TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬆️

በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር #ታከለ_ኡማ ሰብሳቢነት የሚመራው እና የፌደራል ፖሊስ ፣ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽኖችን ያካተተው የፀጥታ ግብረሀይል ሳምንታዊ ውይይት አድርጎል። በተለይ በመዲናዋ የአዲስ አመት በዓል ያለምንም #የፀጥታ ችግር እንዲከበር በሚደረጉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ተወያይተዋል።

ህብረተሰቡ የሚመለከታቸውን #አጠራጣሪ ነገሮች #ለፖሊስ በማሳወቅ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ግብረሀይሉ #አሳስቧል

ግብረሀይሉ በህገወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ የገቡ 300 የሚሆኑ ሞተር ሳይክሎችን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጎል። በተመሳሳይ ከቀናት በፊት በርካታ ቁጥር ያለው ህገወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉ ይታወሳል።

©የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በደቡብ ወሎ ዞን ሐይቅ ከተማ ከ600 በላይ ጥይት ከአንድ ክላሽንኮብ ጠብመንጃ ጋር በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር መያዙን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ኮማንደር ጌታቸው ሙላት እንደገለጹት መሳሪያው ከነጥይቱ ሊያዝ የቻለው የህብረተሰቡን ጥቆማ መሰረት በማድረግ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ነው፡፡

በእዚህም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-20584 በሆነ የህዝብ ማመላለሻ አይሱዝ መኪና ውስጥ አንድ ታጣፊ ክላሽ እንኮብ የጦር መሳሪያ፣ 613 የክላሽ እንዲሁም ዘጠኝ የመትረየስ መሳሪያ ጥይቶች ተይዘዋል።

በተጨማሪም ሰባት ህገ ወጥ የሞባይል ስልኮች በፍተሻው መያዛቸውን የገለጹት። ተሽከርካሪው የተያዘው ትናንት ከወረባቦ ወረዳ ተነስቶ ወደ ሐይቅ ከተማ ሊገባ ሲል ቀበሌ 02 ላይ ሲደርስ መሆኑንም ኮማንደር ጌታቸው አመልክተዋል፡፡

እንደእርሳቸው ገለጻ በወንጀሉ የተጠረጠሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳዩ በመጣራት ላይ ሲሆን ሁለቱ መምህር መሆናቸው ታውቋል።

ህብረተሰቡ #ለፖሊስ ላደረሰው #ጥቆማ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ኮማንደሩ በቀጣይም ህገ ወጥነትን በጋራ ለመከላከል ህብረተሰቡ የጀመረውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

Via #OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia