TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update መቄዶኒያ⬆️

"የከተማ አስተዳደራችን እያከናወነ ባለው የበጎ ፍቃድ ሳምንት አንዱ አካል ያደረግነው #መቄዶኒያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማእከል ውስጥ ከአረጋውያንንና ከአእምሮ ህሙማን ጋር በጋራ ምሳ መብላት ይገኝበታል በዚህ ዥግጅት ላይም ክብርት ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ #ዝናሽ_ታያቸው ተገኝተው አረጋዊያኑንና የአእምሮ ህሙማኑን ምሳ በማብላት ላይ እንገኛለን።"

©ምክትል ከንቲባ ዳግማዊት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

በአዲስ አበባ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ የቀጨኔ ህፃናት ማሳደጊያ ተቋም የአደራ ቤተሰብ የህፃናት ርክክብ ፕሮግራም አካሂዷል። በፕሮግራሙ ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው በክብር እንግድነት ተገኝተው ነበር።

©የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው በኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች ለሚገነቡ ሁለተኛ ደረጃ
ትምህርት ቤቶች የግንባታ ማስጀመሪያ የመግባቢያ ስምምነት ከክልሎቹ ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በትናንትናው ዕለት ፈርመዋል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አልብኮ⬆️

ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ በ20 ሚሊየን ብር ለሚገነባው ጦሳ ፈላና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ይልቃል ከፍያለው እና የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳዳሪ አቶ እጅጉ መላኬን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ሚኒስቴር በሚዘጋጀው የሴቶች ሰላም ኮንፍረንስና ጀግኒት ፕሮግራም ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፣ የሰላም ሚኒስትሯ #ሙፈሪያት_ካሚል፣ ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው ይገኛሉ ተብሏል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቄዶንያ‼️

ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ ዛሬ ጠዋት ከክብርት ቀዳማይ እመቤት ወ/ሮ #ዝናሽ_ታያቸው ጋር በመሆን የመቄዶንያ የአረጋውያን እና የአካል ጉዳተኞች ማዕከልን ጎበኙ። ለአካል ጉዳተኞች መንቀሳቅሻ የሚሆኑ 15 ዊልቼሮችንም በእርዳታ አስረክበዋል። ለሜቄዶንያ አመራሮች፣ ሰራተኞች እና ድጋፍ ለሚያደርጉ አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር⬆️

ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው በባሕር ዳር የአካል ተሃድሶ ማዕከል በመገኘት ለአካል ጉዳተኞች 15 ዊልቼር ድጋፍ አደረጉ፡፡

የክልሉን መንግስት በመወከል ንግግር ያደረጉት አቶ ብናልፍ አንዷለም አካል ጉዳተኞችን ማዕከል ያደረገ ስራ መሰራቱ ጥቅሙ ላቅ ያለ በመሆኑ ቀዳማዊት እመቤቷ ያደረጉትን ድጋፍ የክልሉ መንግስት በአድናቆት ይመለከተዋል ነው ያሉት፡፡

የአካል ጉዳተኞቹን ወክለው ድጋፉን የተቀበሉት አቶ ይመር መልካሙ ባለፈው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ.ር ዐብይ መጥተው በጎበኙን ወቅት የገቡትን ቃል ቀዳማዊት እመቤቷ ተግባራዊ ስላደረጉልን ደስታችን ለመግለፅ እንወዳለን ብለዋል፡፡

በማዕከሉ የምንኖር ጉዳተኞች በጠቅላይ ሚኒስትር ስንጎበኝ ዶ.ር ዐብይ የመጀመሪያው ናቸው ያሉት አቶ ይመር በቀጣይም ተከታታይ ድጋፍ ሊደረግልን ይገባል ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሽረ እንዳስላሴ🔝

ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ሽሬ እንዳስላሴ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው። ቀዳማዊት እመቤቷ ዛሬ ረፋድ ላይ ሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ሲገቡ የክልሉ ምክትል ርእሰ-መስተዳድር ዶክተር #ደብረፅዮን_ገብረሚካኤልን ጨምሮ የከተማው ነዋሪ ህዝብ ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል። እንደ ኢዜአ ዘገባ ወይዘሮ ዝናሽ በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ለሚገነባው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት #መሰረተ_ድንጋይ ያስቀምጣሉ ተብሎም ይጠበቃል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ #ዝናሽ_ታያቸው በሽረ እንዳስላሴ በ20 ሚሊን ብር የሚገነባ የ2ኛ ደ/ት ቤት መሰረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበታ ዓይነ ስውራን ትምህርት ቤት🔝

ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው በሰበታ የሚገኘውን የሰበታ ዓይነ ስውራን ትምህርት ቤት ጎብኝተዋል። ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው በጉብኝቱ ወቅትም ከባለድርሻ አካላት ጋር በትምህርት ቤቱ ዙሪያ ውይይት አደርገዋል። በቆይታቸውም በትምህርት ቤቱ አሉ በተባሉ ችግሮች ዙሪያ እና በመፍትሄዎቻቸው ላይ ምክክር ተደርጓል።

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ!!

ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለተከታተሉበት የጎንደሩ ጻዲቁ ዮሐንስ 1ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የኮምፒዩተር ድጋፍ አድርገዋል፡፡

በጻድቁ ዮሐንስ አንደኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የተገኙት ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለዓይነ ስውራን ተማሪዎች የሚያገለግል መተግበሪያ የተጫነባቸውን ሁለት ኮምፒተሮች አበርክተዋል።

በቀጣይም 20 ተጨማሪ ለዓይነ ስውራን ተማሪዎች የሚያግዙ ኮምፒዩተሮችን ለመስጠትም ቃል የገቡት ቀዳማዊት እመቤቷ በርካታ መጻሕፍትንም ለትምህርት ቤቱ አበርክተዋል።

ባለፈው መስከረም ወር ላይ በዚሁ ትምህርት ቤት የተገኙት ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከ60 በላይ የዓይነ ስውራን መፃፊያ መሳሪያ (ብሬይል)፣የብሬይል ወረቀት፣ የዓይነ ስውራን መምሪያ ዱላ፣ ልዩ ልዩ እስክሪብቶዎች፣ ደብተሮችንና ቦርሳዎችን ማበርከታቸው ይታወሳል።

በተጨማሪም በጎንደር ከተማ ሎዛ ማሪያም አካባቢ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስገንባት መጀመራቸን ከአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምናና የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አደረጉ፡፡ በእርዳታ ርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደተገለጸው እርዳታው ከተደረገላቸው መካከል በጎንደር ከተማ የሚገኘው የጻዲቁ ዮሃንስ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ቤትና በአዘዞ ከተማ የሚገኘው የአይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤት ይገኙበታል፡፡ ለሁለቱ ትምህርት ቤቶች በእርዳታ ከተሰጡት የትምህርት ቁሳቁሶች መካከል አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችሉ  አራት ኮምፒውተሮች ይገኙበታል፡፡ እንዲሁም አራት የብሬል መጻፊያ ታይፕራይተሮችና 30 በብሬል የተዘጋጁ የማስተማሪያና የማጣቀሻ መጻህፍቶች በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ለትምህርት ቤቶቹ ተበርክቶላቸዋል፡፡ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልም ለአእምሮ ታማሚዎች ህክምና አገልግሎት የሚውል የአእምሮ ነርቭ ስርአት መለኪያ መሳሪያ በእርዳታ ተሰጥቷል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 21/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ መንግስት “የጤፍ ባለቤት ነኝ” ያለውን የሆላንድ ድርጀት በዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት ሊከስ ነው።
.
.
በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ሁለት አርሶ አደሮች በኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር "ኦነግ ታጣቂዎች" መገደላቸውንና አንድ አርሶ አደር መቁሰሉን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር የሴፍቲና ሲኬዩሪቲ ዲፓርትመንት ባለሙያዎች በባቡሩ ላይ #ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቢከሰት እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል የሚያሳይ ልምምድ አካሂደዋል።
.
.
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የቀጠለውን የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መርተዋል።
.
.
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፓሬሽን/ሜቴክ/ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ እንደሚያደርግ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #አህመድ_ሀምዛ አስታውቀዋል።
.
.
በሰቆጣ ከተማ ሦስት #ፓኪስታናውያን በሕገ ወጥ የሞባይል ሽያጭ ተሰማርተው እጅ ከፈንጅ ተይዘዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት፣ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ፣ የልደትና ሞት ሰርተፍኬት እንዲሁም የጋብቻ እና ፍቺ ሰርተፍኬቶች በዲጂታል ሰርተፍኬት ሊቀየሩ ነው ተብሏል።
.
.
ኢ/ር #ታከለ_ኡማ ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የፈረሰውን መስጂድ በመጎብኘት የአከባቢውን የሙስሊም ማህበረሰብም አነጋግረዋል፡፡
.
.
#የፌዴራል_መንግሥት አመራሮች የድሬዳዋ ነዋሪዎችን በከተማዋ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ አወያይተዋል፡፡
.
.
በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና በማህበራዊ ፍትህ ላይ ያተኮረ የመጀመሪያውን አረንጓዴ የፖለቲካ ፓርቲ (Green Party) ለማቋቋም ጊዜያዊ አስተባባሪ ፓርቲ መሰየሙን ዋዜማ ራድዮ ዘግቧል።
.
.
ከሳውዲ አረቢያ ጋር በተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ መንገድ ለሚሄዱ ሰራተኞች የቪዛ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።
.
.
ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና ያለምንም ህጋዊ ሰነድ ከአገር ሊወጣ ሲል #በጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ከጥር 19 እስከ 21 ለተከታታይ ሦስት ቀናት #በሀዋሳ_ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ 4ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ተጠናቋል።
.
.
ከጭናግሰን ከተማ የማርያምን ክብረ በዐል አክብረው ይመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች መንገድ መዝጋታቸውን ተከትሎ #በጅግጅጋ_ከተማ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት መረጋጋቱ ታውቋል። በግጭቱ የ2 ሰው ህይወት አልፏል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለተከታተሉበት የጎንደሩ ጻዲቁ ዮሐንስ 1ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የኮምፒዩተር ድጋፍ አድርገዋል፡፡
.
.
#በድሬዳዋ_ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ #የምስራቅ_ዕዝ_ጠቅላይ_መምሪያ አስጠነቅቋል።
.
.
አቃቤ ሕግ የቀድሞ #የሜቴክ የስራ #ሀላፊዎች በነበሩት ሻለቃ #ክንደያ_ግርማይና ሌተናል ኮሎኔል #አሰፋ_ዮሐንስ ላይ ክስ መስርቷል።
.
.
የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) በዚህ ሳምንት ሐሙስ በይፋ ትጥቅ ይፈታል።
.
.
በቅርቡ በመንግስት እና ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል በአምቦ በተደረገው ስምምነት መሠረት እርቁን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የቴክኒክ ኮሚቴ ሥራውን በተግባር መጀመሩን የቴክኒክ ኮሚቴው አባል አቶ #ጀዋር_መሀመድ አስታውቀዋል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምናና የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አድርገዋል።
.
.
#የኢፌዲሪ_አየር_ሃይል በሶማሊያ ከባይደዋ በስተምስራቅ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ቡርሃይቤ በተባለ የአልሻባብ ይዞታ ላይ ጥር 16 ቀን 2ዐ11 ዓ.ም ድብደባ በመፈፀም ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ የተከሰተዉን #አለመረጋጋት ተከትሎ የከተማዉ ፖሊስ ኮሚሽን 308 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያካሄደ ነዉ፡፡

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ፣ etv፣ fbc፣ VOA፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት፣ የጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ አብመድ
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ህፃን ሚሊዮን🔝

ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ህጻን ሚሊዮንን #በጉዲፈቻ ለማሳደግ ያቀረቡት ጥያቄ በፍርድ ቤቱ ተቀባይነት አገኘ።

ቀዳማዊ ቤተሰቡ ህጻን #ሚሊዮንን ከክበበ ህጻናት ማሳደጊያ ተቀብሎ #ለማሳደግ ጥር 14 ቀን 2011 ዓ.ም ለፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ የወንጀል ችሎት የህጻናትና ሴቶች ጉዳይ በፅሁፍ ማመልከቻ አቅርቦ ነበር። በማመልከቻቸው አመልካቾች የተፈራረሙበት የጉዲፈቻ ውል #እንዲጸድቅላቸው ጠይቀዋል።

ቀዳማዊ ቤተሰቡ ለህጻኑ #መልካም አስተዳደግ እንደሚሰጥና ህጻኑን ለማሳደግ በቂ ኢኮኖሚያዊ አቅም እንዳለው ጠቅሷል። ፍርድ ቤቱም ህጻን ሚሊዮን ከሁለት አመት እድሜ በታች በመሆኑ ችሎት ፊት ቀርቦ አስተያየት መስጠት ስለማይችል ችሎቱ የተለያዩ ማስረጃዎችን መርምሮ፥ አመልካቾች ህጻኑን በጉዲፈቻ ቢያሳድጉት ችግር የለውም ወይም መልካም ነው ብሎ በመወሰን ጥር 14 ቀን 2011 ዓ.ም የተፈራረሙትን ውል ተሻሽሎ በወጣው የቤተሰብ ህግ 213/92 አንቀጽ 93 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት አጽድቆላቸዋል።

የውሳኔውን ግልባጭም ጉዳዩን ችሎት ፊት ቀርበው ለተከታተሉት ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው እንዲደርሳቸው ተደርጓል። የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ለቀዳማዊ ቤተሰቡ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። አያይዘውም በጉዲፈቻ ልጅ ለማሳደግ መወሰናቸው ለሌሎች አርዓያ እንደሚሆንና ልጅ ማሳደግ ትልቅ ሃላፊነት መሆኑን እንዲሁም ህጻናትን በጉዲፈቻ ለማሳደግ ሁሉም እንዲያስብ ያደርጋል ብለዋል።

በእድሜያቸው ሶስት መንግስታት ማየታቸውን ያነሱት ፕሬዚዳንቷ ከፍተኛ የሃገር መሪዎችና ሃላፊዎች ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ሲያስፈጽሙ አይተው እንደማያውቁም ተናግረዋል። ቀዳማዊት እመቤቷ #ችሎት ፊት ቀርበው ጉዳያቸውን ማስፈጸማቸው ሁሉም ሰው በህግ ፊት እኩል መሆኑን ያመላክታልም ነው ያሉት።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው በምዕራብ ጉጂ ዞን ሱሮ በርጉዳ ወረዳ ለሚገነባ የሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት የመሰረተ ድጋይ አስቀመጡ፡፡ የሚገነባው የሁለተኛ ድርጅት ትምህርት ቤት ሲጠናቀቀ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በአካባቢያቸው መከታተል እንደሚያስችላቸው ተነግሯል፡፡

via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሩዳንዳ የዘር ጭፍጨፋ መታሠቢያ🔝

ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድና ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው ለሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ 25ኛ ዓመት መታሰቢያ በተዘጋጀዉ የእግር ጉዞ ላይ ተሳትፈዋል። የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ 25ኛ ዓመት መታሰቢያ ላይ ለመገኘት ወደ ሩዋንዳ የቀኑት ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በእግር ጉዞው የተሳተፉት ከፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜና ከሌሎችም የአለም መሪዎች ጋር በመሆን ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሩዋንዳ ቆይታቸውን አጠናቀው ትላንት ማምሻዉን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ምንጭ:-ጠቅላይ ሚንስቴር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ #ዝናሽ_ታያቸው በግንባታ ላይ የሚገኘውን የቁስቋም የህፃናት ክብካቤ ማዕከል ጎበኙ፡፡ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው በዛሬው ዕለት የቁስቋም የህፃናት ክብካቤ ማዕከል የግንባታ ሂደት የደረሰበትን ደረጃ ጎብኝተዋል፡፡ ማዕከሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ ለወ/ሮ ዘውዴ የህፃናት ክብካቤ ማዕከል ተላልፎ እንደሚሰጥም ነው ከቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት የተገኝ መረጃ ያመላክታል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia