TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Ethiopia🇪🇹

" ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን በቅርበት ትከታተላለች አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ተገቢውን ምላሽ ትሰጣለች " - ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫቸው ፥ " የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎረቤት ሀገራት ልዩ ትኩረት ይሰጣል " ሲሉ ጠቁመዋል።

" ኢትዮጵያ መርህን መሠረት ያደረገ በበጎ መንፈስ የተቃኘ ዘላቂ ዲፕሎማሲ ላይ አተኩራ ትሰራለች "ም ብለዋል።

" የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናን የትርምስ ማዕከል ለማድረግ የሚደረግ እንቅስቃሴም ሊቆም ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን በቅርበት እንደምትከታተልና አስፈላጊ በሆነበት ጊዜም ተገቢውን ምላሽ እንደምትሰጥ ገልፀዋል።

አምባሳደር ነቢያት ፥
➡️ ከአውሮፓ ህብረት፣
➡️ ከአሜሪካ
➡️ ከተመድ ልዩ መልዕክተኞች ጋር ውይይቶች መካሄዳቸውን ጠቁመዋል።

" ለሁሉም መልዕክተኞች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነበት ሆኖ የኢኮኖሚ ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል " ብለዋል። #EPA

@tikvahethiopia
#ወጋገን_ባንክ

አጓጊው የሽልማት ቀን ደረሰ ‼️
ወጋገን ባንክ ባዘጋጀው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ጠቀም ባሉ አጓጊ ሽልማቶች በድጋሚ ሊያንበሸብሽዎ ነው!!

ይመልሱ በወጋገን ይሸለሙ !!

አሁኑኑ ከስር የተቀመጡትን የወጋገን ባንክ ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል እና የፌስቡክ ገፅ ሊንኮች ተጭነው በመቀላቀል እና ጥያቄዎችን አስቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ!!

ቴሌግራም || ፌስቡክ

https://publielectoral.lat/WegagenBanksc
#TechnoMobile

የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
🔈 #የወላጆችድምፅ

“ ወደ ባሕር ዳር ከተማ ልጆቻችንን ለማስመዘገብ ስንሄድ ለሚቀመጡበት ወንበር 6 ሺሕ ብር ክፈሉ እያሉን ነው ” - የተማሪ ወላጆች

“ እኔ የማውቀው ችግር የለም ” - የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ

በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ዙሪያ የሚገኙ ወላጆች በጸጥታው ችግር በአካባቢያቸው መማር ያልቻሉ ልጆቻቸውን በባህር ዳር ከተማ ከፍተኛ ትምህርት ቤቶች ለማስመዝገብ ሲሄዱ ከአቅማቸው በላይ የሆነ ገንዘብ ክፈሉ እየተባሉ መሆኑን ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የተማሪ ወላጆች በዝርዝር ምን አሉ ?

“ በጸጥታው ችግር ምክንያት በባህር ዳር ዙሪያ ያሉ ወረዳዎች ትምህርት መቀጠል አልቻሉም፡፡

ጫናውን ተቋቁመን አንጻራዊ ሰላም ወዳለበት ወደ ባህር ዳር ልጆቻችንን ለማስመዘገብ መሸኛ ይዘን ስንሄድ ተማሪዎቹ የሚቀመጡበት አንድ ወንበር ለሦስት ይዛችሁ ስትመጡ ብቻ ነው የሚመዘገቡት እያሉን ነው።

በወላጅ ተለምነው በድርድር ወደ ገንዘብ ይቀይሩታል፡፡

አንድን ሰው 2 ሺሕ ብር፣ ለአንድ ወንበር 6 ሺሕ ብር ይጠይቃሉ፡፡ ልጆቻችን በጭንቀት ውስጥ ስለሆኑ ገንዘቡን በመክፈል ምዝገባ አካሂደናል፡፡

ተማሪዎቹ ቤተሰቦቻቸው በሚገብሩት ግብር የተሰሩ ትምህርት ቤቶች ነበሯቸው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ስላልቻሉ ነው የመጡት። ከዚሁ ክልል ውስጥ ነው፡፡

ችግሩ ደግሞ የመጣው እራሳቸው መቆጣጠር ባለመቻላቸው ነው መስዋዕትነት እየከፈልን ያለነው። ችግሩን ተቋቁመን ስንሄድ አበረታትተው መቀበል ሲገባቸው ገንዘብ ያስከፍላሉ፡፡

ገንዘቡን ወንበር ይገዙበታል ወይ የሚለውም አጠያያቂ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ገንዘቡን ስንከፍል ደረሰኝ እንኳ አይሰጡንም፡፡

ክፍያውን የሚቀበሉት ለመመዝገብ የተወከሉ ሰዎች ናቸው፡፡ እንዲህ የሚደረገውም በባህር ዳር በሚገኙ ሃይስኩል ትምህርት ቤቶች ነው፡፡ ዞረን በጠየቅንባው ትምህርት ቤቶች ተመሳሳይ አሰራር ገጥሞናል፡፡

በጸጥታ ችግር መማር ሳይችሉ ከሚቀሩ አንጻራዊ ሰላም ወዳለበት አጎራባች ቦታ ሲሄዱ መባል የነበረበት ' እንኳን ደኀና መጣችሁ ' ነበር፡፡ ነገር ግን ተማሪዎቹ ሲሄዱ ሌላ ጫና እየተፈጠረ ነው፡፡

የወንበር ችግር ገጥሟቸውም አይመስለንም፡፡ ወላጅ ላይ የተለዬ ምሬትና ጫና ከመፍጠር በመተዛዘን ተማሪዎቹን ቢያስተናግዷቸው መልካም ነው፡፡ ገንዘቡን መክፈል ያልቻሉ መመዘገብ አልቻሉም። ” ብለዋል።

ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያን ጠይቋል።

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አንድ ኃላፊ በሰጡት ቃል፣ “ ባሕር ዳር ዙሪያ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሊመዘገብ መጥቶ ሁሉም ትምህርት ቤት ጋር ' ለሦስት፤ ለሦስት አንድ ወንበር አምጡ ወይም ወንበር ይዛችሁ ካልመጣችሁ አላስተናግድም ' ያለ ትምህርት ቤት የለም። ” ብለዋል።

“ እኛ ጋ ' ችግር ደረሰብኝ ' ብሎ የመጣም የለም፡፡ ' ወንበር አምጣ ተብያለሁ ' ብሎ መጥቶ የጠየቀኝ ተማሪም የለም፡፡ ሁሉንም ትምህርት ቤት እየዞርኩ እያየሁ ነው፡፡ የትኛውም ትምህርት ቤት ላይ እየተመዘገቡ ነው። ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ አልፎ አልፎ አንመዘግብም ያሏቸውን እራሴ እየመራሁ ነው ያስመዘገብኳቸው፡፡ ትምህርት ቤቱ የማህበረሰብ ተሳትፎ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ ግን አግሪመንት ወስዶ ማህበረሰቡ የፈረመውን ነው እያስከፈለ ያለው። ” ሲሉ አክለዋል።

“ እኔ የማውቀው ችግር የለም ” ያለው ትምህርት መምሪያው፣ እንዲህ የሚያደርጉ ትምህርት ቤቶች ካሉ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ቢያሳውቁት ታች ድረስ ወርዶ እርማት እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

ወላጆች መሰል ችግር ያለባቸውን ቦታዎች ለትምህርት መምሪያ መጠቆም እንደሚችሉ ተመላክቷል።

#TikvahethiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል።

ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል።

" ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል።

" በጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን የዜጎችን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደርገ ነው " ብለው ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ተናግረዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥንቃቄ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል። ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል። " ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል። "…
🔈#ይነበብ

(በድጋሚ የተለጠፈ)

ወጣቶችን ወስደው ምንድነው የሚያሰሯቸው ?

በኦንላይን ወይም በደላሎች አልያም በኤጀንሲዎች " እዚህ ሀገር ጥሩ ስራ አለ ፤ ክፍያውም ከፍ ያለነው " ተብለው ብዙ ወጣቶች ከተለያዩ ሀገራት ይዘዋወራሉ።

ለአብነት ያህል ወጣቶች ከሚዘዋወሩባቸው ሀገራት መካከል የሳይበር ማጭበበር ( Cyber Scam) ማዕከላት ተብለው ወደ ሚታወቁት ፦
• ማይናማር ፣
• ካምቦዲያ፣
• ላኦስ
• ማይናማር ታይላንድ ድንበር
• ቻይና ማይናማር ድንበር በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ አካባቢዎች ባሉ የተለያዩ ቦታዎች በኦንላይን ማጭበርበር ላይ የተሰማሩ በርካታ ድርጅቶች አሉ።

በእርግጥ መጀመሪያ ላይ ወጣቶቹን " እልካችኋለን " የሚሏቸው ሌሎች በኢኮኖሚና ደህንነት እጅግ ጠንካራ ፣ ጠንካራ ባይሆኑም እንኳን ያን ያህል የከፋ ሁኔታ ላይ ወደማይገኙ ሀገራት ነው።

እዛ ቦታ ከደረሱ በኋላ ግን የሚልኳቸው ወደ ጎረቤት ድሃ እና የህግ ስርዓት ወዳልጠነከረባቸው ሀገራት ይሆናል።

የሚሰራው ማጭበርበር ምንድነው ?

ስራ ብለው የሚልኳቸው መጀመሪያ ፦
- የኦላንይ ግብይት ስራ ማቀላጠፍ
- የኦንላይን ሴልስ ስራ
- የሆቴል እንግዳ ተቀባይ
- የማርኬቲንግ ስራ ... ሌላም ሌላም ነው።

ነገር ግን ስራ አለበት ወደ ተባለው ስፍራ ሲሄዱ የሚሰሩት ስራ መጀመሪያ ላይ ከተነገራቸው ተቃራኒ ነው።

የየራሳቸው ጋንግ አለቆች ባላቸው እጃቸውም ረጅም በሆኑ ሰዎች በሚመሩ የማጨበርበር ተግባር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች ያስገቧቸዋል።

እነዚህ ሰዎች ስልክ / ኮምፒየተር የሚያቀርቡላቸው ሲሆን በዛም ዓለም አቀፍ የማጨበርበር ስራ ላይ ያሰማሯቸዋል።

🔴 ዴቲንግ 🔴

የመጀመሪያ ስራቸው ከኢንተርኔት ላይ ውብ የሆኑ ሴቶችን / ስኬታማ ሴቶችን / ስኬታማ ወንዶችን ታዋቂ ሰዎችን ፎቶ በማውረድ የውሸት አካውንት መክፈት ነው።

በመቀጠል የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ። ምናልባትም በቅርብ የሚያውቋቸውን ሰዎችንም ሊሆን ይችላል።

እነዛን ሰዎች ልክ እንደ ኖርማል ሆነው ያለ ማቋረጥ ጊዜ ወስደው ያናግሯቸዋል።

የትኛውንም ጊዜ ይፍጅ ማናገራቸውን ይቀጥላሉ።

ስለ ውሸት ስራቸው፣ ስለ ህይወታቸው እየፈጠሩ ያወራሉ። በዚህ ውስጥ ምንም ምልክት አያሳዩም።

ወደ ፍቅር ከወሰዷቸውና ከጣሏቸው እምነትም ካገኙ በኃላ መጨረሻው ወደሆነው ዓላማቸው ገንዘብ ማስላክ ይገባሉ።

" ለምን እኔ ምሰራው ስራ ላይ ኢንቨስት አታደርም / አታደርጊም " በማለት ለምሳሌ ክሪፕቶ  ላይ ብለው ገንዘብ ይቀበላሉ።

በቃ አለቀ ! ገንዘባችሁ ተበልቶ ይቀራል። በኃላም ብሎክ አድርገው ይሸኟችኋል። ቀጣይ ሌላ ሰው ታርጌት ያደርጋሉ።

ወጣቶቹ ይሄን ካላደረጉ ምናልባትም ኢ-ሰብአዊ ቅጣት ሊፈጸምባቸው ይችላል።

⚫️ በጎ አድራጎት ⚫️

የውሸት ማንነት ፎቶ ተጠቅመው አካውንት ከፍተው (ሴትን በወንድ ወንድ ደግሞ በሴት ማንነት) አንድ ታርጌት ያደረጉትን ሰው ረጅም ጊዜ ያናግሩ እና ለእርዳታ / ለእርዳታ ድርጅታቸው ገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያሳምኗቸኣል።

እነዛ ሰዎች ላይ እምነት የጣሉባቸው ተጨበርባሪዎች በሀዘን ተሰብረው ገንዘባቸውን ይልካሉ። ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ይደረጋሉ።

🟡 ባለሃብት መምሰል 🟡

የውሸት ማንነት በመፍጠር ፣ ፎቶዎችን በመጠቀም በኦንላይን ሰው ያናግራሉ።

እንዲታመኑ ረጅም ጊዜ ሊወስዱም ይችላሉ።

ሰዎቹ ካመኗቸው በኃላ ገንዘባቸውን በጋራ አፍስሰው ስለሚሰሯቸው ስራዎች በማናገር ገንዘብ ያስልካሉ። ከዛማ ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ያደረጋሉ !

🟤 ደንበኞችን ማነጋገር 🟤

ይህም በተመሳሳይ በሀሰተኛ ማንነትና ስራ ከተለያዩ ሰዎች እያነጋገሩ በማጭበርበር ገንዘብ መቀበል ነው።

ለምሳሌ ፦ እቃ የሚሸጡ አስመስለው ብር ካስላኩ በኋላ የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ።

🔵 ' ኮሜንት/ሬት በማድረግ ገንዘብ አግኙ ' 🔵

እነዚ አጭበርባሪዎቹ የውሸት ማንነት ተጠቅመው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ ወይም በሌላ መንገድ ተጠቅመው የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ።

" ጎግል ላይ ግቡና ስለዚህ ድርጅት ጥሩ አስተያየት ጻፉ ይከፈላችኋል " ይላቸዋል።

ከዛም የመጀመሪያውን ክፍያ በመፈጸም እምነት ያሳድራሉ።

" ይሄን ያህል ብር ከላካችሁ ይሄን ያህል ታገኛላቹ " በማለት የሰዎቹን ማንነት ይገመግማሉ። እስከዛ ድረስ ግን ገንዘብ መላካቸውን አያቆሙም።

የሚጭበረበረው ሰው ብዙ ብር ካስላኩት በኋላ የውሃ ሽታ ይሆናሉ።


በተጨማሪም ...

እንደ ፖሊስ፣ደህንነት፣ ባንክ ሰራተኛ ፣ እንደ ድርጅት ኃላፊ ሆነው የሚያስመስሉ አጭበርባሪዎችም አሉ።

ስራውን የሚሰሩት ሰዎችም ተጠቂዎች ናቸው።

ስራውን ካልሰሩ አሰቃቂ ጥቃት ሊደርስባቸው ይችላል።

እንደ ባሪያ ለረጅም ሰአትም ያሰሯቸዋል።

እንደ ቅርብ ጊዜ ሪፖርት ፥ በማይናማር፣ ካምቦዲያ፣ ላኦስ፣ ቻይና በመሳሰሉ ሀገራት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች በኦንላይ ማጭበርበር ላይ ተሰማርተዋል።

ስራዎቹንም የሚያሰሯቸው ሰዎች እጃቸው በጣም ረጅም ነው።

#TikvahEthiopia
#CyberScam

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
24 - ሰዓት የሚሰሩ ሁለት ቅርንጫፎች እንዳሉን ያውቃሉ ?

ሕብረት ባንክ በስካይ ላይት ሆቴል ውስጥ ስካይ ላይት ንዑስ ቅርንጫፍ እንዲሁም በሒልተን ሆቴል ውስጥ ሒልተን ቅርንጫፍ ላይ የ24 ሰዓት የተሟላ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ በእነዚህ ቅርንጫፎቻችን ለሊቱም ቀን ነው!

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!


ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡ አዳዲስ መረጃ እንዲደርሶ የሚከተሉትን የማህበራዊ ገፆቻችንን ይቀላቀሉ፡፡
               ቴሌግራም-  https://publielectoral.lat/HibretBanket
            linktr.ee/Hibret.Bank

   
#Hibretbank
Hey Mobile !

Tab A9 - 19,500 ETB
•Tab A8 - 29,500 ETB
•Tab A9+ 5G - 31,000 ETB
•Tab S6 Lite - 47,000 ETB
•Tab S9 FE - 59,000 ETB
•Tab S9 +5G - 99,000 ETB
•Tab S9 Ultra - 129,000 ETB

Contact us :
0936222222 @heymobile1
0925927457 @eBRO4

@Heyonlinemarket
በአዲስ አበባ ለብዙሃን ትራንስፖርት ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ መስመሮች ይፋ ሆኑ።

ከትምህርት ቤቶች መከፈት ጋር ተያይዞ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ከመጪው እሑድ ጀምሮ በተመረጡ መስመሮች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

መስመሮቹም ከቦሌ- ፒያሳ፣ ከቦሌ- ሜክሲኮ፣ ከቦሌ- አራት ኪሎ፣ ከቦሌ- አውቶቢስ ተራ፣ ከቦሌ- ሽሮሜዳ፣ ከጀሞ- ፒያሳ እና ከጀሞ- ሜክሲኮ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

በተመሳሳይ ከፒያሳ- ቦሌ፣ ከሜክሲኮ- ቦሌ፣ ከአራት ኪሎ- ቦሌ፣ ከአውቶቡስ ተራ- ቦሌ፣ ከሽሮ ሜዳ- ቦሌ፣ ከፒያሳ ጀሞ እና ከሜክሲኮ - ጀሞ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ብቻ መሰጠት እንደሚጀምር ተመላክቷል፡፡

ቢሮው " የአገልግሎቱ መጀመር የመንገድ መዘጋጋቱን ለመቀነስ እና ብዙ የሰው ቁጥር ያለው ተጓዥ በአንድ ጊዜ ማመላለስ ያስችላል " ብሏል።

በዚህም ተማሪና መምህራን ብሎም ሌሎች ተገልጋዮች በሰዓታቸው ወደ ሚፈልጉት ቦታ በመንቀሳቀስ አገልግሎት እንዲያገኙ ያግዛል ተብሏል፡፡

" በከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው የተነቃቃ እንዲሆን ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል " ሲልም አክሏል።

ዜጎች የሚያጋጥሟቸውንና የሚስተዋሉ ችግሮችን በአቅራቢያ ለሚገኙ የትራንስፖርት ቁጥጥር ሰራተኞች ወይም በ9417 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል፡፡

@tikvahethiopia
" ወደ ፖለቲካ ፈጽሞ መመለስ አልፈልግም ! " - የእናት ፓርቲው አቶ ዳዊት ብርሃኑ

የእናት ፓርቲ አባል፣ አመራርና የሕዝብ ግንኙነት ሆነው ያገለገሉት አቶ ዳዊት ብርሃኑ ከዛሬ (መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ/ም) ጀምሮ በፈቃዳቸው ሥራ መልቀቃቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" በተለይም ፓርቲው አንደኛ መደበኛ ጉባኤውን መጋቢት 30 ቀን 2015  ዓ/ም ባከናወነበት ወቅት በጠቅላላ ጉባኤው በሕዝብ ግንኙነት ከተመረጥኩ በኋላ የተሰጠኝን ኃላፊነት በአግባቡ ስወጣ ቆይቻለሁ " ብለዋል።

" በትብብር ፓርቲዎችም ዘንድ ባለኝ የፀሐፊነት ሚና የበኩሌን ድርሻ ስወጣ ነበር " ነው ያሉት።

" ምንም እንኳ ፓርቲው ከተመሠረተ ያስቆጠረው እድሜ አጭር ቢሆንም የቆየሁባቸው አራት አመታት በሀሳብ ልዕልና እና በሰለጠነ የሀሳብ ጉርብትና ብቻ ፖለቲካ መስራት የሚችሉ አባላትን ያፈራንበትም ወቅት ነበር " ሲሉም አክለዋል።

ከፓርቲው የለቀቁት በምን ምክንያት ነው? በሥራ? ባለመግባባት? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በምላሻቸው፣ " ከፓርቲው የለቀቁት በግል ውሳኔ ነው " ብለዋል።

በተለይ የፓለቲካ ምህዳሩ እንደ ጠበበ በሚገለጽበት በአሁን ወቅት በፓርቲ ሥራ ውስጥ መቆዬት ተግዳሮቱ ምንድን ነው ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ፣ " ከባድ ነው። የአገርና ሕዝብን አደራ መሸከም እጅግ በጣም ከባድ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ተፎካካሪ ፓርቲዎችና ገዢው ብልጽግና ለሻከረ ግንኙነታቸው መፍትሄው ምንድነው ይላሉ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ምላቸው፣ " ሀቀኛ፣ ሁሉን አቀፍ፣ በአግባቡ የሚመራና ግልጽ የሆነ የፓለቲካ ድርድር ማድረግ " የሚል ነው።

የፓርቲ የሕዝብ ግንኙት አገልግሎትዎ ምን ይመስል ነበር? ለሚለው ጥያቄ ደግሞ፣ " አስቸጋሪ፣ ፈታኝ እንዲሁም ከፊል ስኬታማ ነበር " ብለዋል።

ካሁን ወዲያ በሌላ ፓርቲ እንጠብቀዎት ወይስ በፓርቲ ሥራ እስከወዲያኛው እየወጡ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ "ወደ ፓለቲካ ፈጽሞ መመለስ አልፈልግም" ነው ያሉት።

እናት ፓርቲ ለወደፊት ምን ያስተካክል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ አቶ ዳዊት አጭር ምላሻቸው፣ "መሠረቱን" የሚል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
🔥 ዘመናዊ የእጅ ስልክ ከ1 ዓመት የጥቅል ስጦታ ጋር!!

የጎግል መተግበሪያዎች የተጫኑባቸውን አዳዲሶቹን የ #ZTE_Nubia_Music ዘመናዊ የእጅ ስልኮች በተመጣጣኝ ዋጋ ሲገዙ

▶️ የ2 ጊ.ባ ወርኃዊ የዩትዩብ ጥቅል ለአንድ ዓመት እንዲሁም

🌐+📞 ለ3 ተከታታይ ወራት 3 ጊ.ባ የዳታና 200 ደቂቃ የድምጽ ጥቅል በስጦታ ያገኛሉ!

📍 በአገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን እንዲሁም የአዲስ አበባ ደንበኞቻችን በቴሌገበያ ድረገጽ https://telegebeya.ethiotelecom.et/ መግዛት ትችላላችሁ!


#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#ONLF #SOMALIREGION

ከሰሞኑን ተቃዋሚው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ' የሶማሌ ክልል የዜጎች መብት የሚጣስበት እየሆነ ነው " ሲል ከሷል።

ፓርቲው ክልሉ ሶማሌዎች ማንነታቸውን እንዲክዱ የሚገደዱበት እየሆነ ነው ብሏል።

የክልሉን ስያሜና ሰንደቀላማ የመቀየር እቅድ እንዳለ ከአሉባልታ ከፍ ያለ መረጃ አለን ሲሉም፣ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አብዲራህማን መሀዲ ተናግረዋል።

ባለፉት 6 አመታት በክልሉ የጎሳ ግጭቶች ጨምረዋል ሲሉም ወቀሳ አቅርበዋል።

የክልሉ ርዕሰመስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ በበኩላቸው፣ የክልሉ የሀገር ሽማግሌዎች " እኛ ሶማሌዎች እንጂ ሶማሊያውያን አይደለንም " ማለታቸው ማንነትን እንደመካድ ሊወሰድባቸው አይገባም ብለዋል።

በቀድሞው አስተዳደር ህግን ባልተከተለ መንገድ ተቀይሮ የነበረውን ስያሜና ሰንደቅ አላማ በመተው በህገመንግስቱ የተቀመጠውን ስያሜ መጠቀም የጀመረው የእርሳቸው አስተዳደር መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ሙስጠፋ የኦብነግ ሊቀመንበር የሚመሩት ቡድን ይህንን መግለጫ ያወጣው በክልሉ ችግር ስላለ ሳይሆን " ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ እየተስተዋለ ያለውን ጂኦፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ ጥቅም በመፈለግ ነው " ሲሉ ተችተዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#Tigray

አዲሱ የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሁለት የዞን ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነታቸው አነሱ።

በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ገ/ክርስቶስ  ፊርማ መስከረም 8/ 2017  ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው የዞኑ የመንግስታዊ አገልግሎት ዘርፍና የልማታዊ ዘርፍ አግልግሎት ሃላፊዎች ከስራ ተነስተዋል።

ለሃላፊዎቹ ከዞኑ መንግስታዊ የስራ ሃላፊነት መነሳት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራዎች አልፈፅምም ማለትና ማደናቀፍ እንደ ምክንያት ተጠቅሰዋል።

ሁለቱ የዞን የስራ ሃላፊዎች ከመስከረም 8/2017 ዓ.ም ከነበራቸው የስራ ሃላፊነታቸው ተሰናብተው የተሰጣቸው የመንግስት ንብረትና ስራ እንዲያስረክቡ በተፃፉላቸው የስንብት ደብዳቤዎች ተገልፆላቸዋል።

አቶ ፀጋይ ገ/ተኽለ ገ/ክርስቶስ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት በቅርቡ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው የተመረጡት ወ/ሮ ሊያ ካሳ ተክተው  የደቡብ ምስራቅ ዞን ዋና  አስተዳዳሪነት እንዲመሩ በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተሾሙ ናቸው። 

በተመሳሳይ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት መስከረም 6/2917 ዓ.ም " ከአባላትና ከድርጅታዊ ሃላፊነት አባርሪያቸዋለሁ " ብሎ ደብዳቤ የፃፈላቸው የህወሓት ማእካላዊ ኮሚቴ አባልና የትግራይ ማእከላይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሙን መዓሾ የአክሱም ከተማ የፀጥታ ሃላፊ ፣  የተምቤን ዓብዩ ዓዲ ከተማ ከንቲባና ሁለት የዞን የስራ ሃላፊዎች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ በማደናቀፍ በሚል ከሃላፊነታቸው ማንሳታቸው መዘገባችን ይታወሳል።  

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" እስክንወያይ ድረስ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ባለበት ይቀጥላል " - ትራንስፖርት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከትምህርት ቤቶች መከፈት ጋር ተያይዞ " የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር " በሚል የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ከመጪው እሑድ ጀምሮ በተመረጡ መስመሮች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቆ ነበር።

መስመሮቹም ከቦሌ- ፒያሳ፣ ከቦሌ- ሜክሲኮ፣ ከቦሌ- አራት ኪሎ፣ ከቦሌ- አውቶቢስ ተራ፣ ከቦሌ- ሽሮሜዳ፣ ከጀሞ- ፒያሳ እና ከጀሞ- ሜክሲኮ እንደሆነ ተመላክቶ ነበር።

በተመሳሳይ  ከፒያሳ- ቦሌ፣ ከሜክሲኮ- ቦሌ፣ ከአራት ኪሎ- ቦሌ፣ ከአውቶቡስ ተራ- ቦሌ፣ ከሽሮ ሜዳ- ቦሌ፣ ከፒያሳ ጀሞ እና ከሜክሲኮ - ጀሞ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ብቻ መሰጠት እንደሚጀምር ተገልጾ ነበር።

ቢሮው " የአገልግሎቱ መጀመር የመንገድ መዘጋጋቱን ለመቀነስ እና ብዙ የሰው ቁጥር ያለው ተጓዥ በአንድ ጊዜ ማመላለስ ያስችላል " ነበር ያለው።

ይህን ውሳኔ ለሚዲያ ካሰራጨ በኃላ ሰዓታት ሳይቆይ ውሳኔውን በመሻር " ትራንስፖርት ባለበት ይቀጥላል " ብሏል።

ቢሮው " በቀጣይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር እስክንወያይ ድረስ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ባለበት የቀጥላል " ሲል ነው ያሳወቀው።

@tikvahethiopia