TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማስታወሻ🗓

በነገው ዕለት ጠ/ሚ ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከመላ ሀገሪቱ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ይወያያሉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ዛሬ ከመምህራን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ስለህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ከተናገሩት የተወሰደ...
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"መንግስት ሀገር መምራት አልቻለም፣ አቅም አጥሮታል፣ የምትሉ ወገኖች መግረፍና ማሰር ነው ያልቻልነው እንጂ መምራት የምንችልና ለውጥ ያመጣን መሆኑን ዓለም መስክሮልናል'' ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከመላ ሀገሪቱ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ባደረጉት ውይይት ከተናገሩት የተወሰደ...

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይ ሀዘናቸውን ገልፁ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አህመድ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በሰላማዊ ዜጎች ላይ በተፈጸመው ጥቃት መንግሥት የተሰማውን ሀዘን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቃቱ በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመ #ዘግናኝ ድርጊት ሲሉ ኮንነውታል። ለተጎጂ ቤተሰቦችና በሀዘን ላይ ለሚገኙት መላው ኬንያውያን የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን ገልጸዋል። ትናንት ናይሮቢ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን የኬንያው ፕሬዚዳንት #ኡሁሩ_ኬንያታ ዛሬ መግለጻቸው ይታወሳል።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳዲስ ሹመቶች‼️

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ የመንግስት ሀላፊነት ቦታዎች #ሹመቶችን ሰጥተዋል፡፡

እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ መሰረት፦

•አቶ ፍራኦል ተፈራ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ ማተቤ አዲስ የኮንስትራክሽን ስራዎች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ እዮብ አወቀ የስደተኞና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣

•ዶ/ር መብራህቱ ገ/ማሪያም የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ መስፍን ነገዎ የኮንስትራክሽን ስራዎ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ እስማኤል አሊሴሮ በሚንስትር ዴኤታ ማእረግ የሰላም ሚንስትር አማካሪ፣

አቶ ታምሩ ግንበቶ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾመዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከፓርላማ አባላት ለተነሱት ጥያቄ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• ዴሞክራሲን ለመገንባት መንግስት አርቆ አሳቢና ሆደሰፊ መሆን አለበት

• 20 የሚጠጉ የታጠቁም ያልጠተቁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ አገር ተመልሷል፣ ይህንን እንደ ድል ማየት ያስፈልጋል፡፡ እሱን ድል ዘንግተን ከመግባታቸው ጋር ተያይዞ የተፈጠሩ ችግሮች ላይ ማተኮር የለብንም

• የቀረበው የሰላም ጥሪ የሰላም መርህን የተከተለ ነው

• ከሁሉም ፓርቲዎች ጋር ተመሳሳይ መርህን የተከተለ ድርድር ነው የተደረገው፡፡

• ውግያ አያስፈልግም፣ ለበርካታ ዓመታት ሲንዋጋ ቆይተናል፤ የጦር መሳሪያ ድምጽ መሰመት የለበትም፣ በሀሳብ እንወያይና እናሸንፍ ነው ያልነው

• ከውጭ የገቡት ፓርቲዎች ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚሰሩ አሉ፣ ያን የማያደርጉ አንድ እግራቸውን አዲስአባባ አንድ እግራቸውን ውጭ አድርገው የሚጫወቱ አሉ እሱ አካሄድ ውጤታማ አያደርግም፡፡

• በሀሳብ አሸናፊ ለመሆን ነው መስራት ያለብን፡፡

• ችግር እየፈጠሩ ከችግር ለማትረፍ የሚሞክሩ ኃይሎች አሉ

• የፖለቲካ ምህዳሩ ሰፊቷል፣ ረጅም ርቀት መሮጥ የማይችሉ ፓርቲዎች ትንፋሽ ያጥራቸዋል፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች ያላቸው ምርጫ ሀሳብ ወዳላቸው ፓርቲዎች ሰብሰብ ማለት ነው

• ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ዴሞክራሲ ሰላም ነው የሚንሰረው፤ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ሰላም ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነገር ሲኖር የማያደጋም እርምጃ እንወስዳለን

Via ETV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከፓርላማ አባላት መከላከያን አስመልክቶ ለተነሱት ጥያቄ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• የመከላከያ ሰራዊት በሰፈር ውስጥ አንድ ሌባ ቦርሳ ይዞ ሲሮጥ ለምን ቦርሳ አላስጣልክም ብሎ መጠየቅ የለበትም፡፡

• የአገር ሉዓላዊነት ተደፍሮ መከላከያ ዝም ያለበት ጊዜ የለም፡፡ ያ ነው የመከላከያ ሰራዊት ስራ፡፡

• ችግሮች ሲገጥሙ መከላከያ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ከፍሎ ችግሮችን ማረጋጋት ችሏል፡፡

• መከለካያ በአገር ውስጥም በውጭም ሕይወቱን ገብሮ ለዚህች አገር እየሰራ ነው

• ወለጋ ውስጥ የክልሉ መንግስት ጥሪ ሲያደርግ መከላከያ ችግሩን ለመፍታት ሁለት ወር አልፈጃበትም፡፡

via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከፓርላማ አባላት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን አስመልክቶ ለተነሱት ጥያቄዎች ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደ ጦር ቀጠና የመጠቀም ዝንባሌ እንደሚኖር ቀድመን እናውቅ ነበር፤ ለዚያም ውይይትና ዝግጅት ተደርጎ ነበር፤ ለሁሉም ተማሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት በሚዲያ ተላልፎ ነበር

• ይህም ተደርጎ ተማሪዎችን የፖለቲካ ንግድ መጠቀሚያ ለማድረግ የሚሰሩ ኃይሎች ነበሩ፡፡

• የፖለቲካ አጀንዳን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አስገብቶ ተማሪዎችን ለማጋደል የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈጸሚያ የሚውለው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው፣ ሌላ ዓለም ላይ የትም የለም፡፡

• ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሀሳብ ልዩነት ላይ መወያየት፣ መከራከር ችግር የለውም፡፡ ተማሪዎች ድንጋና ድንጋይ አጋጭቶ እሳት ማውጣት የጋሪዮሽ ዘመን አስተሳሰብ ነው፡፡ ሀሳብና ሀሳብ እያጋጨ የተሻለ ሀሳብ የሚያመጣ ተማሪ ነው የሚፈለገው

• ድንጋይና ድንጋይ አጋጭቶ እሳት መፍጠር እንደሚቻል ለማረጋገጥ ትምህርት አያስፈልግም፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከፓርላማ አባላት ወንጀለኞችን ለፍርድ ስለማቅረብ በተመለከተ ለተነሱት ጥያቄ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• ኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀል ሰርቶ ያልታሰረ ሰው የለም፡፡ ልዩነቱ መንግስት ባዘጋጀው ማረሚያ ቤት መታሰርና ራሱን ማሰር ካልሆነ እንጂ፡፡

• መታሰር ማለት በአንድ በተወሰነ አከባቢ ተወስኖ መኖር ነው

• ሰውን ገድሎ፣ ሰርቆ ከሕግ ተጠያቂነት ውጪ የሚሆን የለም፡፡

• የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በማረሚያ ቤቶች ድንገተኛ ጉብኝት አድርጎ ክፍተት ያለበት እንዲስተካከል ተደርጓል፡፡

• በእስር ቤት ያሉ ያነባሉ፣ ይጽፋሉ፣ ስፖርት ይሰራሉ፣ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፡፡ በግል እስር ቤት ያሉ ያን ያክል የተመቻቸ ነገር እንዳለ አላውቅም

• ሁሉም ክልሎች ወንጀለኛ ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን ለመያዝ ጥረት እያደረጉ ነው፤ አሳልፈው የሰጡ አሉ፣ እየፈለግን ነው ያሉም አሉ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ገድሎም ሰርቆም መጠየቁ አይቀርም፣ ከሕግ በላይ የሆነ ማንም የለም፡፡

• እንደ ብሔር ቀርቶ እንደ ቤተሰብም ሌባ የለም፣ ሌቦች ሁሉም ብሔር ውስጥ አሉ፣ ሌቦች ሲሰርቁ ማንንም አያማክሩም፣ ከሰረቀ በኋላ የእንትን ብሔር ስለሆንኩ ብሎ ወደ ብሔር ይጠጋል፡፡

via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስካይ ላይት ሆቴል🔝

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ለአፍሪካ መሪዎች በስካይ ላይት ሆቴል የእራት ግብዣ አደረጉ። በእራት ግብዣው ላይ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

• ብዙዎች አፍሪካ ሲባል ወደ አይምሯቸው ምን እንደሚመጣ ቢታወቅም ለኔ ግን መልካም ተስፋ ያለባት አህጉር ናት

• አፍሪካ ከማንም በላይ የመልማት ተስፋ የሰነቀች አህጉር ናት፣ ከእንቅልፏም ነቅታለች

• ነገር ግን አፍሪካ ስኬታማ ለመሆን አሰቀድማ ከተለየችበት ማንነት መግኘት አለባት

• የዚህ ዘመን አፍሪካዊያን መተባበር መተማመን እና መደመር ያስፈልገናል፡፡ ከዚህ የተሻለ ምቹ ሁኔታ አይገኝምና

• አፍሪካ ከረሷ አልፎ በሰላምና ብልጽግና ለአለም ማበርከት ትችላለች

• የለውጥ ባቡር ያገኘውን እየደመረ ጉዞውን ጀምሯል፡፡ ኢትዮጵያም በግስጋሴ ላይ ትገኛለች፤ ባቡሩም ለሁሉም የሚበቃ ነው፡፡

• ከእኛም አልፎ መደመራችን አለም አቃፋዊ ይዘት እንዲኖረው መስራት ይኖርብናል

• የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ መሪ ለነበሩት ቀደማዊ ኃይለስላሴ ሃውልት እንዲቆምና እንዲታወሱ በማድረጉ ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡

• የትላንት ሳይኖር የዛሬው እኛ ያሌለን በመሆኑ የትላንቱን ማመስገን ተገቢ ነው።

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስካይ ላይት ሆቴል🔝

ለ32ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ወደ አዲስ አበባ ለመጡ መሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አህመድ የእራት ግብዣ ባደረጉበት ወቅት የተለያዩ ስጦታዎችን ለሀገራት መሪዎች አበርክተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የሰራዊቱን ስም #በማጠልሽተ የሚገኝ ምንም አይነት ቁምነገር የለም!"
.
.
መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዩኒፎርም የለበሱና መለዮ አድርጎ በህዝብ መገልገያ ስፍራዎች ለሚገኙ ወታደሮች ከሁሉም ተገልጋይ በፊት ቅድሚያ በመስጠት፤ ለሞያውና #ለወታደሮቹ ያለንን #ክብር ማሳየት እንደሚኖርበት ጠቅላይ ሚስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ አሳሰቡ፡፡

ሚድያውን ጨምሮ አጠቃላይ የኪነ-ጥበብ ማህበረሰቡ መከላከያ ሰራዊቱ በሚፈለገው ደረጃ እንዲቀረፅና በህዝብ ዘንድ ያለው እምነት እንዲያድግ የማድረግ ሀላፊነት እንዳለውም ገልፀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በ7ኛው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ቀን በአል ላይ ባደረጉ ንግግር የኪነጥበብ ባለሞያዎች በሚሰሯቸው የኪነጥበብ ስራዎች የአገር መከላከያ ሰራዊትን በተመለከተ በጥንቃቄ ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

የሰራዊቱን ስም #በማጠልሸት የሚገኝም ምንም አይነት ቁምነገር እንደሌለም ጠቅላይ ሚንስትሩ አንስተዋል፡፡

#ሆሊውድ አገርን በውትድርና ማገልገል ትልቅ ሞያ እንደሆነ በማሳየት በኩል #ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ሲሆን አሜሪካ በተሸነፈችባቸው አውደ ውጊያወችም ጭምር ወታደሮቿ የፈፀሙትን ገድል በማሳየት የወታደሮቻቸውን ጀግንነትና አገልጋይነት ለማጉላት ይሰራሉ፡፡

በአንፃሩ በአገራችን በአብዛኞቹ ፊልሞቻችን፣ ቀልዶቻችንና ፅሁፎቻችን የሚሳለው የወታደሮች እና የጦር አመራሮች ገፀባህሪ ቀረፃ #ጥንቃቄ_የጎደለው እንደሆነ መታዘብ እንደሚቻል ጠቅላይ ሚንስትሩ ጠቅሰዋል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትሩ ለሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች መከላከያ ሰራዊት ነገ ህዝብ የመረጠው ፓርቲን ተቀብሎ የሚያስቀጥለው ሰራዊት በመሆኑ ከጅምላ ፍረጃ እና ሂስ ሊታቀቡ እንደሚገባ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የቃል ኪዳን ሰነድ ፊርማ ላይ ከተናገሩት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት የክልል ሕገ መንግስት አይደለም፣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ሕገ መንግስት ሆኖ የሚቀርበው የአብዛኛውን ህዝብ ፍላጎት ለመመለስ እንጂ የአንድን ክልል፣ የአንድን ብሔር ፍላጎት ለማሳካት አይደለም፡፡

• የሁሉንም ፓርቲ ፍላጎት የሚያሟላ ሕገ መንግስት ኢትዮጵያ ከ100 ዓመት በኋላም ሊኖራት አይችልም፡፡

• ፓርቲዎች ሰብሰብ ማለት ከቻሉ መንግስት ባለው አቅም እንዲሁም ሌሎች አካላትን በማስተባበር ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነው፡፡ ለ100 ፓርቲ ግን ይህንን ማድረግ አይቻልም፡፡

• የእኛ ፍላጎት ኢትዮጵያ ውስጥ እውነተኛ ዴሞክራሲን ማምጣት እንጂ ለዘመናት ስልጣን ላይ መቀመጥ አይደለም፡፡

• የመንግስት ሚዲያዎች ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን በማያዳላ መልኩ ማስተናገድ አለባቸው፡፡

• እውነተኛ ዴሞክራሲን በኢትዮጵያ ውስጥ ለመገንባት አሁን ያለውን ውጥንቅጥ ማለፍ ይጠበቅብናል፡፡

• ዛሬ በርካታ የአፍሪካ አገራት ኢትዮጵያ ያለችበትን መሆን ይመኛሉ፣ ልምድ ይጠይቃሉ፡፡ የታሰሩ እንዲፈቱ፣ የተሰደዱ እንዲመለሱ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ሆነው ለአገር ግንባታ እንዲነጋገሩ ብዙዎች ይመኛሉ፣ ልምድ ይጠይቃሉ፡፡

• አሁን ያለንበት ሁኔታ በለፉት ዓመታት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የሚዲያ ነፃነት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያሻቸውን የሚናገሩበት ጊዜ ነው፡፡

• አሁን ላለንበት ጊዜ መምጣት ዋጋ የከፈላችሁ ሰዎች እንደ ድል አድራጊ ክብር ሊሰማችሁ ይገባል፡፡

• ስሜት ቀስቃሽ የሆኑ፣ እኔና እኛ ላይ ብቻ ያተኮሩ ንግግሮች የፖለቲካ ፓርቲዎችን የኋላ ኋላ ዋጋ ስለሚያስከፍሉ በንግግራችንም በድርጊታችንም የሚታዘበን ህዝብ እንዳለ እያሰብን ቢሆን መልካም ነው፡፡

Via etv
@tsegbawolde @tikvahethiopia
#update በጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አህመድ የተመራ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ #ኳታር ገብቷል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ዶሃ ሲደርስ የአገሪቱ የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስትር፣ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር እንዲሁም በኳታር የኢትዮጵያ አምባሳደር አቀባበል አድርገውለታል፡፡

ምንጭ፡ በኳታር የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"አዲስ ወግ"🔝

በጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አዘጋጅነት ትናንት የተጀመረውና ዛሬ ከሰዐት በኋላ በቀጠለውና የመጨረሻ በሆነው በሸራተን ሆቴል እየተካሄደ ባለው 'አዲስ ወግ' የተሰኘና ባለፈው አንድ አመት የመጣውን ለውጥ ብሎም ያጋጠሙ ፈተናዎችን በሚዳስሰው የውይይት መድረክ ''የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ማጽናት በኢትዮጵያ፤ ተግዳሮቶችና ቀጣይ አካሄዶች'' በሚል ርዕስ ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱ ላይም የኢፌዲሪ ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ተገኝተዋል።

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
etv Live🔝

#ከመጋቢት_እስከ_መጋቢት በሚል ርዕስ የጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር #ዐቢይ_አህመድ ሀላፊነታቸውን የተረከቡበት #1ኛ_ዓመት በሚሊኒየም አዳራሽ እየተከበረ ይገኛል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ሀላፊነታቸውን የተረከቡበት 1ኛ ዓመት አስመልክቶ በሚሊኒየም አዳራሽ ካደረጉት ንግግር የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፦

• በዚህ አመት በሄድኩበት ስፍራ የደገፋችሁን ወገኖች የሞታችሁልኝ የቆሰላችሁልኝ ወገኖች ልባዊ ምስጋናዬን ላቀርብ እፈልጋለሁ

• እናንተ ያለ እኔ መኖር ትችላላችሁ እኔ ግን ያለ እናተ የማልረባ ነኝ

• ለውጡ እንደ ደራሽ ውሃ ሳይሆን በብዙ ዋጋ የመጣ በመሆኑ ለውጡን ማስቀጠል ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚተው አደራ ነው

• አምና በዚህ ጊዜ የአገሪቱ ቀጣይነት በኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ ከጨለማ ጊዜ መውጣት መቻሉን መዘንጋት ተገቢ አይሆንም

• ለህዝባችን ያለፈውን ድል ብቻ በመናገር ሳይሆን ተደጋጋሚ ድሎችን ማስመዝገብ ይኖርብናል

• ባልተለወጠ ባህል እና ባልታደሰ ተቋም ለውጥ መጀመር ከባድ ነው

• ላለፉት 100 አመታት ኢትዮጵያ በአንድ አመት አምጥታ የማታውቀውን ባለፉት 7 ወራት ብቻ 13 ቢሊዮን ዶላር ወደ ኢትዮጵያ ማምጣት ተችሏል

• 8 ቢሊዮን ዶላር ባለፉት 7 ወራት ለግሉ ሴክተር ተሰጥቷል

• 8 አመቱን ያከበረውን የህዳሴ ግድብ እንዲቀጥል ቁርጠኛ አመራር ተሰጥቷል

• በኢትዮጵያውያን መካካል አንገት የሚቀላውን ሳይሆን የሰላም ሰይፍ በመምዘዝ ሰላምን ማስከበር ያስፈልጋል

•ለውጡ በድል ብቻ የታጀበ አይደለም፣ ኢትዮጵያውያን ሊሰሙት የማይፈልጉት መፈናቀል ተከስቷል

•ድሉን በጋራ እንዳመጣነው ሁሉ ችግሩንም በጋራ እንፈተዋለን

•አቅፎ ማለፍ ሳይሆን ጥሎ ማለፍ ላይ የተመሰረተው የሀገራችን ፖለቲካ ለለውጡ እንቅፋት እየሆነ ነው

•እኛ ሀላፊነት መውሰድ ባለመቻላችን የሚያድጉ ልጆች ተጧሪ እንዳይሆኑ ሁለም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል

•የምንሰራውና የምንነጋገረው ኢትዮጵያን ትልቅ ለማድረግ መሆን አለበት፡፡ ጉልበታች ለኢትዮጵያ ልማት አንጂ ህዝብ ለማፈናቀል መዋል የለበትም

•መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲገነዘብ የሚፈልገው አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግራይ፣ ጋምቤላ ብሎ ኢትዮጵያ ከሌለ ሙሉ መሆን አንችልም

•ሁላችንም ማወቅ ያለብን ኢትዮጵያ ለማኝ አገር ናት፤ ድንቅ ሳይንቲስት፣ አርቲስት፣ ባለሃብት ብንፈጥር የለማኝ አገር ሳይንቲስት፣ አርቲስት፣ ባለሃብት መባሉ አይቀርም

Via etv
@tsegabwolde @tijvahethiopia
የጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ሀላፊነታቸውን የተረከቡበት 1ኛ ዓመት አስመልክቶ በሚሊኒየም አዳራሽ ባደረጉት ንግግር በቀጣይ አመት ሊሰሩ የሚገቡ ስራዎችን አመላክተዋል፦

• መላው ኢትዮጵያውያን ይቅር በመባባል በጋራ ወደ ፊት እንዲጓዙ ማድረግ

• የተጀመረው ተቋማዊ ለውጥ ያልተሟላ በመሆኑ ተቋማት የመገንባት ስራ አጠናክሮ መቀጠል

• በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ሰራዎች ይሰራሉ

• በግብርና ዘርፍ በተለይም በትናንሽና መካከለኛ መስኖ ስራዎች ውጤተማ ስራዎችን ማከናወን

• የማዕድን ዘርፍ በማስፋፋት ለወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠር

• የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ፍጻሜውን ለመቋደስ ወሳኝ በመሆኑ ህግ የሚያስከብሩ እና የሚተገብሩ አካላት በጠንካራ መሰረት የሚገነቡበት ጊዜ ይሆናል

• የተፈናቀሉ ዜጎች እንዲቋቋሙ ይሰራል

• በቀጣይ አመት የሚደረገው ምርጫ ለአፍሪካ አርአያ በሆነ መልኩ የሚደረግ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ይህን አንዲጠበቁ እፈልጋለው

• የጎደለ ነገር ካለ ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብዬ ይቅርታ መጠየቅ ፈልጋለሁ

• የጎደሉ ነገሮች ባለማወቅ እና ሁኔታዎች በለመመቻቸታቸው እንጂ ዳተኛ በመሆን የተከሰቱ አይደሉም ብለዋል

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሸርማ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል፡፡ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሸርማ፣ በኢትዮጵያ ያለው አገር በቀል ሪፎርምን አድንቀው፣ አገራቸው ለኢትዮጵያ ልማት የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል፡፡

#PMO
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አህመድ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ኢትዮጵያን እንዲጉበኙ ጋበዟቸው፡፡ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚ በመሆናቸው የደስታ መግለጫ ማስተላለፋቸውን ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia