TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሁን2021

የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ከተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና ከ xHub Addis (የጀማሪ ሥራ ፈጠሪዎች ማበልፀጊያ ማዕከል) ጋር በተለያዩ ዘርፎች የቢዝነስ ሃሳብ ያላቸው ጀማሪዎችን ለማሳደግ #አሁን2021 የውድድር መድረክ የተሳትፎ ጥሪ ቀርቧል።

#አሁን2021የአራት ወራት የስልጠና እና የማበልጸጊያ ፕሮግራም ሲሆን በፍጥነት የማደግ እምቅ አቅም ያላቸው የቢዝነስ ሃሳቦችን በማገዝ በማወዳደርና ለሥራ ማስጀመሪያ የሚሆን ዶላር የመሸለም ዓላማ ያለው ተብሏል።

ይህ ማስታወቂያ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ለ15 ቀናት በ http://xhubaddis.com/jcc/ መመዝገብ ትችላላችሁ።

አመልካቾቸ ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ፦

• ኢትዮጲያዊ ዜግነት ያለው/ያላት
• ኢኖቬቲቭ የቢዝነስ ሀሳብ ያለው/ያላት

ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።

#Share #ሼር

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#ምርጫ2013

አንድ መራጭ ለክልል ምክር ቤት መቀመጫ ምን ያህል እጩዎችን መምረጥ ይችላል?

ለክልል ወይም ለከተማ ም/ቤት መቀመጫ አንድ መራጭ መምረጥ የሚችለው የእጩዎች ብዛት እንደየምርጫ ክልሉ ይለያያል።

አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 1 እጩ፣ እንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 3 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ላይ 9 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 14 እጩዎች ወይም ሌላ ቁጥር ያለው የመቀመጫ ብዛት ሊኖራቸው ይችላል።

ብዛቱ የሚወሰነው የምርጫ ክልሉ በክልል ምክር ቤቱ ባለው የመቀመጫ ቁጥር ብዛት ነው።

በመሆኑም አንድ መራጭ በክልል ምክር ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ መምረጥ የሚችለው የዕጩዎች ብዛት በክልል ምክር ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ከላይ ተፅፎ ይገኛል።

በዚህም መሰረት አስፈጻሚዎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ሲሰጡ ለመራጩ በምርጫ ጣቢያ ውስጥ እስከ ስንት እጩ መምረጥ እንደሚችል ያስረዳሉ።

ሆኖም ግን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች አንድ ዕጩ ብቻ የሚመረጥ ይሆናል። ስለዚህም ከዚህ ቁጥር ገደብ በላይ ምልክት የተደረገባቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ዋጋ አይኖራቸውም።

ስለሆነም ድምፅዎን ሲሰጡ በወይን ጠጁ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወረቀት #አንድ በክልል ምክር ቤት ወረቀት ደግሞ ወረቀቱ ላይ በተጻፈው እና ምርጫ አስፈጻሚው በሚነግርዎ ቁጥር መሰረት መሆኑን አይርሱ። ከተፈቀደው የእጬ ቁጥር በላይ ምልክት አያድርጉ።

#ሼር #Share

(የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ)

@tikvahethiopia
#BREAKING

በሁሉም ምርጫ ጣቢያ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እስከምሽቱ 3:00 ሰዓት ድረስ ይቀጥላል።

#Share #ሼር

@tikvahethiopia
#BREAKING

እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ድምፅ መስጠት ይቻላል።

በመላው ሀገሪቱ ውስጥ ምርጫ እየተካሄደ ባለባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እስከምሽቱ 3:00 ሰዓት ድረስ እንደሚቀጥል ምርጫ ቦርድ አሳውቋል።

#Share #ሼር

@tikvahethiopia
#ATTENTION

ሠመራ እና ዱብቲ ከተሞች ላይ ከፍተኛ የሆነ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ፦
- ሠመራ፣
- ዱብቲ፣
- አይሳኢታ፣
- ሎጊያ እና ሚሌ ከተሞች ላይ ዛሬ በ23/12/2013 ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጧል።

የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመመለስ የጥገና ሰራተኞች ርብርብ እያደረጉ እንደሚገኙ ጠቁሟል።

በሠመራና ዱብቲ ከተሞች የሚገኙ ዜጎች የወደቀ የኤሌክትሪክ ምሰሶ እና የተበጠሰ የኤሌክትሪክ ገመድ በአካባቢያቸው ካለ ጉዳት እንዳያደርስ በስልክ ቁጥር 0910123048 ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል።

#SHARE #ሼር

@tikvahethiopia
#ማስጠንቀቂያ

" ሲሪስ አፕል ጁይስ " 100% የተሰኘው ጭማቂ በውስጡ ጎጂ የሆነ ከሻጋታ የመነጨ መርዛማ ኬሚካል ስለተገኘበት ምርቱን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ማሳሰቡን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

በፍራፍሬዎች ላይ የሚከሰት ማይኮቶክሲን የተሰኘው ከሻጋታ የሚመነጭ መርዛማ ኬሚካል በሲሪስ አፕል ጁይስ ውስጥ 100% ስለተገኘ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ማስጠንቀቂያ ተላልፏል።

ምርቱ የዓለም አቀፍ የምግብ ደህንነት ማስጠንቀቂያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርቱ ጥቅም ላይ እንዳይውል ባለስልጣን መ/ቤቱ ያስጠነቀቀ ሲሆን፥ በተመሳሳይ የሲሪስ አፕል ጁይስ አምራች የሆነው የደቡብ አፍሪካ የምግብና የመጠጥ አምራች ምርቱ ማይኮቶክሲን የተሰኘው ከሻጋታ የሚመነጭ መርዛማ ኬሚካል በውስጡ በእንዳለ በመግለጽ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀመው ነው ያሳሰበው፡፡

የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ፥ ህብረተሰቡ የሲሪስ አፕል ጁይስ 100% ምርት በሀገራች ገበያ ውስጥ እንዳለ በመገንዘብ ምርቱን እንዳይጠቀም አስጠንቅቆ ÷ ምርቱን በማንኛውም አጋጣሚ ገበያ ላይ ሲገኝ በፌዴራል ደረጃ በነጻ ስልክ መስመር በ8482 እንዲሁም በአቅራቢያ ለሚገኙ የክልል ተቆጣጣሪ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ መልዕክት ማስተላልፏል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#GONDAR

" ለመንገድ ስራ ደማሚት ይፈነዳል፤ እንዳትደናገጡ " - የጎንደር ፖሊስ

ከዛሬ ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ከኮሌጅ ብሪጋታ የመንገድ ስራ ለመስራት ደማሚት ይፈነዳል፡፡

ነዋሪዎች ጉዳዩን አውቀው ያለ ምንም መደናገጥ የዕለት ከዕለት ተግባራቸውን እንዲያከናውኑ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ መልእክት አስተላልፏል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
አዲስ አበባ !

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሲመለከቱ የሚያመለክቱበት ነፃ የስልክ መስመር ይፋ ሆነ።

ነዋሪዎች አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሲመለከቱ የሚያሳውቁበት ነፃ የስልክ መስመር " 9977 " ነው።

#ሼር #SHARE

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

ማንኛውም የፀጥታ ችግር እንቅስቃሴ ሲመለከቱ ወይም ደግሞ ጥቆማ ለመስጠት ከፈለጉ ከላይ በተቀመጡት የስልክ መስመሮች ፈጥነው እንዲደውሉ የፌዴራል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ተጨማሪ አዳዲስ የደንብ ልብሶችን ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ አሳውቋል።

ነባሩን የደንብ ልብስ መጠቀም ማቆሙን ተቋሙ ገልጿል፡፡

ከዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አዳዲሶቹ የደንብ አልባሳትን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ እና ነባሩ የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ መቀየሩ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ አሮጌውን የደንብ ልብስ ለብሶ የተገኘ አመራር እና አባል ላይ ጠንከር ያለ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል ተብሏል።

ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አሮጌው የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ በአዳዲሶቹ መቀየሩን ተገንዝበው አሮጌውን የደንብ ልብስ የለበሰ የፖሊስ አባል ሲያጋጥማቸው መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ፖሊስ ስራ ላይ ካዋላቸው አዳዲስ የደንብ አልባሳት ጋር ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደገገ ስለሆነ ከአ/አ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

#Share #ሼር

@tikvahethiopia