንዳይበላብኝ ብዬ አስሬዋለሁ!"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE የትራፊክ አደጋ በሰው ህይወትና አካል ላይ የሚያደርሰውን አደጋ ለመቀነስ ኀብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የፐብሊክ ሰርቪስ ሰራተኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ጥሪ አቅርቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia