TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትናንት ማታ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ ለሊት 8:00 መጥፋቱ ተረጋግጧል። ትናንት ሰኔ 01/2011 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ ነበር እስካሁን ምክንያቱ #ያልታወቀው የእሳት ቃጠሎ የተከሰተው። በግቢው ውስጥ በሁለት ህንፃዎች ላይም ጉዳት አድርሷል። በእሳት ማጥፊያ መኪና እና የልዩ ኃይል እና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ጨምሮ በሰው ኃይል ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ጥረት ተደርጎ ነበር፤ ነገር ግን እሳቱ የህንፃዎቹን የመጨሻ ክፍል ሙሉ በሙሉ ካወደመ በኋላ ሌሊት 8:00 አካባቢ መጥፋቱን ተሰምቷል፡፡
የተቃጠሉት ህንፃዎች የተማሪዎች መኖሪያ ነበሩ። በሰው ህይወትም ሆነ አካል ላይ ጉዳት እንዳልደረሰም ታውቋል።

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia