TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ከተያዘው እቅድ ውጭ እኛ የማናቀውን ስብሰባ ማካሄድ አይቻልም " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር

በትግራይ ክልል ፣ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጊዚያዊ አስተዳደሩ የማያውቀው ማንኛውም ሰብሰባ ማካሄድ የሚከልክል የስራ መመሪያ ይፋ ተደረገ።

ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፅህፈት ቤት በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፊርማ ለሁሉም
-  የዞን አስተዳደሮች
- ለወረዳ አስተዳደሮች
- የክፍለ ከተማ አስተዳደሮችና
- የወረዳ ምክር ቤቶች 
የተላከው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፈቀደው ውጪ ሌላ ስብሰባ ማካሄድ አይቻልም ይላል።

➡️ የኮሌራ በሽታ መከላከል
➡️ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስና የክልሉን ግዛታዊ አንድነት ማስከበር
➡️ የ2016 ዓ.ም በጀት መዝጋትና የ2017 ዓ.ም በጀት ማዘጋጀት ... ሌሎች ህዝባዊና መንግስታዊ እቅዶች የጊዚያዊ አስተዳደሩ መሆናቸው የጠቀሰው የስራ መመሪያው ፤ " ከዚህ ውጪ የሚደረጉ ሰብሰባዎች የተያዘው እቅድ ስለሚጎዱ አይፈቀዱም " ብሏል።

ከላይ ከተጠቀሱት እቅዶች ውጪ ማሰተናገድ የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስራ በማደናቀፍ #ተጠያቂነት_የሚያስከተል መሆኑን  በመግለጽ አስጠንቅቋል።

የሚመለከታቸው የመንግስት አካላትም ይህኑን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጥብቅ መመሪያ ሰጥቷል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF #Tigray የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ። አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት ቡድን " አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም ” ብለዋል። ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም…
#Tigray

የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ።

ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጡ አደራ በማለት ያሳስባል።

አዲሱ ተሿሚ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ኽርስቶስ ቀደም ሲል በዞኑ የእንደርታ ወረዳ አስተዳዳሪ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል። 

ወ/ሮ ሊያ ከቀናት በፊት የህወሓት ስራ አስፈጻሚ በመሆን መመረጣቸው ይታወሳል።

ህወሓት ባካሄደው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ያልሰጠው ፤ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን " ህጋዊ አይደለም " ያሉት ጉባኤ ካልተሳተፉት መካከል  ፦
- የምዕራባዊ
- የማእከላዊ
- የምስራቃዊ
- የደቡበዊ ዞኖች አስተዳዳሪዎች ይገኙበታል። 

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው የስልጣን ሹምሽር ያደረጉበት የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ኣስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው የተሸሙት ወ/ሮ ሊያ ካሳ የተኩት አምስተኛ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ የሚቃወሙ የዞን አስተዳዳሪ ናቸው።

በትግራይ ካሉ 7 የዞን አስተዳደሮች አምስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ ሁለት ዞኖች ማለትም የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በተካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት  ተኽላይ ገ/መድህን የመቐለ ከተማ ደግሞ በተካሄደው ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይትባረክ ኣማሃና ኤልያስ ካሕሳይ ዋናና ምክትል በመሆን በመመራት ላይ ይገኛሉ።

ቀሪዎቹ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን አካሄድ የሚደግፉ የሁለት ዞን አስተዳዳሪዎች በያዙት ሃላፊነት የቆዩ ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው። 

የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከቀናት በፊት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ ተናግረው ነበር።

ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም " ነበር ያሉት።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ። ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል። በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ…
#TPLF #Tigray

በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ።

በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል።

የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ ፥ " ከሰርዓታዊና ተቋማዊ አሰራር ውጪ የሚካሄዱ የስራ ምደባዎች ኢህጋዊ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂነትን ያስከትላሉ " ሲል አስጠንቅቋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ መሾማቸው ዘግበናል።

ነሃሴ 18/2016 ዓ.ም የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዋና አስተዳዳሪና በቅርቡ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተክላይ ገ/መድህን ምትክ የክልሉ የስፓርት ኮሚሽን ኮምሽነር የነበሩት ተኽላይ ፍቓዱ ተሹመዋል።

ትግራይ ካሉዋት ሰባት የዞን አስተዳደሮች በአሁኑ ጊዜ ስድስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ የመቐለ ከተማ ብቻ በቅርቡ  በተካሄደ ጉባኤ  የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይመራል። 

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF #Tigray በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ። በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል። የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ…
#Tigray

" በቅርቡ ሁሉም ተቀባይነት ያላቸው ህጎችና አሰራሮች በመጣስ ጉባኤ አድርጊያሎህ የሚለው ህገ-ወጥ ቡድን በትግራይ ስርአት አልበኝነት እንዲስፋፋ እየሰራ ነው " ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከሷል።

አስተዳደሩ ፥ ህዝብ ለማገልገል የሚያካሂዳቸው የመዋቅራዊ አደረጃጀት ማስተካከያዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የመንግስት ውሳኔና ተግባር የሚያደናቅፍ ማንኛውም አካል ሆነ ሃይል አልታገስም ብሏል።

" ህግና ስርዓት የሚጥስ አካል ሆነ ሃይል ህጋዊ አሰራር የተከተለ ተጠያቂነትና እርምጃ እንደሚወሰድበት ሊታወቅ ይገባል " ሲል አስጠንቅቋል።

በአሁኑ ወቅት ማንኛውም የስልጣን ጥያቄ አለኝ የሚል ቡድን በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ጠያቄውን ለሚመለከተው አደራዳሪ አካል   በሰላማዊ አግባብ የማቅረብ መብቱ ዝግ እንዳልሆነ ጠቁሟል።

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንዲዳከም ሳያለሰልስ የሰራ ቡድን አሁን የሚደረጉት የስራ ምደባዎች ' ህጋዊ አይደሉም ' ብሎ በመቃወም ለዓመታት እስከ ታች በሰፋው ኔትወርክ እንቅፋት እየፈጠረ ይገኛል " ብሏል።

" ቡድኑ በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተመደቡ አመራሮች ህጋዊ አይደሉም ተቀባይነት የላቸውም ' ከማለት አልፎ ባደራጀው ኔትወርክ እስከ ቀበሌ መዋቅር ድረስ በመውረድ ' እንዳትቀበሉዋቸው ' በማለት ህግ አልበኝነት እንዲነግስ በመንቀሳቀስ ላይ ነው " ሲል ከሷል።

" ህዝቡ ህገ-ወጥቶች ሃይ ሊላቸው ሊያስታግሳቸው ይገባል " ሲል አስገንዝቧክ።  

" ህዝቡ ተገቢውን  መንግስታዊ አገልግሎት እንዲያገኝ አልሞ የሚከናወነው የመዋቅር ማስተካከያ እርምጃ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ፤ መንግስታዊ የመዋቅር ማስተካከያ እርምጃ በሚቃደናቅፍ አካል ሆነ ሃይል እርምጃ እንደሚወሰድ ህዝባችን ሊያውቀው ይገባል "  ሲል በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራስ ጊዜዊ አስተዳደር አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 
#Tigray

ዛሬ በአክሱም ከተማ የብዙዎች መነጋገሪየ የሆነ ፓለቲካዊ ክስተት ተከስቷል።

በመካከላቸው በተፈጠረው ፓለቲካዊ ልዩነት በርቀት በመግለጫዎች ሲጎነታተሉ የከረሙት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በዓመታዊው አክሱም ከተማ የዓይኒ ዋሪ በዓል አከባበር ላይ ተገናኝተዋል።

በመድረኩ በቅደም ተከተል ንግግር ያደረጉት ሁለቱ መሪዎች ከምር ይሁን ከአንገት በላይ በማይታወቅ የእጅ ሰላምታ ተጨባብጠዋል።

ከአክሱም ከተማ የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከንግግራቸው በላይ አነጋገሪ የሆነው " በዓሉ ላይ እኔ ነኝ መገኘትና መሳተፍ ያለብኝ " የሚል ክርክርና ሰጣ ገባ መነሳቱ ነው።

ክርክርና ሰጣ ገባቸው የሃይማኖት አባቶች መሃል ገብተው አስማምተው ሁለቱም በመድረኩ እንዲገኙና ንግግር እንዲያደርጉ ለማሳመን የወሰደው ጊዜ ፕሮግራሙ ሳይጀመር ለሰዓታት እንዲራዘም ሆኗል።

ሁለቱ መሪዎች ያደረጉት ሰጣ ገባ ደጋፊዎቻቸው ደረስ ዘልቆ እስከ አሁን ድረስ በማህበራዊ የትስስር ገፆ እያከራከረ ይገኛል።

ቀድመው ንግግር ያደረጉት ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ድርጅታቸው በቅርቡ ባካሄደው 14ኛው ጉባኤ ያሳለፋቸው ውሳኔዎችና አተገባበራቸው ያተኮረ ሲሆን ቀጥለው የተናገሩት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በንግግራቸው የጊዚያዊ  አስተዳደሩ የስራ አቅዶችና አንድነትን የሚመለከት ነበር። 

ፕሬዜዳንት ጌታቸው በስም ያልገለፁዋቸው " የውጭ  ጠላቶች " የሚያደርጉት ሙከራ ከትግራይ አቅም በላይ አይደለም ፤ ስለሆነም ከጨለማ ለመውጣት በአንድነት መጓዝ አለብን ብለዋል።

ለሦስት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ትግራይ የነበሩት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በህወሓትና በጊዚያዊ አስተዳደሩ መካከል የተፈጠረው ውጥረት መርገብ እንዳለበት ማሳሰባቸው መዘገባችን ይታወሳል። 

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

" በችግር ላይ ሌላ ችግር  በህዝቡ ላይ የመጫን ፍላጎት የለንም ፤ አሁን የገጠመን ፈተና እናልፈዋለን። አባቶች በፀሎትና ምክር አግዙን !! " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)

የህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ/ም ከአበው ጳጳሳት እና የአገር ሽማግሌዎች ጋር በኣክሱም ከተማ መወያየታቸውን የሚገልጽና አንድ ንግግር ሲያደርጉ የሚታይበት ቪድዮ ተሰራጭቷል።

ቪድዮው በትግራይ ፐብሊክ ሚዲያ (TPM) የማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ነው የተሰራጨው።

ሊቀመንበሩ የ5 ደቂቃ ርዝማኔ ባለው ንግግራቸው  ፥ " እኔ ለድርጅትና ለህዝብ ደህንነት ስል ብዙ ታግሻለሁ ፤ ትዕግስትና ዝምታዬ ግን መልካም ነገር ሳይሆን አደጋ ነው ያስከተለው ፤ ስለሆነም ከአሁን በኋላ መታገስ ሳይሆን ተመጣጣኝ ሰላማዊ ትግል ነው የሚያዋጣው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" እኛ የውጭ ጠላት አለብን የውስጥ ጉዳይ አናቆየው በማለታችን በውስጣችን ብዙ ችግሮች እንዲፈጠሩ ሆኗል " ያሉት ደብረፅዮን (ዶ/ር) ፥ " ከአሁን በኋላ የጎራ መደበላለቅ አይኖርም አቋማችን በግልፅ በማንፀባረቅ ሰላማዊ ትግል ማካሄዳችን እንቀጥላለን " ብለዋል።

" በሃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ የሚል አካል ሃይ ሊባል ይገባዋል ፥ በትግራይ በጉልበት እሰራለሁ ማለት አያዋጣም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከአሁን በኋላ ከህዝብ የሚደበቅ ሚስጥር አይኖርም " በማለትም ተናግረዋል።

ሊቀመንበሩ ፤ " የተፈጠረውን ልዩነት በሰላም እንጨርሰው ፤ የማይሳካ ከሆነ ግን ሉአላዊነታችንን አሳልፈን አንሰጥም ፤ አቋማችን ግልፅ በማድረግ እንታገላለን " ብለዋል።

" አንድ በማያደርገን አንድ ሁኑ አትበሉን  በፓለቲካ አንድ በማያደርግህ አቋም አንድ መሆን አይቻልም ፤ ተከባብሮ በሰላም መስራት ግን ይቻላል ፤ ትግራይ ለሁሉም በቂ ናት " ሲሉም ደብረጽዮን (ዶ/ር) አክለዋል።

ህዝቡ ላይ በችግር ላይ ሌላ ችግር መጫን  እንደማይፈልጉ የተናገሩት ሊቀመንበሩ ፥ የተፈጠረው ሁኔታ ተስፋ የሚያስቆርጥ እንዳልሆነና በሰላማዊ አግባብ እንደሚፈታ በማመላከት የሃይማኖት አባቶች በፀሎትና በምክር እንዲረዱዋቸው ጠይቀዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ #TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TIGRAY

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በዓዲግራት ምን አሉ ?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና ከተማ ዓዲግራት ህዝባዊ ውይይት አካሂደዋል።

" ህዝቡ ስጋት ላይ የሚጥል ሁኔታ ለመቅረፍ ከናንተ መሃል ተገናኝተናል " ብለዋል።

" የትግራይ መልሶ ግንባታ ጋሃድ እንዲሆን በመደጋገፍ መስራት ይገባናል " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" በውስጣች በተፈጠረው መፎካከር መስራት የሚገቡን አልሰራንም " ያሉት አቶ ጌታቸው " አብዛኛው ጊዚያችን በጭቅጭቅና በጎሪጥ በመተያየት ነው ያሳለፍነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በማህበራዊ አገልግሎት መልሶ ግንባታ ጥሩ እንቅስቃሴ አድርገናል ፤ ጅምሮቻችን ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በውስጣችን የታዩ ድክመቶችን ማረምና የጋራ መፍትሄ ለመሻት መስራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።

" በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ሁሉም በጠላት ስር የሚገኙ አከባቢዎች  ወደ ነባር አስተዳደራቸው መመለስ አለባቸው ብለን እየሰራን ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " የሰላም ስምምነቱ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እንደ መንግስት ጠንክረን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።

" የህዝባችን ሰላም በማረጋገጥ በኩል ዓለም ከኛ ጋር ናት ይህንን እንዲቀጥል ግን ውስጣዊ አንድነታችን እንዳይላላ ያለማቋረጥ መስራት አለብንም " ብለዋል።

በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዓዲግራት ሲደርሱ በልዩ አጀብ በፈረሰኞች የተደገፈ አቀባበል ነበር የተደረገላቸው።

በአቀባበሉ የተገኙ የዓዲግራት ከተማ ወጣቶች ፦
👉 የጥይት ድምፅ እንጠየፍ !! 
👉 መሰረታዊ ለውጥ እንፈልጋለን !!" 
👉 ተፈናቃዮች ይመለሱ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
👉 ትግራይ በሳይንስና ጥበብ እንጂ በጥይት አፈሙዝ አትመራም !!
👉 ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደግፋለን !!
የሚሉና ልሎች መፈክሮች በመያዝ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በተመራ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ቡድን ምክትል ፕሬዜዳንት ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ነበሩበት።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ምን አሉ ?

የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩትና ም/ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ የሚገኙበት የአመራሮች ቡድን ከሰሞኑን ህዝባዊ ውይይቶችን እያደረገ ነው።

ትላንት ማይጨው ላይ በነበረ ውይይት ጀነራል ፃድቃን ስለ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዙሪያ ሃሳቦች ሰጥተዋል።

" የሚታየውን ዋናው የልዩነት ነጥብ በፕሪቶሪያ ውል ላይ ያለ የአመለካለት ልዩነት ነው " ብለዋል።

" ስምምነቱ ዓለም አቀፍ ውል ነው መከበር አለበት " ሲሉም በቅርቡ እኔ ነኝ ህጋዊ ህወሓት የሚለው የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል ሲሸነቆጥ አድርገዋል።

ፕሬዜዳንቱ ጌታቸው ረዳ ደግሞ ሃሳቡ አጠናክረዋል።

"  የፕሪቶሪያ ውል ለማፍረስ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ጦርነትን መጥራት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል " በማለት አስጠንቅቀዋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንትና ምክትላቸው በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትና አመለካከትና አተገባበር  ዙሪያ የሰነዙሩዋቸው ጥንካራ ትችቶች ተከተሎ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል መልስ ሰጥቷል።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል በመወከል መልስ የሰጡት የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድና በህወሓት ምክትል ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩ በርካታ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ህጋዊ ጉባኤ አይደለም " ባሉት 14ኛው ጉባኤ የስራ አስፈፃሚ አባል ሆነው የተመረጡና በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ህወሓት ወክለው ከተደራደሩትና ውሉ ከፈረሙት አንዱ ፍስሃ ሃፍተፅዮን (ዶ/ር) ናቸው ። 

ፍስሃ (ዶ/ር) " ህወሓት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት እንደማይደግፍ ተደርጎ እየቀረበ ያለው ሃሳብ ስም ማጥፋት ነው " ሲሉ ኮንነዋብ።

" ህወሓት በፕሪቶሪያ ስምምነትና አተገባበር የፀና አቋም አለው " ሲሉ ተናግዋል።

የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በደቡብ አፍሪካ በሚፈፀምበት ወቅት ትግራይን ወክለው በተሳተፉ ተደራዳሪዎች መካከል ልዩነት ተፈጥሮ እንደነበረ አስታውሰዋል።

ጊዚያዊ መንግስት ማቋቋም አለመቋቋም በተደራዳሪዎች መካከል ከነበሩት የሃሳብ ልዩነት እንድ አንድ ነጥብ ጠቅሰውታል።   

" በፕሪቶሪያ ተስማምተን መፈረማችን አንድ ፀጋ ሆኖ የቀሩት ጉድለቶች በሂደት እንፈታቸዋለን ብለን አምነን ነው የተመለስነው " ሲሉ ፍስሃ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ሌላው " ህወሓት ከሻዕብያ ጋር ግንኙነት አለው የሚለው ወሬ ነጭ ውሸት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የፕሪቶሪያ ስምምነት ተደራዳሪና ፈራሚ ቡድን አባል የሆኑት ፍስሃ (ዶ/ር) " በውስጣችን ያሉ ግን መሬታችን ወረው ለያዙ ያግዛሉ " በማለት በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ጊዚያዊ አስተዳደር ወቅሰዋል። 

" ወደ ጦርነት የሚያስገባ አንድም ምክንያት የለም " ያሉ ሲሆን በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀምና አተገባበር እሳቸውን ያቀፈው የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል ትክክለኛ እንደሆነ ሞግተዋል።

የአሜሪካው የፕሪቶሪያ የሰላም አደራዳሪ ማይክ ሃመር ውሉና አተገባበሩ የሚመለከት ጉብኝት ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ፓለቲካዊ ልዩነት ግን አሁንም አልበረደም።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ሃይል " ህጋዊ  አይደለም " የተባለ 14ኛ ጉባኤ ካካሄደ በኋላ የእነ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ሃይል ፥
- ደርጅታዊ ስብሰባዎች በመንግስት የስራ ሰአት እንዳይካሄዱ የሚከለክል የስራ መመሪያ ፣
- ላልተወሰነ ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ የሚከለክል ማስጠንቀቅያ ፣
- የዞን አስተዳደሪዎች ሹምሹር ያካሄደ ሲሆን በክልሉ የዞኑ ትልልቅ ከተሞች በመዘዋወርም ህዝባዊ ውይይቶች በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ባለፈው ሳምንት በተምቤን ፣ በዓዲግራትና በማይጨው ህዝባዊ ውይይቶች አካሂዷል።

በቀጣይ የጳጉሜን ቀናትም ኣክሱምና እንዳስላሰ ሽረ እንደሚያቀና እየተነገረ ነው።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ምን አሉ ? የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩትና ም/ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ የሚገኙበት የአመራሮች ቡድን ከሰሞኑን ህዝባዊ ውይይቶችን እያደረገ ነው። ትላንት ማይጨው ላይ በነበረ ውይይት ጀነራል ፃድቃን ስለ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዙሪያ ሃሳቦች ሰጥተዋል። " የሚታየውን ዋናው የልዩነት ነጥብ በፕሪቶሪያ ውል ላይ ያለ የአመለካለት…
#Tigray

አቶ ጌታቸው ረዳ የጤና አክል ገጥሟቸዋል።

ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው ፥ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ዛሬ በአክሱም ሊካሄድ የታቀደው ህዝባዊ ውይይት ተሰርዟል።

ፅ/ቤቱ ፕሬዜዳንቱ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ከአክሱም ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች ጋር ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት ህዝባዊ ውይይት ሳይካሄድ በመቅረቱ ይቅርታ ጠይቋል።

ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ያጋጠማቸው የጤና እክል ቀላል ይሁን ከባድ በመግለጫው የተጠቀሰ የለም ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

ከሰሞኑን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ምክትላቸው ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ያሉበት የአመራሮች ቡድን በየከተማው ህዝባዊ ምክክር እያደረገ እንደነበር ይታወቃል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray አቶ ጌታቸው ረዳ የጤና አክል ገጥሟቸዋል። ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው ፥ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ዛሬ በአክሱም ሊካሄድ የታቀደው ህዝባዊ ውይይት ተሰርዟል። ፅ/ቤቱ ፕሬዜዳንቱ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ከአክሱም ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች ጋር ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት…
#UPDATE

" የጤናዬ ሁኔታ ብዙ የሚያሳስብ አይደለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ 

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም በ X ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሑፍ የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት በማስቀደም " የጤንነት ሁኔታየና ድህንነቴ ያሳሰባችሁና ያስጨነቃችሁ ሁላችሁም ደህና ነኝ " ብለዋል። 

" ተደጋጋሚ ረጅም መንገድ በመኪና መጓዝና ደካም ተደራርቦ የፈጠረው ጊዚያዊ ችግር እንጂ በሚያሳስብ ሁኔታ እንዳልሆንኩ በፈጣሪና በፅዮን ማርያም ስም እገልፅላችኃለሁ " ሲሉ ፅፈዋል።   

ቀጣይ ህዝባዊ መድረኮች ከተወሰኑ ቀናት በኋላ እንደሚቀጥሉ የገለፁት አቶ ጌታቸው " በመድረኩ ለመሳተፍ አክሱም ድረስ ለተንገላቱ ተሳታፊዎች ደግሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ " በማለት አክለዋል።   

ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም ከጊዚያዊ  አስተዳደሩ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የወጣ መግለጫ ፕሬዜዳንቱ የጤና እከለ እንደገጠማቸው በመግለፅ በአክሱም ከተማ ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት ህዝባዊ ውይይት ለሌላ ጊዜ መተላለፉና ይቅርታ መጠየቁን መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
#TPLF #እንዳስላሰሽረ

በሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ።

ህወሓት ሰላማዊ ስልፍ ለማካሄድ ከጳጉሜን 3 - 5 ባሉት ቀናት የጠየቀ ሲሆን ሰልፉ የሚካሄድበት ቦታ ደግሞ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ ነው።

የህወሓት ፅህፈት ቤት እንዳስላሰ ሽረ ቅርንጫፍ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም በፃፈው የሰላማዊ ሰልፍ የፍቃድ ደብዳቤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፁ ለማሰማት መፈለጉ ያትታል።

ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ፍቃድ በጠየቀበት ሰላማዊ ሰልፍ ፦

"
- ከባቢያዊ መለያየትና አገር የሚበትኑ ተግባራት ይቁሙ !
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ !!
- የፀለምቲና ራያ ተመላሽ ተፈናቃዮች ድህንነታቸው ይጠበቅ !
- የህዝበኝነት ፓለቲካ በትግራይ እንቃወማለን !
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር !
- ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመለት ዓላማ ይተግብር !
- ህወሓትን ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ይቁም !
- ህወሓት ሰላምን ይደግፋል !
- ጦርነት የሚናፍቅ የህወሓት መሪ የለም ! "

የሚሉና ሌሎች መፈክሮች እንደሚያሰማ በፍቃድ መጠየቂያ ደብዳቤው ላይ ገልጿል።

ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ለጠየቀው ' ሰላማዊ ሰልፍ ' የማካሄድ ጥያቄ መልስ የሰጠው የእንዳስላሰ ሽረ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ ባለው የፓለቲካ ትኩሳት እና የአዲስ ዓመት መለወጫ በመሆኑ ምክንያት የፀጥታ ሃይሉ የተደራረቡ ስራዎች ስላሉበት ሰላማዊ ስልፉ እንዳልተፈቀደ አሳውቋል።

በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ልኡክ በተምቤን ዓብዩ ዓዲ ዓዲግራትን ማይጨው ካካሄዳቸው ህዝባዊ ውይይቶች በመቀጠል በአክሱምና በእንዳስላሰ ሽረ ከተማዎች ለማካሄድ አቅዶ የነበረ ቢሆንም አቶ ጌታቸው ባጋጣመቸው የጤና እክል ምክንያቱ ውይይቱ ለሌላ ጊዜ መዛወሩን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል መዘገቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#ትንሳኤ70እንደርታ

" የመቐለ ከተማ አስተዳደር የፈቀድልን ህዝባዊ ስብሰባ ተከለከልን " ሲል ትንሳኤ 70 እንደርታ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን አሰማ።

የፓርቲው ሊቀመንበር ከበደ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በሰጡት ቃል ፥ _ እሁድ ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም በመቐለ ከተማ አስተዳደር ግቢ በሚገኘው አግኣዚ የስብሰባ አዳራሽ ህዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ ተፈቕዶልን አባልና ደጋፊዎቻችን ጠርተን ስናበቃ አዳራሽ እንዳንገባ በታጣቂዎች ተከልክለናል " ብለዋል።

" በህጋዊ መንገድ የተፈቀደ ህዝባዊ ውይይት መከልከልና ታዳሚዎች ማንገላታት ኢ-ዴሞክራሲያዊ ነው " ያሉት የፓርቲው ሊቀመንበር በተግባሩ ማዘናቸው በመግለፅ ከሚመለከተው አካል ግልፅ ማብራርያ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸው ተናግረዋል።

" የመቐለ ከተማ ፀጥታ ፅ/ቤት በፃፈልን ደብዳቤ መሰረት ስብሰባውን የፀጥታ ጥበቃ ለማድረግ ፓሊስ መድቦ በቦታው የተገኙ ሲሆን ማንነታቸውና ተጠሪነታቸው የማይታወቁ ሌሎች ሃይሎች ተሳብሳቢው ወደ ግቢ እንዳናሰግባ የአዳራሹ ሰራተኞች ሳይቀር እንዳይገቡ በር ላይ ለነበሩ የጥበቃ ሰራተኞች ትእዛዝ በመሰጠቱ ምክንያት ስብሰባው ሳይደረግ ቀርተዋል " ሲሉ አስረድተዋል።

" እንደምክንያት ያቀረቡትም የከንቲባ ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ለጋስ ማርያም ' እኔ ካልደወልኩኝ እንዳይገቡ ብለዋል ' የሚል ሲሆን ግለሰብዋ በደብዳቤ የፈቀዱትን ስብሰባ በዚህ መንገድ የከለከሉበት ምክንያት ለመጠየቅ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ስላካቸውን በመዝጋታቸው ምክንያት ልናገኛቸው አልቻልንም " በማለት ገልጸዋል።

የመቐለ ከተማ ፀጥታ ዘርፍና ፓሊስ መንግስታዊ ሃላፊነቱን በአግባቡ ለመወጣት መሞከሩን አመልክተው " ምስጋና ይገባዋል " ብለዋል።

የመቐለ ከተማ አስተዳደርና ፓሊስ እስከ አሁን ሰዓት ስለ ክልከላው የሰጠው ይፋዊ ማብራርያም ሆነ መግለጫ የለም። 

ትንሳኤ 70 እንደርታ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ከአንድ ዓመት በፊት ሰላማዊ ፓለቲካዊ ትግል ለማካሄድ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ እውቅና አግኝቶ መመስረቱ ይታወቃል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#Tigray

ባጋጠመ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ ከ10 በላይ ተሳፋሪዎች ህይወታቸው ተቀጠፈ።

የትራፊክ አደጋው ዛሬ  ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት አከባቢ የተከሰተ ሲሆን የሰሌዳ ቁጥር TG - 04539 የሆነ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከዓድዋ ወደ መቐለ ሲጓዝ ወርዒ ልዩ ቦታ  እንዳፈላሲ ቁልቁለት ሲወርድ ወደ ገደል በመግባቱ ነው አደጋው ያጋጠመው።

በውስጥ ከተሳፈሩ ሰዎች ከ10 በላይ ወድያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ 5 ሰዎች በፅኑ ተጎድተዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የደረሰው መረጃ እንደሚያመላክተው 48 ሰዎች የመጫን አቅም ያለው መለስተኛ አውቶቡስ በአጋጣሚ 20 ሰዎች ብቻ አሳፍሮ መጓዙ ለሟችና ቁስለኞች መቀነስ ምክንያት ሆኗል።

የአደጋው ምክንያት ገና በመጣራት ላይ ነው።

ይህ ወር በርካታ በዓላት የሚከበሩበት በመሆኑ ብዙ የትራፊክ እንቅስቃሴ ይኖራል ፤ በመላው ኢትዮጵያ የምትገኙ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ አይለያችሁ።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 
" 60 ሰዎችን አግተው ወስደዋል ፤ 369 ከብቶች ተዘርፈዋል ፤ 19 ቤቶችን አቃጥለዋል " - በትግራይ ክልል የምስራቃዊ ዞን

የኤርትራ መንግስት ወታደሮች 60 ሰዎች አግተው መውሰዳቸው 369 ከብቶችን በመዝረፍ 19 ቤት ማቃጠላቸው ተገልጿል።

የኤርትራ መንግስት ወታደሮች የእገታ የዝርፍያና ቤቶች የማቃጠል ተግባር የፈፀሙት በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የኢሮብና ጉሎመኸዳ ወረዳዎች እንደሆነ የዞኑ የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት አሳውቋል።

ከዞኑ ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ፥ ታግተው ከተወሱዱት 60 ሰዎች ሁለቱ ሴቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ወጣቶችና የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች ናቸው።

የኢሮብና የጉመኸዳ ወረዳዎች 8 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት የትግራይ ጦርነት ከተጀመረበት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ወዲህ ሙሉ በሙሉና በከፊል በኤርትራ መንግስት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።

ለድህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉት የጉሎመኸዳ ወረዳ ቀበሌ ገበሬ ማህበራት አርሶ አደሮች በሰጡት አስተያየት ፥ ባሳለፍነው ዓመት መጨረሻ በዜጎች ላይ ያነጣጠረ አፈና ተባብሶ መቀጠሉ አመልክተዋል።

" በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነት ወደነበረበት ባለመመለሱና የኤርትራ ሰራዊት ከአከባቢያቸው ሙሉ በሙሉ ባለመውጣቱ ለአፈናና ለከባድ የፀጥታ ስጋት አደጋ ተጋልጠናል " ብለዋል።

የጉሎመኸዳ ወረዳ የሰላምና የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊ ነብዩ ስዩም በበኩላቸው " በሙሉና በከፊል በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ከሚገኙ የወረዳው 4 ቀበሌ ገበሬ ማህበራት አስከአሁን 52 ወገኖች ታፍነው መወሰዳቸው እረጋግጠናል " ብለዋል።

" ማርታ ፣ አዲስ ተስፋ ፣ አዲስ ዓለም ሙሉ በሙሉ ሸዊት ለምለም በከፊል በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ይገኛሉ " ያሉት ሃላፊው " የኢትዮጵያ የአገር መከላከያ ሰራዊት በአከባቢው የለም " ሲሉ ገልፀዋል።

በተያያዘ ባለፈው ዓመት መጨረሻ ከተለያዩ የኢሮብ ወረዳ ቀበሌ ገበሬ ማህበራት 8 ሰዎች ታፍነው 222 ከብት፣ 157 ፍየልና በጎች ሲዘረፉ 19 ቤቶች በኤርትራ መንግስት መቃጠላቸው የዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) ሊቀ-መንበር ዶሪ አስገዶም አስታውቀዋል። 

የወረዳው የኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት እንደገለፀው አራት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በሙሉና በከፊል በኤርትራ መንግስት ወታደሮች ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።

በኤርትራ መንግስት ወታደሮች ቁጥጥር ስር የሚገኘው የአከባቢው ማህበረሰብ ለአራት ዓመታት በከፍተኛ የፀጥታ አደጋ ስጋትና ተስፋ መቁረጥ ስሜት እንደሚገኝ የገለፁት የወረዳዎች ነዋሪና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ገልጸዋል።

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተተግብሮ የኤርትራ ጦር ከያዘው አካባቢ እንዲወጣ ፣ የህዝብ ደህንነት እንዲጠበው፣ ተፈናቃዮች ወደ ቂያቸው እንዲመለሱ ተጠይቋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ።

ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :- 

1. አቶ ጌታቸው ረዳ 
2. አቶ በየነ ምክሩ
3. ፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት
4. ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፈይ
5. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃዲቕ
6. አቶ ረዳኢ ሓለፎም
7. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
8. አቶ ኢሳያስ ታደሰ
9. አቶ ሰለሞን መዓሾ
10. አቶ ሺሻይ መረሳ
11. ዶ/ር ገ/ሂወት ገ/ሄር 
12. አቶ ርስቁ አለማው
13. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
14. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
15. አቶ ሩፋኤል ሽፋረ 
16. አቶ ነጋ ኣሰፋ 

ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት " አባርሪያችኃለሁ " ብሏል።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ህወሓት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈገውና የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳና በርካታ የማእከለዊ ኮሚቴ አባላት " ህገወጥ " ያሉትን 14ኛ ጉባኤ በማካሄድ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መልሶ የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle  

@tikvahethiopia 
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF #Tigray በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ። በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል። የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ…
#Tigray

" ... የቆየው አመራር በአካልና በስልክ ስልጣን ለማስረከብ ቢጠየቅም ፍቃደኛ መሆን አልቻለም  " -  አዲሱ የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተኽላይ ፍቓዱ 

በቅርብ በትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር የተሾሙት  የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተኽላይ ፍቓዱ " የቆየው አመራር በአካልና በስልክ ስልጣን ለማስረከብ ቢጠየቅም ፍቃደኛ መሆን አልቻለም " ሲሉ ተናገሩ።

ይህን ያሉት ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ነው።

አቶ ተኽላይ ፥ በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋዊ ደብዳቤ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ከተሾሙ ሁለት ሳምንት መቆጠሩን ተናግረዋን።

ነገር ግን የቆየው አስተዳደር በአካልም ሆነ በስልክ የስልጣን ርክክብ ለማደረግ ቢጠየቅም ፍቃደኛ መሆን አልቻለም።

" በመንግስት በጀት የመንግስት ተፃፃራሪ ሆኖ መቆም ሽፍትነት ነው " ያሉት አቶ ተኽላይ " ከዚህ በኋላ መንግስት ሕግና ስርዓት ለማስከበር ይገደዳል " በማለት አስጠንቅቀዋል፡፡

በቅርቡ የተከሰተው የህወሓት መሰነጣጠቅ ተክትሎ በየቀኑ አዳዲስ ክስተቶች በመታየት ላይ ይገኛሉ።

(ለማስታወስ)

በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው ተተኪ የሚባሉ 16 የማእከላዊ ኮሚቴ  አባላት ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ያልሰጡትን 14ኛው ጉባኤ አካሂደዋል፡፡

14ኛው ድርጅታዊ ጉባኤው ህጋዊ አይደለም ያሉት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በጉባኤው የስራ አሰፈፃሚ አድርጎ የመረጣቸው የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ ሊያ ካሳና የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተኽላይ ገ/መድህን ምትክ አዳዲስ የዞን አስተዳዳሪዎች ሹመዋል፡፡

የዶ/ር ደብረፅዮኑ ህወሓት መስከረም 6 /2017 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ 14ኛ ጉባኤው ያልተሳተፉት የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላይ ኮሚቴ  አባላት ከአባልነትና ከድርጅታዊ የስራ ሃላፊነታቸው ማባረሩን አሳውቋል።

የእነ ዶክተር ደብረፅዮኑ ህወሓት " ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት አባርሪያቸዋለሁ " ብሎ መግለጫ ካወጣባቸው 16 የድርጅቱ የማእከላይ ኮሚቴ 5 አሁንም በጊዚያዊ አስተዳደሩ እውቅናና ተቀባይነት ያላቸው የትግራይ ደቡባዊ ፣ ደቡባዊ ምስራቅ ፣ ምስራቅ ፣ ማእከላዊ ፣ ሰሜናዊ ምዕራብና የምዕራብ ዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች ናቸው፡፡

በእነ ዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት በቅርቡ ባካሄደው ጉባኤ የማእከላይ ኮሚቴ አመራር በመሆን ከተመረጡት መካከል ይትባረክ ኣማሃና ኤልያስ ካሕሳይ የመቐለ ከተማ ዋናና ምክትል በመሆን በማስተዳደር ላይ ይገኛሉ በሃላፊነት ይቀጥሉ ይሆን ? በቀጣይ የምናየው ይሆናል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ። ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :-  1. አቶ ጌታቸው ረዳ  2. አቶ በየነ…
#Tigray

" ህገወጥ ቡድኑ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ አቅዷል " - በህወሓት ጉባኤ ያልተሳተፉት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት

በህወሓት ጉባኤ ላይ ያልተሳፉት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በጋራ መግለጫ አውጥተዋል።

በዚህም " ህገመንግስትና ህገ ድርጅት በመጣስ ህገወጥ ጉባኤ ያካሄደ ቡድን ሌላውን የማባረር ሞራልና ስልጣን የለውም " ብለዋል።

ከሰሞኑን በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን አቶ ጌታቸውን ጨምሮ 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን ማባረሩ ይታወሳል።

የማእከላዊ ኮሚቴ አባላቱ " ህገ-መንግስትና ህገ ድርጅት በመጣስ ህገ-ወጥ ጉባኤ ያካሄደው ቡድን ሌላውን የማባረር ህጋዊና ሞራላዊ ስልጣን የለውም " ከማለት ባለፈ " መፈንቀለ መንግስት ለማካሄድ ማቀዱን ደርሰንበታል " ብለዋል።

" የህገወጡ ቡድን መሪ በትግራይ ህዝብ ላይ የተፈፀመ ጄኖሳይድ ፍትህ እንዲያገኝና ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ መታገል ሲገባው ጉዳቱ ወደ ቁጥር ጨዋታ በማውረድ የህዝብ መስዋእትና የወጣቶች ጉዳት ዋጋ እያሳጣው ይገኛል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑን ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል " ኒው ሆራይዘን " ከተሰኘ የማህበራዊ ሚድያ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።

በዚህ ወቅትም " By the way ከአንድ ሚልየን በላይ አለቀ የሚለው ፤ ማስረጃ የለው፣ ጥናት የለው ፣ ለማስፈራርያ ነው የሚውለው። ተጨፍጭፈናል ለማለትም አይደለም ፣ ጄኖሳይድ ተፈፀመብን ለማለትም አይደለም። አመራሩ አስጨረሰን ይላል ፤ አመራር ለመምታት ፣ ስልጣን ለመያዝ የማይሰራ ነገር የለም። " ሲሉ ተናግረው ነበር።

በኃላም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ፤ " በህዝባችን ላይ የተፈፀመው ጄኖሳይድ አሁንም በርካታ በወራሪዎች ስር ያሉ የትግራይ አከባቢዎች ነፃ ባለመውጣታቸው ምክንያት የተሟለ መረጃ መስጠት ባይቻልም የደረሰው እልቂት ግን ከተጠቀሰው ቁጥር በላይ መሆን እንደሚችል ለመግለፅ እፈልጋሎህ " የሚል ማስተባበያ ለመስጠት ሞክረዋል።

የአቶ ጌታቸው ቡድን ህገ-ወጥ ሲል የሚጠራውን የዶ/ር ደብረጽዮን ቡድንን " ዓለምአቀፋዊ ወንጀል ሸምጥጦ በመካድ የዓለም ማህበረሰብ የተከራከረለትና የመሰከረውና የህዝብ እልቂት ወደ ጎን በመተው ዋጋ የሌለው እንዲሆን ወሰኖ ጥላሸት በመቀባት ላይ ይገኛል " ሲል ከሷል።

" ህገወጥ ቡድኑ ቡድናዊ የስልጣን ፍላጎቱ በፀረ ዴሞክራሲያዊ አካሄድ ፣ በማሰፈራራትና ሃሳቦች በማፈን ለመጫንና ለማሳካት ላይ ታች በማለት ይገኛል " ያለው የማእከላዊ ኮሚቴው " ይባስ ብሎ የመንግስት መዋቅር አንዲፈርስና ትግራይ መንግስት አልባ ሆና የረብሻና ግርግር ማእከል እንድትሆን እየሰራ ነው " ሲል አሳውቋል።

" ህገወጥ ቡድኑ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ማቀዱ ግልፅ ሆኗል " ያለው የማእከላዊ ኮሚቴው " ጊዚያዊ አስተዳደሩና ህዝቡ ከአደገኛ አካሄዱ ሊያስቆሙት ይገባል " በማለት አክለዋል።

50 ዓመት ያስቆጠረ ድርጅት እንደ አዲስ እንዲመዘገብ በማድረግ የትግራይ ህዝብ ትግል የካደው ቡድን ህዝቡና የዳያስፓራ አባላት እንዲታገሉት ጥሪ አቅርቦ የህወሓት ህጋዊ ሰውነት ለማስመለስ ፓለቲካዊ ውይይት መጀመሩን አመልክቷል።

መላው ህዝብ ከጎኑ እንዲሰለፍም ጥሪ አቅርቧል።

በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ እውቅና ውጪ ባካሄደው 14ኛው ጉባኤ ያልተሳተፉና ሂደቱን የተቋወሙት የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነታቸው አባርሪያለሁ " ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
#Tigray

አዲሱ የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሁለት የዞን ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነታቸው አነሱ።

በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ገ/ክርስቶስ  ፊርማ መስከረም 8/ 2017  ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው የዞኑ የመንግስታዊ አገልግሎት ዘርፍና የልማታዊ ዘርፍ አግልግሎት ሃላፊዎች ከስራ ተነስተዋል።

ለሃላፊዎቹ ከዞኑ መንግስታዊ የስራ ሃላፊነት መነሳት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራዎች አልፈፅምም ማለትና ማደናቀፍ እንደ ምክንያት ተጠቅሰዋል።

ሁለቱ የዞን የስራ ሃላፊዎች ከመስከረም 8/2017 ዓ.ም ከነበራቸው የስራ ሃላፊነታቸው ተሰናብተው የተሰጣቸው የመንግስት ንብረትና ስራ እንዲያስረክቡ በተፃፉላቸው የስንብት ደብዳቤዎች ተገልፆላቸዋል።

አቶ ፀጋይ ገ/ተኽለ ገ/ክርስቶስ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት በቅርቡ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው የተመረጡት ወ/ሮ ሊያ ካሳ ተክተው  የደቡብ ምስራቅ ዞን ዋና  አስተዳዳሪነት እንዲመሩ በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተሾሙ ናቸው። 

በተመሳሳይ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት መስከረም 6/2917 ዓ.ም " ከአባላትና ከድርጅታዊ ሃላፊነት አባርሪያቸዋለሁ " ብሎ ደብዳቤ የፃፈላቸው የህወሓት ማእካላዊ ኮሚቴ አባልና የትግራይ ማእከላይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሙን መዓሾ የአክሱም ከተማ የፀጥታ ሃላፊ ፣  የተምቤን ዓብዩ ዓዲ ከተማ ከንቲባና ሁለት የዞን የስራ ሃላፊዎች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ በማደናቀፍ በሚል ከሃላፊነታቸው ማንሳታቸው መዘገባችን ይታወሳል።  

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray አዲሱ የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሁለት የዞን ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነታቸው አነሱ። በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ገ/ክርስቶስ  ፊርማ መስከረም 8/ 2017  ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው የዞኑ የመንግስታዊ አገልግሎት ዘርፍና የልማታዊ ዘርፍ አግልግሎት ሃላፊዎች ከስራ ተነስተዋል። ለሃላፊዎቹ ከዞኑ መንግስታዊ የስራ ሃላፊነት መነሳት የጊዚያዊ አስተዳደሩ…
#Tigray

" የመንግስት መዋቅር ለመረበሽ እና ለመበጥበጥ የሚደረግ የተደራጀ ሙከራና እንቅስቃሴ አንቀበልም ፥ መንግስት ለዚህ መሰል እንቅስቃሴ ህጋዊ የሆነ የማስተካከያ እርምጃ ይወስዳል " ሲል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ አስጠንቅቋል።

ከሰሞኑን ካቢኔው ስብሰባ አድርጎ ነበር።

ይህን ተከትሎ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም የመንግስት መዋቅር ለመረበሽ ስለሚደረግ እንቅስቃሴ እና ስለ ህወሓት አመራሮች ክፍፍል እና ስለ ጸጥታ ኃይሉ ተነስቷል።

ካቢኔው " ከጊዚያዊ አስተዳደር እውቅና ውጪ ፦
- መንግስታዊ የስራ ምደባ ማካሄድ ፣
- የጊዚያዊ አስተዳደሩ ውሳኔዎች ማፍረስ
- የመንግስት መዋቅር ለመረበሽና ለመበጥበጥ የሚደረግ የተደራጀ ሙከራና እንቅስቃሴ ተቀባይነት የለውም " ብሏል።

" መንግስት ለዚህ መሰል ተቀባይነት የሌለው እንቅስቃሴ ህጋዊ የማስተካከያ እርምጃ ይወስዳል " ሲል አስጠንቅቋል።

ከህወሓት ክፍፍል ጋር በተያያዘ ካቢኔው " በአሁኑ ወቅት በህወሓት አመራሮች ዙሪያ የተፈጠረው መከፋፈል በህወሓትና በጊዚያዊ አስተዳደሩ መካከል የተፈጠረ ተደርጎ መወሰዱ ልክ አይደለም " ብሏል።

" ክፍፍሉ በጥቂት የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች የተፈጠረ ነው " ያለው ካቢኔው " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከህወሓት ከሙሁራን ከፀጥታ አካላትና ከተፎካካሪ ድርጅቶች በተወጣጡ አካላት የተደራጀ መሆኑ ከግምት ውሰጥ በማስገባት ከህወሓት ክፍፍል ጋር አቆራኝቶ መግለፅ ልክ አይደለም " ሲል ገልጿል።

ካቢኔው ስለ ፀጥታ ኃይሎች ባነሳው ነጥብ " የፀጥታ አካላት ሁሉም ዓይነት ችግሮችና ፈተናዎች ተቋቁመው የህዝብ ፀጥታ ለማስከበር እያደረጉት ያለውን ጥረት አወንታዊ እና እውቅና የሚቸረው ነው " ብሏል።

" ስራዎቻቸው ከማንኛውም የፓለቲካ አስተሳሰብ ነፃ በማድረግ ገለልተኛ አቋም ይዘው እንዲሰሩ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ይደግፋል ያበረታታል " ሲል አመልክቷል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " እኔ ድርድር ያስፈልጋል በሰላም ይፈታ ስል ፤ እሱ ግን ' ከማን ጋር ነው የምንደራደረው ? ' ነበር ያለው " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፤ ጄነራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ስልጣን ለመጠቅለል በማቀድና የቆየ ቂም ለመወጣት በሚል ከሰሱ። በደብረጽዮን (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ባሳለፍነው ሳምንት የመጨረሻ ቀናት መቐለን ጨምሮ በተለያዩ የትግራይ ከተሞች…
#Tigray
 
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፥ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራውን የህወሓት ቡድን አስጠነቀቁ።

ፕሬዜዳንቱ በማስጠንቀቂያቸው " ቡድን " ሲሉ የጠሩት ሃይል የወረዳና የከተማ የህዝብ ምክር ቤቶች ለመረበሽ እየሄደበት ያለው ርቀትና በማድረግ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ማቆም አለበት ብለዋል።

መስከረም 14/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንቱ ፊርማ ተፈርሞ ለሁሉም የወረዳና የከተማ ም/ቤቶች የተፃፈው የማስጠንቀቅያ ደብዳቤ " የህዝብ ምክር ቤቶች የትግራይ ጊዚያዊ መንግስትና የህዝቡ አካል እንጂ የህወሓት መዋቅር አለመሆናቸው አውቆ ' ቡድኑ ' የራሱ መሳሪያ ለማድረግ እያካሄደ ያለውን መሯሯጥና ውንብድና ማቆም አለበት " ይላል።

ስለሆነም ምክር ቤቶቹ የመንግስትና የህዝብ መዋቅር መሆናቸው በማመን ' ቡድኑ' ምክር ቤቶቹ በመጠቀም ያልደገፉትንና ሃሳቡ ያልተቀበሉት የመንግስት ሹመኞች ጥላሸት ለመቀባትና ከሃላፊነት ለማውረድ የሚያደርገው ጥረት መቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል።

ምክር ቤቶቹም ይህንን የመንግሰትና የፓለቲካ ድርጅት የሚቀላቅል ህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ማውገዝ አለባቸው ብሏል።

" ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን ህግና ስርዓት ለማስከበር ሲባል ወደ ህጋዊ ተጠያቂነት መሸጋገር የግድ ይሆናል " በማለት አክለዋል።  

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ከቀናት በፊት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ  ያወጣውን የአቋም መግለጫ የሚቃወም መግለጫ  አውጥቷል።

በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት መስከረም 14/2017 ዓ.ም ያወጣው  ባለ 4 ነጥብ የተቋውሞ መግለጫ ፤ " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጊዚያዊ  ስራዎች ለመስራት መቋቋሙ ተዘንግቶ ከተቀመጠለት የቆይታ የጊዜ ሰሌዳ በላይ እንዲቆይና ራሱን ወደ ተሟላ የመንግስት ሃላፊነት  ለመለወጥ የሚያደርገው ጥረት ፀረ ዴሞክራሲና ኢ-ህገመንግስታዊ ነው " ብሏል።

ምንም እንኳን " ኢ-ህገመንግስታዊ " ብሎ ቢገልጽም የአገር ወይም የክልሉ ህገ-መንግስት አንቀፆችን አላጣቀሰም።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ቡድን " ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጠው ተልእኮ ወደ ጎን በመተው ህወሓት ለማፍረስ ፣ ሰራዊት ለማዘዝና የመንግስትና ህዝብ ሃብት በመጠቀም የትግራይ ህዝብ አንድነት ለመበተን እየሄደበት ያለውን የተሳሳተ መንገድ ሊያቆም ይገባል " ሲል አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia