TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሶሳ🔝በቤኒሻንጉል ጉመዝ ክልል በአሶሳ ከተማ በክልሉ መስተዳድር ም/ቤት ትላንት በቀን 7/03/2011 ዓ/ም አክቲቪስት #ጃዋር_መሀመድና አቶ #በቀለ_ገርባ ክክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ አሻዲል ሀስን፣ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ከአሶሳ ከተማ እና አካባቢዋ ማሀበረስብ ጋር በምዕራብ ኦሮሚያና በቤኒሻንጉል ጉመዝ ክልል ድንበር አካበቢዎች በሚከሰቱ #ግጭቶች ዙሪያ መፍትሄ በሚያገኘበት ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የአለምገነት ጣርያ አምራች ኩባንያ (Alemgenet Roofing PLC) ባለቤት ጃክሮስ በሚገኘው ቤታቸው እንዲሁም ጎፋ ገብርኤል አካባቢ የሚገኘው የKG ኢንጅነሪንግ ባለቤት ቪ8 መኪና እያሽከረከሩ ቄራ አካባቢ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ምንጮች ጠቁመዋል። አቶ #ካህሳይ የተባሉት የKG ኢንጂነሪንግ ባለቤት ሰሞኑን በመንግስት ሚድያዎች በተላለፈው ዶክመንተሪ ላይ በተነሳው የመርከብ ግዢ እና ሽያጭ ዙርያ ተጠርጥረዋል ተብሏል። አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ "አንድ ቄራ አካባቢ ያለ ግለሰብ" ብለው የጠቀሱት እርሳቸውን ነውም ተብሏል።"

ምንጭ፦ Elias Meseret
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመጀመሪያውን የ3 ወር ስራ ለማስጀመር!!

በሺዎች የሚቆጠሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት የቀረበውን ሀሳብ ወደውታል ያላችውን ስጋትን እና ጥርጣሬን ገልፀዋል። በተለይ ተረጂዎችን በመለይት ውስጥ ጥልቅ ጥናት እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። በዚህ ምንም አያሳስበንም በቂ #ማስረጃ ይዘን ነው ሰው የምንደግፈው። ከመንግስት አካላት ጋር እና ከማዕበረሰቡ ጋር በቅንጅት ይሰራል። እገዛ የተደረገላቸው ሰዎችም ስልክ እና አድራሻቸው ይገለፃል። በአካል ሄዶ መጠየቅ ይቻላል። ተማሪዎች ምልመላም በከፍተኛ ጥንቃቄ ይሰራል። ለተለያዩ የበጎ አድርጎት ድርጅቶችም እገዛ ሲደረግ በግልፅ በይፋ ይገለፃል።

ማሳሰቢያ፦ TIKVAH-ETH የኢትዮጵያዊያን መሰብሰቢያ ቤት ነው። #እንደድርጅት የተቋቋመ አይደለም። በግለሰብ ተነሳሽነት የሚንቀሳቀስ ነው።

በአካውንቱ ዙሪያ የቀረቡት ሀሳቦች፦

የመጀመሪያው እንደ ማህበር እንዲቋቋም እና አካውንት እንዲዘጋጅ ለዚህም ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ተጠቁሟል። አሁን ቤተሰባችን ይህን የሚያደርግበት ደረጃ ላይ አይደለም። በቀጣይ 2 አመት እቅድ ውስጥ የተካተተ ነው ይሄ!! አካውንት እንደ ማዕበር ለማዘጋጀት ብዙ የሚያስፈልጉ ነገሮች እንዳሉ ተጠቁሟል።

ሌላኛው፦ በ5 አባላት ስም እንዲከፈት ስለሰዎቹ ዝርዝር መረጃ እንዲሰጥ እነማን እንደሆኑ አካውንቱ ውስጥ ያለው ገንዘብ በሶስት ሰው ፍቃድ እንዲወጣ ማድረግ!! ለዚህም ሰዎችን መምረጥ የሚል ነው።

የመጨረሻው፦ TSEGAB WOLDE ባዶ አካውንት ተከፍቶ ስራው እንዲጀመርም እንደሀሳብ ቀርቧል። ይህም ለስራ እና ለግል ከምጠቀምበት ውጭ የሆነ እንዲሆን የሚል ሀሳብ ነው። ማንኛው አይነት የገንዘብ እንቅስቃሴን የTIKVAH-ETH ባንክ ቤት ሰራተኞች እንዲከታተሉ እና #ሌብነትም ላይ ስጋት እንዳይኖር እንቅስቃሴውን ሁሉ እየተከታተሉ ለህዝብ እንዲገልፁ የቻናሉ admin እንዲሆኑ እንዲደረግ የሚል ሀሳብም ቀርቧል። አካውንቱ በ15 ቀን ወይም በወር ባዶ እንደሆነ ለህዝብ እንዲታይ! በአካውንቱ ውስጥ በምንም ምክንያት ብር እንዳይኖር...ይህንንም ለህዝብ ማሳየት።

ለዚህም፦ 10 የባንክ ሰራተኞች admin እንዲሆኑ ሃሳብ ቀርቧል።

ሌላው ምንም አይነት ጥርጣሬ እና ስጋት ካለ እገዛው ያለአግባብ ተሰጥቷል፣ ገንዘብ ባክኗል የሚል ሰው በማስረጃ አስደግፎ ይሄን ቁጥር ይዞ 0919 74 36 30 ለፖሊስ እንዲያመለክት እንደሀሳብ ቀርቧል።

በድጋሚ ማሳሰብ የምወደው ነገር፦ #ተቀማጭ የሚባል ገንዘብ የለም። በወር ሁሉም ገንዘብ ወጥቶ ለታለመለት አላማ ይውላል።

🔹የቀን ሪፖርት በተመለከተ፦ በየዕለቱ ያለውን እንቅስቃሴ በቻናሉ ላይ በግለፅ ይገለፃል። ከባንክ የሚላኩትን መረጃዎች ህዝቡ በፎቶው እንዲያየው ይደረጋል።

ይህ እቅድ መነሻ ነው! ሶሻል ሚዲያውን እንዴት ለትልቅ ለወጥ መጠቀም እንደምንችል የምናሳይበት ነው። በጥቂት ጊዜ ውስጥ ደግሞ #ሆስፒታል እና #ትምህርት_ተቋማት በራሳችን ወጪ በመግንባት ለሀገራችን ሰርተን የምናልፍበትን መንገድ የምንጀምርበት ነው።

ሲጠቃለል...

ድምፅ እንድትሰጡ በትህትና እጠይቃለሁ፦

❤️TIKVAH-AID በእቅዱ መሰረት ከ2 ዐመት በኋላ እንደማህበር ከተቋቋመ በኃላ ወደ ስራ እንግባ!

💚5 ሰዎች ከቻናሉ ተመርጠው አካውንቱ ተከፍቶ የቀኑን ውሎ ከባንክ በምናገኘው መረጃ እየተከታተልን ሰዎችን እንርዳ!!

💜ባዶ አካውንት ተዘጋጅቶ ሁሉም በየቀኑ አካውንት ውስጥ የገባውን ገንዘብ እንዲያየው ይደረግ። በ15 ቀን የገባው ገንዘብ ወጥቶ እንዲረዳበት። ገንዘብ ሲወጣ እና ሲገባ በየሰዓቱ በፎቶ ይገለፅ!!

እኛ ጋር የተሻለ ሀሳብ አለ የምትሉ ደግሞ በ0919 74 36 30 ወይም @tsegabwolde አናግሩኝ!

እናተው ወስኑ እና ወደእንቅስቃሴ መግባት እንችላለን! ብዙሀኑ ጥርጣሬ ካደረበት ደግሞ ስራው አይሰራም ይቆማል። ሀሳቡ ተቀባይነት ካጣ አብረን መስራት የምንችል ሰዎች ብቻ ተነጋግረን መጠነኛ ድጋፍ የማድረግ ስራ ላይ እንሰማራለን።

〽️ እንደከዚህ ቀደሙ የታመሙ ሰዎችን የምንረዳበት ስራ ግን አይቋረጥም። ይቀጥላል!!

🔹ከምንም በላይ የባንክ ቤት ሰራተኞች ሌብነትን በማጋለጥ በዚህ ስራ ውስጥ ይሳተፋሉ ብዬ ጠብቃለሁ። በፌስቡክ እና በቴሌግራም 1 ብር እንኳን ከባከነ ለህዝብ ያሳውቃሉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እጅግ በጣም ለድምፃችሁ እናመሰግናለን!

በብዙሀኑ ድምፅ❤️መሰረት ስራዎች ከ2 ዐመት በኃላ እንዲሰሩ ተጠይቋል። ይሄን ሀሳብ ስላቀረባችሁ እናመሰግናለን። ከሁለት አመት በኃላ ለመሳተፍ ተዘጋጁ!

💜ይህን ምልክት ተጭናችሁ ድምፅ የሰጣችሁ #ብቻ ወደዚህ ግቡ @tikvahaid2 በዚህ በኩል ሌሎች ስራዎችን እንሰራለን። ይህም በተለይ ተቸግረው የሚማሩትን ተማሪዎች እናስተምርበታለን!

ለሰዎች ህክምና ገንዘብ የማሰበቡ ቅስቀሳ ግን ይቀጥላል!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሶሳ🔝

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከምዕራብ ኢትዮጵያ ተጎራባች ክልሎች ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትና #የሰላም_ኮንፈረንስ በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በኮንፈረንሱ ላይ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአማራ ከኦሮሚያ ከጋምቤላ ክልሎች የተወከሉ የህዝብ ወኪሎችና አመራሮች እንዲሁም የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል።

የኮንፈረንሱ አላማም የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ከመከበሩ በፊት የአገራችን ሰላምና መረጋጋት ችግር በሚፈታ እና ለዘመናት ስር ሰዶ የቆየው በመከባበር በመደጋገፍ እና በመቻቻል የተመሰረተውን የህዝቦች ግንኙነትና ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ ነው።

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport ኢንተርናሽናል ዳኛ ሊድያ ታፈሰ የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታን ትመራለች። ነገ በሚጀመረው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ ሀገር ጋና ከአልጄሪያ የሚያደርጉትን የመክፈቻ ጨዋታ የኢትዮጵያዊቷ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በዋና ዳኝነት ጨዋታውን ትመራለች። በ2016 ካሜሮን ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ የመክፈቻ ጨዋታውን መምራቷ የሚታወስ ነው።

ምንጭ፦ካፍ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቀለ🔝

"ሠላም ፀግሽ ዛሬ በመቀለ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በቻሪቲ ክበብ አማካኘነት ለተቸገሩ ወገኖች የሚውል አልባሳት ተሰብስቧል እንዲሁም በተማሪው አማካኝነትም ታጥበዋል እነዚህም መልካም ተግባራት ቀጣይነት እንዲኖራቸው የሁሉን ድጋፋ እንሻለን! ሁላችንም ስንተሳሰብ እንጂ ስንቀማማ አያምርብንም! @henossol"

@tsgabwolde @tikvahethiopia