TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች...
/#ሼር/#Share/

"አጠገባችሁ ያለው ተማሪ ወንድማችሁ እንደናንተው ከምስኪን ቤተሰብ የተገኘ ፣ ጭራሮ ለቅማ፣ ጠላ ሽጣ፣ ግፋ ቢል በጉሊት ችርቻሮ ወይም በመንግሥት ስራ ከእጅ ወደአፍ ኑሮ የምትኖር የአንተንው እናት የምትመስል እናት/ ሀርሜ አለቺው። እንዳንተው በእርሻ ፣ በመለስተኛ ንግድ ወይም በመንግሥት ስራ የሚተዳደር አባት፣ እንዳንተው ነገ ተመርቀህ ለራስህና ለኔ ተሳልፍልኛለህ ብሎ ተስፋ ያሚጥልበትና የሚያዝንለት ወገን ያለው ወገንህ ነዉ። እናም ማንም ከየትም ሆኖ በሚፈጥርልህ በዉል እንኳ ተለይቶ በማይታወቅ ምክንያት ውንድምህን አታጥቃው። እመነኝ በዩኒቨርሲቲ ዉስጥ ትርፍ አልባ ግጭት ደም ገብረህ፣ ወንድምህን ገድለህ በፀፀት አለንጋ እየተገረፍህ እድሜህን ትማቅቃለህ። አሊያም ራስህ ሰለባ ሆናህ የራስህንና የወገንህን ህልም ተጨልማለህ። ባይሆንስ ምንም ውስጥ ከሌለበት ወንድምህ #ተባልተህ ትርፉ ምንድነው? ይሉቁንስ በዚህ የማይደገመውን የካምፓስ ህይወት አጋጣሚ በጋራ በመሆን #ለሀገራችሁ ችግር መፍትሔ ፈልጉ። እመነኝ አንድ ሆነህ ከቆምህ ከፊትህ ብሩህ ተስፋ አለ!!"

Via ዶክተር ታደሰ ቀነአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ በገዛ ሰራተኞቹ ወሊሶ ላይ የመኪና አደጋ እንደደረሰ ተድርጎ በሀሰተኛ ዶክመንት 47,000 ብር የካሳ ክፍያ ተወስዶብኛል አለ። 7 ሰራተኞቹም የፖሊስ ምርመራ ላይ ናቸው።

Via Tesfaye Getnet/ካፒታል ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወሻ!

የ10ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ ሰኔ 3 ቀን 2011ዓ.ም በመላው ኢትዮጵያ ይጀመራል፤ ተማሪዎች መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

በፈተና ጊዜ የፈተና #ትዕዛዛትን በማክበር ከጭንቀት ራስን ነፃ ማድረግ እንደሚቻል የሥነ-ልቦና ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡ በፈተና ጊዜ የፈተና ሕግና ደንብን መጣስ በፈታኙ ‹‹ታየሁ-አልታየሁ›› የሚል ጭንቀት ውስጥ ስለሚከትት የፈታኞችን ትዕዛዝ ማክበር በነፃ አዕምሮ ጥያቄችን ለመመለስ ያስችላል፡፡

ፈተና መምህራን ተማሪ ለመጣል የሚያዘጋጁት መሰናክል ሳይሆን አንድ ተማሪ ያለበትን የክፍል ደረጃ አጠናቅቆ ለቀጣዩ እርከን ብቁ መሆን አለመሆኑ የሚመዘንበት ነው፡፡ ስለሆነም በክፍል ደረጃው አንድ በመካከለኛ ደረጃ የሚገኝ ተማሪ ሊመልሳቸው የሚችሉና ከአጠቃላይ የትምህርቱ ዓለማ የሚመዘዙ የፈተና ጥያቄዎች ስለሚዘጋጁ ተማሪዎች ሊሰጉ አይገባም፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጁ የፈተና ጥያቄዎች በክፍል መምህራን ከሚዘጋጁ ጥያቄዎች የተሻለ ለብዙዎቹ ተማሪዎች የሚቀልሉ እንደሆኑ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ ምክንያቱም በብዙ ጥንቃቄና በበርካታ ሰዎች የሚዘጋጁና የሚገመገሙ በመሆናቸው ሀገር አቀፍ ፈተናዎች የሰዋስውና የፊደል ግድፈታቸው የቀነሰ፣ አብዛኞቹ ተማሪዎች ሊረዷቸው በሚችሉ ቋንቋዎች የሚዘጋጁ፣ ከጥቅል የትምህርቶቹ ዓላማ አንጻር የሚዘጋጁ በመሆናቸው ነው፡፡

ተማሪዎች ተረጋግተው ለመሥራት እንዲችሉ ወደ ትምህርት ቤት ለፈተና ሲሄዱ በአግባቡ የተቀረጹ እርሳሶች፣ መቅረጫ፣ መታወቂያ፣ የፈተና መግቢያ (አድሚሽን) ካርድ ይዘውና የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ለብሰው ስለሆነ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች አሟልተው መሆን አለበት፡፡

Via አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱዳን ባለስልጣናት የተቃዋሚ መሪዎችን እያሰሩ ነው...

በትናንትናው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ ሱዳን ካርቱም ደርሰው ከተመለሱ በኋላ የሱዳን የደህንነት ኃይሎች ተቃዋሚዎችን ማሰር መጀመራቸው ተሰማ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሱዳን አቅንተው የነበረው ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለውን የወታደራዊ ምክር ቤት ባለስልጣናትንና ተቃዋሚዎችን ለማሸማገል ነበር።

ነገር ግን የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪው መሐመድ ኢስማት አርብ እለት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ከተገናኙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰምቷል።

ዛሬ ማለዳም ኢስማኤል ጃላብ እና ቃል አቀባዩ ሙባረክ አርዶል የተሰኙ የተቃዋሚ ቡድን መሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።

ተቃዋሚዎቹ የበርካቶች ደም ከፈሰሰ በኋላ የሚደረጉ ውይይቶችን ስለማያስተማምኑ አንቀበልም ማለታቸው ተሰምቷል።

የወታደራዊ ምክር ቤት የሲቪል አስተዳደር ለመመስረት ቢስማማም ነገር ግን ተቃዋሚዎች የጊዜ ገደቡ ላይ ባለመስማማታቸውና በአድማው በመቀጠላቸው ግጭቶች ተፈትረው ከመቶ በላይ ተቃዋሚ ሰልፈኞች በፀጥታ ኃይሉ ተገድለዋል።

Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትናንት ማታ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ ለሊት 8:00 መጥፋቱ ተረጋግጧል። ትናንት ሰኔ 01/2011 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ ነበር እስካሁን ምክንያቱ #ያልታወቀው የእሳት ቃጠሎ የተከሰተው። በግቢው ውስጥ በሁለት ህንፃዎች ላይም ጉዳት አድርሷል። በእሳት ማጥፊያ መኪና እና የልዩ ኃይል እና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ጨምሮ በሰው ኃይል ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ጥረት ተደርጎ ነበር፤ ነገር ግን እሳቱ የህንፃዎቹን የመጨሻ ክፍል ሙሉ በሙሉ ካወደመ በኋላ ሌሊት 8:00 አካባቢ መጥፋቱን ተሰምቷል፡፡
የተቃጠሉት ህንፃዎች የተማሪዎች መኖሪያ ነበሩ። በሰው ህይወትም ሆነ አካል ላይ ጉዳት እንዳልደረሰም ታውቋል።

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአርባ ምንጭ...

"ይሄ ነው እንግዲ የተነሳው እሳት ያደረሰው እልቂት። እሳቱ ከተነሳ ከሁለት ሰዓታት በኋል የደረሰው የከተማው የእሳት አደጋ መከላከያ መኪና በውስጡ ውሃ ይያዝ አይያያዝ ባይታወቅም ከ10 ደቂቃዎች በላይ እሳቱን ለማጥፋት እርዳታ ማድረግ አልቻለም። ይሁን እንጂ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ቦቴዎች እንዲሁም ግዙፍ የሆነው የኤርፖርት የእሳት አደጋ መከላከያ መኪና እሳቱን ለማጥፋት ህይወቱን መሰዋእት ካደረገው ከአባባቢው ወጣቶች በመቀጠል የአንበሳውን ድርሻ ወስዳል።" ፀጋዘአብ ከአርባ ምንጭ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ትላንት ምሽት በአርባ ምንጭ ትልቁ የሲቀላ ገበያ የተነሳው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ታወቀ።

ከምሽቱ 3:40 አካባቢ የጀመረው እሳት ዋናውን የልብስ ተራ ብሎክ ሙሉ ለሙሉ ማውደሙ የታወቀ ሲሆን በዚህም በርካታ የአልባሳት መጋዘኖች፣ መሸጫ ሱቆች እና በሚሊዮን የሚገመት ገንዘብ የፈሰሰባቸው ንብረቶች እንዳልነበር ሆነዋል።

እሳቱ የተነሳው በገበያው የልባሽ ጨርቅ (ሰልባጅ) ተራ ሲሆን አደጋውን ለመቆጣጠር ዘግይቶም ቢሆን መጀመሪያ የደረሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ተሽከርካሪ ሲሆን የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪ ግን በርካታ ንብረቶች ከወደሙ በኋላ በሥፍራው ደርሷል፡፡

ከምሽቱ 5:00 ሰዓት አካባቢ በቁጥጥር ሥር እንደዋለ የተነገረለት የእሳት አደጋው በአርባ ምንጭ የእሳት አደጋ ታሪክ እጅግ አስከፊው ስለመሆኑ ተነግሯል።

የቃጠሎውን መንስዔ በተመለከተ በማን እና እንዴት ተነሳ ለሚለው በውል የታወቀ ነገር አለመኖሩ የተገለፀ ሲሆን መንግሥት በመንስኤው ዙሪያ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ውጤቱን ለህዝብ እንዲያሳውቅ ጥሪ ተላልፏል፡፡

Via #GMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፀጥታ ስጋት የለም" - ፕ/ር ክንደያ ገብረህይወት
.
.
ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ጓደኞቻቸውን እንደ መልካም እድል በመጠቀም ልምድ መውሰድና የባህል ልውውጥ በማድረግ ግንኙነታቸውን ማጠናከርም አለባቸው።
በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፀጥታ ችግር ስጋት አለመኖሩንና የመማር ማስተማር ሂደቱ በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ክንደያ ገብረህይወት ተናገሩ።

ፕ/ር ክንደያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች እየተስተዋሉ ያሉ የፀጥታ መደፍረስ ችግሮች ወደ ዩኒቨርሲቲው እንዳይመጣ ከተለያዩ አደረጃጀቶች ጋር በመሆን እየተሰራ ነው። 

ትናንት በዩኒቨርሲቲው ከተማሪዎች ጋር ውይይት መደረጉን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ሰሞኑን በደብረ ማርቆስና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች በተፈጠረው ችግር በደረሰው ጉዳት ማዘናቸውን ገልፀዋል፤ አግባብ አለመሆኑንና እያንዳንዱ ተማሪ ከእንደዚህ አይነት ድርጊት እንዲቆጠብ መግባባት ላይ ተደርሷል ብለዋል።

የፀጥታ ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን አስቀድመን መለየት ላይ በትኩረት እየሰራን ነው ያሉት ፕ/ር ክንደያ ገብረህይወት ከአገልግሎት መጓደል ጋር በተያያዘ የሚነሱ ቅሬታዎችንም የአገሪቷ አቅም በሚፈቅደው መሰረት ለመፍታት እየሰራን ነውም ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው በምርምር ዘርፎች፣ በቱሪዝም ዘርፉ ከአጎራባች ክልሎች ጋር በጋራ በመስራት፣ በግብርና እና ህክምና እንዲሁም ሌሎች ዘርፎች ዙሪያ ጠንክሮ በመስራት ማህበራዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ ነው ብለዋል ፕሬዚዳንቱ።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የሚያገኟቸውን ጓደኞቻቸውን እንደ መልካም እድል በመጠቀም ልምድ መውሰድና የባህል ልውውጥ በማድረግ ግንኙነታቸውን ማጠናከር ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ፕ/ር ክንደያ ገብረህይወት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Via #EPA
Forwarded from TIKVAH-SPORT
#Breaking ሱክህዴቭ ጉፕታ የተባሉ የህንድ ዜግነት ያላቸዉ ግለሰብ በትላንትናዉ ማታ ተገድለዉ ተገኙ። ግለሰቡ ቢሸፍቱ ከተማ #ተገድለዉ መገኘታቸዉን ለማረጋገጥ ተችሏል። Mr ጉፕታ በቢሸፍቱ የሚገኘዉ የካኖሪያ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ተቀጣሪ ነበሩ።

Via ዳዊት እንደሻው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተጠርጣሪዎች እየታደኑ ነው...

ትናንት ምሽት #በደብረ_ብርሃን_ዩኒቨርስቲ በደረሰው የዕሳት አደጋ በሰው ህይዎት ላይ ጉዳት አለመድረሱን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል። የእሳት አደጋውን #አድርሰዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ #ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ...

በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ጊዚያት አንዳንድ አለመረጋገቶችን ለመፍጠር በተለያዩ አካላት ሲሞከር ቆይቷል፡፡ በዚህ መሰረት በተነሱ የተማሪዎች አለመግባባት የመማር ማስተማሩ ሂደት ከ27/9/2011 ዓ.ም ጀምሮ ተስተጓጉሏል፡፡ ይህን ችግር ለመፍታትም የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት የተለያዩ ጥረቶችን ዕያደረገ ይገኛል፡፡ ከሚመለከታቸው አካላት ጋርም ሰፊ ውይይት በማድረግና በማረጋገት የሰው ህይዎት እንዳይጠፋና አስከፊ ጉዳት እንዳይደርስ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሠራ ይገኛል፡፡ በተለያየ ጊዜ በዩኒቨርሲቲው ጥፋት ለማድረስና መማር ማስተማሩን ለማወክ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ 58 ተማሪዎች ላይም የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ርምጃ ወስዷል፡፡ አለመረጋጋቱን ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱትም ውስን ተማሪዎች ሲሆኑ ከዩኒቨርሲቲው የተባረሩና ዝቅታኛ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች በማስተባበርና በመምራት በስፋት ይገኙበታል፡፡

ተማሪዎችን ለማረጋገት፣ ደህንነታቸውን ለመጠበቅና መማር ማስተማሩን ወደነበረበት ለመመለስም ዩኒቨርሲቲው በየደረጃው ካሉ የዞን፣ የክልልና የፌደራል መስሪያ-ቤቶችና ሀላፊዎች እንዲሁም ከክልሉና ከፌደራል የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ለማስተካከል እየሰራና እያወያየ ባለበት ወቅትም በቀን 1/09/2011 ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ በ 2(ሁለት) የተማሪዎች መኖሪያ ህንፃዎች ላይ የእሳት ቃጠሎ ተነስቷል፡፡ቃጠሎውም የህንፃዎቹን ኮርኒስ በማያያዝ የተጀመረ ሲሆን ከከተማ አስተዳደሩና ከሀበሻ ቢራ ጋር በመሆን የጊቢውና የአካባቢው ማህበረሰብ ባደረገው ከፍተኛ ርብርብ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ተችሏል፡፡ በአደጋው በሰው ሂዎት ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት የሌለ ሲሆን አደጋውን በማድረስ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ እየሰራ ይገኛል፡፡

በመሆኑም የተማሪ ወላጆች ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና የፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ልጆቻችሁን በመምከርና ከጥፋት እንዲታቀቡ በማድረግ እንድታረጋጉና እንዲሁም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ዕየተራገቡ ያሉ አሉባልታዎች በንፁሀን ተማሪዎች ህይዎት ቁማር መጫወት ሲሆን ተራ የግለሰብና የቡድን አጀንዳን የምታራምዱና ድርጊቱን ለማባባስ የምትሞክሩም ከድርጊታቸሁ እንድትቆጠቡ እናሳስባለን፡፡

ዩኒቨርሲቲው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሃያ ዘጠኝ ቢሊዮን ብር ወጪ ይከናወናል የተባለው የአዲስ አበባ ወንዞች ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክት 30 ሺሕ ነዋሪዎችን እንደሚያስነሳ ተገለጸ፡፡ ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ከተማዋን ለሁለት ከፍለው በሚፈሱ ወንዞች ዙሪያ ሰፍረዋል የተባሉትን 30 ሺሕ ነዋሪዎች መልሶ ለማስፈር እንቅስቃሴ መጀመሩን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) የቴክኒክ አማካሪ ወ/ሮ መስከረም ታምሩ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከነገ ጀምሮ ለሚሰጠው #የ10ኛ ክፍል ፈተና የተደረገውን ዝግጅት አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ጥላዬ ጌቴ የሰጡት ማብራሪያ፡-

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በደቡብ ወሎ ዞን ሐይቅ ከተማ ከ600 በላይ ጥይት ከአንድ ክላሽንኮብ ጠብመንጃ ጋር በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር መያዙን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ኮማንደር ጌታቸው ሙላት እንደገለጹት መሳሪያው ከነጥይቱ ሊያዝ የቻለው የህብረተሰቡን ጥቆማ መሰረት በማድረግ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ነው፡፡

በእዚህም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-20584 በሆነ የህዝብ ማመላለሻ አይሱዝ መኪና ውስጥ አንድ ታጣፊ ክላሽ እንኮብ የጦር መሳሪያ፣ 613 የክላሽ እንዲሁም ዘጠኝ የመትረየስ መሳሪያ ጥይቶች ተይዘዋል።

በተጨማሪም ሰባት ህገ ወጥ የሞባይል ስልኮች በፍተሻው መያዛቸውን የገለጹት። ተሽከርካሪው የተያዘው ትናንት ከወረባቦ ወረዳ ተነስቶ ወደ ሐይቅ ከተማ ሊገባ ሲል ቀበሌ 02 ላይ ሲደርስ መሆኑንም ኮማንደር ጌታቸው አመልክተዋል፡፡

እንደእርሳቸው ገለጻ በወንጀሉ የተጠረጠሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳዩ በመጣራት ላይ ሲሆን ሁለቱ መምህር መሆናቸው ታውቋል።

ህብረተሰቡ #ለፖሊስ ላደረሰው #ጥቆማ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ኮማንደሩ በቀጣይም ህገ ወጥነትን በጋራ ለመከላከል ህብረተሰቡ የጀመረውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

Via #OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

"አርቲስት እንቁስላሴ ጎዳና ላይ ወጣ" ተብሎ እየተሰራጨ ያለው ወሬ የሀሰት እንደሆነ ጓደኞቹ ተናግረዋል። አርቲስቱ በአሁን ሰአት አሜሪካን ሀገር እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

Via @eliasmeseret
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በጉራጌ ለ158 ዓመታት ተቋርጦ የነበረው የኦሮሞ ገዳ ስርዓት በድጋሚ ተቋቋመ። #etv

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ማድረግ ያለባቸው 10 ወሳኝ ነገሮች...

ነገ ሰኞ ሰኔ 03/2011 ዓ.ም ሃገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና መስጠት ይጀመራል። ተማሪዎች በፈተናው ወቅት ማድረግ ያለባቸው ቀላል ነገር ግን ወሳኝ አስር ነጥቦች። መልካም ፈተና!

Via #BBC

@tsegbwolde @tikvahethiopia
"ሰላም ፀግሽ! በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የቅ/ጊዮርጊሱ አጥቂ ጌታነህ ከበደ እና የወ/ሪት ቤተልሔም አዳነ የጋብቻ ስነስርዓት በኃይሌ ሪዞርት ጎንደር እየተካሄደ ይገኛል!! መልካም ጋብቻ ለውዱ አጥቂያችን!"

Via #በያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia