TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የስራ ማቆም አድማ⬇️

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ‹‹ላለፉት ስምንት ዓመታት ላነሳናቸው ፍትሐዊ የሆኑ ከሙያ ዕውቅና፣ ከደመወዝና ከጥቅማ ጥቅም ጋር ለተገናኙ ጥያቄዎች በቂና ወቅታዊ ምላሽ አላገኘንም፤›› በማለት፣ ከሰኞ ነሐሴ 21 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠዋት ጀምሮ የሥራ ማቆም #አድማ እንደሚያደርጉ አስታወቁ፡፡

በዚህም መሠረት #ከሰኞ ጠዋት አንድ ሰዓት ጀምሮ ከአምቡላንስ፣ ከቪአይፒና ከወታደራዊ በረራዎች ውጪ አናስተናግድም ሲሉም፣ ለባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ባስገቡት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡

ተቆጣጣሪዎቹ ሰኔ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባስገቡት ደብዳቤ በአፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው፣ ምላሽ ካላገኙ ግን ሥራቸውን #እንደሚለቁ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡

©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬇️

ዞናዊ ስምሪቱ የሚኖሩበትን አካባቢ ያላገናዘበና ፍትሃዊነት የጎደለው መሆኑን በአዲስ አበባ የተሰማሩ ድጋፍ ሰጭ ባለታክሲዎች ተናገሩ።

ቅሬታቸውን ለFBC ያቀረቡ ባለ ታክሲዎች እንዳሉት ዞናዊ የስራ ስምሪቱ የመኖሪያ አካባቢያቸውን ያለገናዘበና ፍትሃዊነት የጎደለው ነው።

ባለ ታክሲዎቹ ስምሪቱ ፍትሃዊ አለመሆኑን ተከትሎም በዛሬው እለት በአንዳንድ አካባቢዎች የስራ መቆም #አድማ አድርገዋል።

ባለ ታክሲዎቹ አንዳንድ መስመሮች በህገ ወጥ መንገድ ለተወሰኑ ግለሰቦች እየተሰጡ መሆኑንም አንስተዋል።

ጠዋትና ማታ እየሰሩ መሆናቸውን የሚግልጽ የስራ መሙያ ፎርም ለመሙላትም የመንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ተቆጣጣሪዎች ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በስራ ቦታቸው ባለገኘታቸው ምክንያት መቸገራቸውንም አስረድተዋል።

በዚህ ሳቢያም በህገ ወጥ መንገድ ላለመቀጣት በሚል ለተቆጣጣሪዎች ገንዘብ እየከፈሉ መሆኑን በመጥቀስ፥ ተቆጣጣሪዎቹ ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባልም ብለዋል።

እንደ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገለጻ ማህበር ለማቋቋም ያደረጉት ሙከራ በተለያየ ምክንያት ባለመሳካቱ መብታቸውን ለማስከበር ተቸግረዋል።

አሁን ላይ ያለው ችግር ይስተካከል ያሉት አሽከርካሪዎቹ ረጃጅም መስመር እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል።

በተጨማሪም ድጋፍ ሰጭ እንደመሆናቸው መጠን በስራ መግቢያና መውጫ ሰዓት ላይ ከሚሰሩበት መስመር ውጭ ወደ ሌሎች መስመሮች እንዲሰማሩም ነው የጠየቁት።

የአዲስ አበባ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ በበኩሉ ዞናዊ ስምሪቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ በመታገዝ የተሰራ በመሆኑ የፍትሃዊነት ጥያቄ አይነሳበትም ብሏል።

ዛሬ የስራ ማቆም አድማ ያደረጉ ባለ ታክሲዎችም አነስተኛ ገቢ በሚያስገኙ መስመሮች የተመደቡ መሆናቸውን የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ምትኩ አስማረ ተናግረዋል።

ምክትል ሃላፊው ዛሬ የተፈጠረውን የታክሲ አገልግሎት እጥረትም የሸገርና ሌሎች ትራንስፖርት ሰጭ ማህበራትን በማሰማራት ለመፍታት ተሞክሯልም ብለዋል።

በቀጣይም የቁጥጥር ስርዓቱን ለማዘመንና ከሰው ንክኪ ነጻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የስራ ማቆም አድማ⬆️

የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሰራተኞች በደመወዝ ጭማሪ ጥያቄና የአገልግሎት አሰጣጥ መሻሻልን በመጠየቅ ላለፉት ሶስት ቀናት የስራ ማቆም #አድማ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡

ሰራተኞቹ ለኢቢሲ በስልክ እንደገለፁት በግድቡ ግንባታ ላይ አሻራቸውን እያሳረፉ ቢሆንም የሚከፈላቸው #ክፍያ አናሳ መሆኑ ኑሯቸውን ከባድ እንዳደረገባቸው ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በግንባታው ተቋራጭ በኩል ከደመወዝ ክፍያ ማነስ በተጨማሪ፣ የሰራተኛ አያያዝ ችግር፣ የሰራተኞች ምግብ ቤት የጥራት ችግርና የዋጋ መናር የስራ ማቆም አድማ እንዲያደርጉ እንዳስገደዳቸው ተናግረዋል፡፡

የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም ወ/ኪዳን ሰራተኞቹ ላለፉት ሶስት ቀናት የስራ ማቆም አድማ ላይ መሆናቸውን ለአቢሲ አረጋግጠዋል፡፡

ሰራተኞቹ ያቀረቡትን ችግር ለመፍታት ውይይቶች በመደረግ ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡

ከሰዓት በኃላ የግንባታ ተቋራጩን ጨምሮ በሚደረግ የጋራ ውይይት ችግሩ ይፈታል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update⬆️የኢትዮጵያ ሲቪል አቬዬሽን ባለስልጣን በስራ ማቆም #አድማ ላይ ለሚገኙት #ሰራተኞች በነሀሴ 24 እንዲፈርሙ አቅርቦላቸው የነበረው #የይቅርታ ፎርም ከላይ የምትመለከቱትን ይመስላል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአየር ትራፊክ ባለሞያዎች⬇️

ትናንት በቁጥጥር ሥር የዋሉት 9 የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ባለሙያዎች የተያዙት ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት እሥራት ሊያስቀጣ በሚችል #ጥፋት መሆኑ ተገለጸ፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል ናቸው ይሕን ያሉት። ኮሚሽነሩ ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ በአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ሠራተኞቹና በአሠሪያቸው ሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣን መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ በድርድር ለመፍታት ጥረት መደረጉንና ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንም ጣልቃ ገብቶ ማደራደሩን ተናግረዋል።

“የተወሰኑ የእንቅስቃሴው መሪዎች ሠራተኛው #አድማ እንዲመታ በማስተባበር ቀጥለውበታል” ያሉት ኮሚሽነሩ “የኢትዮጵያን አየርም ሆነ የአየር መንገዱን ዝና ጥያቄ ውስጥ የሚያስገቡ
መልዕክቶችን ለዓለምአቀፍ ድርጅቶች ሲያሠራጩ ቆይተዋል” ብለዋል።

©ዋዜማ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የፍርድ ቤት ውሎ⬇️

በሃገር ኢኮኖሚ ላይ #አሻጥር በመስራት እና በኢኮኖሚ ላይ #ጫና ማሣደር ወንጀል ተሣትፈዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የነበሩ 9 የሲቪል አቪዬሽን የአየር ትራፊክ ቁጥጥር ሰራተኞች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ቡድን በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት በአቀረበው የምርመራ መዝገብ ተጠርጣሪዎች በቡድን በመደራጀት መንግሥትና ህዝብን ለማለያየት ተንቀሣቅሰዋል የሚለውን ጠቅሷል፡፡

ወርሀዊ ደሞዛቸው በአስር እጥፍ እንዲያድግና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች አልተከበሩልንም በማለት ከነሐሴ 21 ጀምሮ የሥራ ማቆም #አድማ ማድረጋቸውንም ፖሊስ ጠቅሷል፡፡

ለዚህም እንዲረዳቸው የሌሎች ሰራተኞችን ፊርማ በማስመሰል መፈረም እና ስራ እንዲያቆሙ አነሣስተዋል በሚል #ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር እንዲውሉ ካደረጓቸው ምክንያቶች ይጠቀሣል የሚለውንም የምርመራ ቡድኑ በመዝገቡ አካቷል፡፡

ቡድኑ ሌሎች የምርመራ ስራዎችን ለማከናወን 14 ቀን ጠይቋል። ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው የመብት ጥያቄዎችን ማንሣታቸውን በመጥቀስ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸው እንዲያከብርላቸው አመልክተዋል፡፡

ግራቀኙን የተመለከተው ችሎት ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀን 8 ቀን በመፍቀድ ለመስከረም 2 /2ዐ11 #ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መንገዶች ተከፍተዋል‼️

በአፋር የነበረው የመንገድ መዝጋት #አድማ #እንደተጠናቀቀና መንገዶች #እንደተከፈቱ ተገልጿል፡፡ ሶማሊ ነዋሪዎች የሚበዛባቸው ሶስት ቀበሌዎች ላይ እየተፈጠረ ያለውን #ግጭት ለማርገብ በሚል ከቀበሌዎቹ የአፋር ክልል ልዩ ሃይል #እንዲወጣ መደረጉን #በመቃወም ነበር የክልሉ ወጣቶች ተቃውሞ የጀመሩት፡፡ የተቃውሞ እንቅስቃሴው ተጓዦችንም ሆነ ንብረቶቻቸው ላይ ምንም አይነት #ጉዳት_ያላደረሰ ነበር፡፡ከአዋሽ ወደትግራይ የሚወስደው መንገድ ትላንት ጠዋት 2 ሰዓት ላይ የተከፈተ ሲሆን ከመሃል አገር ወደምስራቅ ኢትዮጵያና ወደ ጂቡቲ የሚወስዱት መንገዶችም ተከፍተዋል፡፡

Via VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስጠንቀቂያ‼️

#በድሬዳዋ_ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ #የምስራቅ_ዕዝ_ጠቅላይ_መምሪያ አስጠነቀቀ።

via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 21/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ መንግስት “የጤፍ ባለቤት ነኝ” ያለውን የሆላንድ ድርጀት በዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት ሊከስ ነው።
.
.
በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ሁለት አርሶ አደሮች በኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር "ኦነግ ታጣቂዎች" መገደላቸውንና አንድ አርሶ አደር መቁሰሉን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር የሴፍቲና ሲኬዩሪቲ ዲፓርትመንት ባለሙያዎች በባቡሩ ላይ #ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቢከሰት እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል የሚያሳይ ልምምድ አካሂደዋል።
.
.
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የቀጠለውን የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መርተዋል።
.
.
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፓሬሽን/ሜቴክ/ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ እንደሚያደርግ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #አህመድ_ሀምዛ አስታውቀዋል።
.
.
በሰቆጣ ከተማ ሦስት #ፓኪስታናውያን በሕገ ወጥ የሞባይል ሽያጭ ተሰማርተው እጅ ከፈንጅ ተይዘዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት፣ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ፣ የልደትና ሞት ሰርተፍኬት እንዲሁም የጋብቻ እና ፍቺ ሰርተፍኬቶች በዲጂታል ሰርተፍኬት ሊቀየሩ ነው ተብሏል።
.
.
ኢ/ር #ታከለ_ኡማ ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የፈረሰውን መስጂድ በመጎብኘት የአከባቢውን የሙስሊም ማህበረሰብም አነጋግረዋል፡፡
.
.
#የፌዴራል_መንግሥት አመራሮች የድሬዳዋ ነዋሪዎችን በከተማዋ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ አወያይተዋል፡፡
.
.
በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና በማህበራዊ ፍትህ ላይ ያተኮረ የመጀመሪያውን አረንጓዴ የፖለቲካ ፓርቲ (Green Party) ለማቋቋም ጊዜያዊ አስተባባሪ ፓርቲ መሰየሙን ዋዜማ ራድዮ ዘግቧል።
.
.
ከሳውዲ አረቢያ ጋር በተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ መንገድ ለሚሄዱ ሰራተኞች የቪዛ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።
.
.
ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና ያለምንም ህጋዊ ሰነድ ከአገር ሊወጣ ሲል #በጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ከጥር 19 እስከ 21 ለተከታታይ ሦስት ቀናት #በሀዋሳ_ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ 4ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ተጠናቋል።
.
.
ከጭናግሰን ከተማ የማርያምን ክብረ በዐል አክብረው ይመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች መንገድ መዝጋታቸውን ተከትሎ #በጅግጅጋ_ከተማ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት መረጋጋቱ ታውቋል። በግጭቱ የ2 ሰው ህይወት አልፏል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለተከታተሉበት የጎንደሩ ጻዲቁ ዮሐንስ 1ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የኮምፒዩተር ድጋፍ አድርገዋል፡፡
.
.
#በድሬዳዋ_ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ #የምስራቅ_ዕዝ_ጠቅላይ_መምሪያ አስጠነቅቋል።
.
.
አቃቤ ሕግ የቀድሞ #የሜቴክ የስራ #ሀላፊዎች በነበሩት ሻለቃ #ክንደያ_ግርማይና ሌተናል ኮሎኔል #አሰፋ_ዮሐንስ ላይ ክስ መስርቷል።
.
.
የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) በዚህ ሳምንት ሐሙስ በይፋ ትጥቅ ይፈታል።
.
.
በቅርቡ በመንግስት እና ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል በአምቦ በተደረገው ስምምነት መሠረት እርቁን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የቴክኒክ ኮሚቴ ሥራውን በተግባር መጀመሩን የቴክኒክ ኮሚቴው አባል አቶ #ጀዋር_መሀመድ አስታውቀዋል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምናና የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አድርገዋል።
.
.
#የኢፌዲሪ_አየር_ሃይል በሶማሊያ ከባይደዋ በስተምስራቅ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ቡርሃይቤ በተባለ የአልሻባብ ይዞታ ላይ ጥር 16 ቀን 2ዐ11 ዓ.ም ድብደባ በመፈፀም ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ የተከሰተዉን #አለመረጋጋት ተከትሎ የከተማዉ ፖሊስ ኮሚሽን 308 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያካሄደ ነዉ፡፡

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ፣ etv፣ fbc፣ VOA፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት፣ የጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ አብመድ
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ‼️

የመልካም አስተዳደርና የሥራ  አጥነት መሠረታዊ ጥያቄዎች በፍጥነት ለመመለስ የሚያግዝ የ60 ቀናት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናገሩ።

የድሬዳዋ አስተዳደርና የሐረሪ ክልል ፖሊስ ገለልተኛ ሆኖ አገር አቀፍ ለውጡን በሚያግዝ መንገድ ማዋቀር /ሪፎርም/ እንደሚያስፈልግ የፀጥታ ጊዜያዊ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብርጋዲዬር ጄኔራል #ተስፋዬ_ወልደማርያም አስታውቀዋል፡፡

ዕቅዱ ሕዝብ #ብሶቱን የሚያሰማባቸውን 17 መሠረታዊ ጉዳዮች በመለየት  ሁሉን አቀፍ ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቱን ከንቲባው አቶ #ኢብራሂም_ዑስማን አስታውቀዋል፡፡

አመራሩ ከፖለቲካ ፣ከሰላምና ፀጥታ እንዲሁም ከልማትና ከመልካም አስተዳደር አኳያ የተጀመረውን እንቅስቃሴ ዳር ለማድረስ  መሥራት እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡

”በዕቅዱ መሰረት የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጭምር በማጠናቀቅ የሕዝቡን  የዓመታት ጥያቄ ምላሽ የሚያገኝበት ይሆናል። በየሥፍራው የተገነቡ የመሸጫና የማምረቻ ቦታዎች ለወጣቱ ይሰጣሉ” ብለዋል፡፡

ከሚመለከተው የበላይ አካል ጋር በመነጋገር ፖሊስ በአስቸኳይ ወደ ሪፎርም እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡

ኅብረተሰቡ ዕቅዱ ስኬታማ ለማድረግ ድጋፍና ትብብር ከማድረግ ጎን ለሰላምና #ለፀጥታ መረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ከንቲባው ጠይቀዋል፡፡

የድሬዳዋ ጊዜያዊ የፀጥታ ኮሚቴ ሰብሳቢ የምሥራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽን ብርጋዲዬር ጄኔራል ተስፋዬ ወልደማርያም በከተማዋ ሰሞኑን የተፈጠረው ሕገ-ወጥ ተግባራትና ሁከት መንስዔ አመራሩ የተሰጠውን ኃላፊነት ባለመወጣቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሁንም አመራሩ ባለበት ተጠያቂነትና ይቅርታ በመጠየቅ ዕቅዱን በማከናወን ሕዝቡን መካስ እንዳለበት አሳስበዋል። ”ሕዝቡን የማያገለግል አመራር መነሳት አለበት፤ በብጥብጥና ሁከት ውስጥ የተገኘ አመራር የማያስፈልግና በሕግ መጠየቅ ያለበት ይሆናል” ብለዋል፡፡

ኅብረተሰቡ ለውጥ በሂደት የሚመጣ  መሆኑን በመገንዘብ አገራዊ ለውጡን ለማደናቀፍና በሚፈለገው መንገድ አንዳይጓዝ የሚፈልጉ አካላትን በተቀናጀ መንገድ መከላከል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ብርጋዲዬር ጄኔራል ተስፋዬ እንደተናገሩት በድሬዳዋም ሆነ በምሥራቁ የአገሪቱ ክፍል #አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ የሚያሰፍን ዕቅድ ተዘጋጅቶ  በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡

ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ በማራገብ ሂደት #ፖሊስና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ብለዋል።

በመሆኑም የድሬዳዋ አስተዳደርም ሆነ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽኖች ውስጥ ሥር ነቀል ለውጥ ማድረግና የኅብረተሰቡን ሰላምና ፀጥታ በአስተማማኝ መንገድ መጠበቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ምንጭ፦ ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ድሬዳዋ

ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ #በማራገብ ሂደት #ፖሊስ እና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ተብሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ማስጠንቀቂያ

በድሬዳዋ ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ የምስራቅ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አስጠነቅቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 22/2011 ዓ.ም.

በሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ #መሃመድ_ዑመርን ጨምሮ በ47 ግለሰቦች ላይ #ክስ ተመስርቷል።
.
.
ለከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉትን ‹‹ቪ8›› መኪኖች በሌሎች አዳዲስና ወጪ ቆጣቢ ተሽከርካሪዎች የመተካቱ ሂደት በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ ተፈጥሮ በነበረው #አለመረጋጋት እና የተቃውሞ ቀናት ጉዳት ሳይደርስበት በሀሰት ጉዳት የደረሰበት በማስመሰልና ይህንን የሃሰት ፎቶ በማህበራዊ ድረ ገፅ በመልቀቅ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
.
.
በቅርቡ የፀደቀውን የስደተኞች አዋጅ በመቃወም በአዲስ አበባና በጋምቤላ #የተቃውሞ_ሠልፍ ሊደረግ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
በሶማሌ ክልል ግጭት፣ ግድያና ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ከአራት ወራት በላይ በእስር ላይ የነበረው #ቴዎድሮስ_አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) በ80,000 ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ሰጥቷል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን "ግዴታዬን እወጣለሁ ፣ መብቴንም እጠይቃለሁ!" በሚል መርህ ቃል የከተማ አቀፍ የታክስ ንቃናቄ መድረክ ተካሂዷል።
.
.
ከኮንሶ ዞን ወደ ሶያማ ቡርጂ ወረዳ ሲጓዝ በነበረ የጭነት መኪና ላይ ባልታወቁ #ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ በትላንትናው ዕለት የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል።
.
.
#በምሥራቅ_ወለጋ_ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች 2ሺህ 380 ዩኒት ደም መለገሳቸውን የነቀምቴ ደም ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።
.
.
የመልካም አስተዳደርና የሥራ  አጥነት መሠረታዊ ጥያቄዎች በፍጥነት ለመመለስ የሚያግዝ የ60 ቀናት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናግረዋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ #በማራገብ ሂደት #ፖሊስ እና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ተብሏል።
.
.
15ኛው የኢትዮ-ጅቡቲ የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ በዛሬው ዕለት በጂቡቲ ተጀምሯል፡፡
.
.
ትናንት በሶማሌ ክልል መዲና- ጅግጅጋ የሃይማኖት ክብረ በዓልን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።
.
.
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #በኔዘርላንድ የሚገኙ ኩባንያዎችን ጎብኝተዋል።
.
.
የኢትዮጵያ #ጉብኝታቸዉን አጠናቀዉ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በዝግጅት ላይ ያሉት የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የሚበሩበት አዉሮፕላን የቴክኒክ #እክል ገጥሞት መዘግየቱ ተሰምቷል።
.
.
ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምት በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 11 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙን የኢሉገላን ወረዳ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል በአምሀራ ሳይንት ወረዳ በአጅባር ከተማ በተቀሰቀሰ #ተቃውሞ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቋረጣቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
.
.
ከጥረት ኮርፖሬት የሃብት ምዝበራ ጋር በተያያዘ የአምባሰል ንግድ ስራዎች ስራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ #ምትኩ_በየነን ጨምሮ አምስት ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
.
.
የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያና ዩጋንዳ የፖሊስ አመራሮችና አቃቤ ሕጎች የሶስት ቀናት አውደጥናትን ዛሬ #በኤርትራ_አስመራ ተጀምሯል፡፡
.
.
በአለም ላይ ያለውን የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪን ግምት ውስጥ በማስገባት እና በህዳር ወር ተደረገው ዋጋ #ማስተካከያ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ #መጠነኛ_ጭማሪ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ምንጭ፦ etv፣ fbc፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ ኢዜአ፣ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ🔝

በሀዋሳ ከተማ ተጠርቷል በተባለ የስራ ማቆም #አድማ ባንክ ቤቶች፣ የትምህርት ተቋማት፣ የንግድ ተቋማት፣ ዝግ መሆናቸውን የአይን እማኞች ገልፀውልኛል። እንዲሁም የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚሰሩ ሰራተኞችም ከስራ እንዲወጡ ተደርጓል። ምክንያቱ ደግሞ የክልል ጥያቄው በአግባቡ ምላሽ እየተሰጠው አይደለም በሚል እንደሆነ ያነጋገርኳቸው የከተማው ነዋሪዎች ነግረውኛል። ከዚህ በተጨማሪ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ትላንት ምሽት ተሰራጭቷል በተባለ የአድማ ጥሪ ወረቀት የዛሬ የትምህርት መርሃ ግብር ተቋርጧል።

ፎቶ: የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

የሚመለከታቸው አካላት አነጋግሬ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን አቀርባለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia