#Ethiopia🇪🇹

" ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን በቅርበት ትከታተላለች አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ተገቢውን ምላሽ ትሰጣለች " - ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫቸው ፥ " የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎረቤት ሀገራት ልዩ ትኩረት ይሰጣል " ሲሉ ጠቁመዋል።

" ኢትዮጵያ መርህን መሠረት ያደረገ በበጎ መንፈስ የተቃኘ ዘላቂ ዲፕሎማሲ ላይ አተኩራ ትሰራለች "ም ብለዋል።

" የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናን የትርምስ ማዕከል ለማድረግ የሚደረግ እንቅስቃሴም ሊቆም ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን በቅርበት እንደምትከታተልና አስፈላጊ በሆነበት ጊዜም ተገቢውን ምላሽ እንደምትሰጥ ገልፀዋል።

አምባሳደር ነቢያት ፥
➡️ ከአውሮፓ ህብረት፣
➡️ ከአሜሪካ
➡️ ከተመድ ልዩ መልዕክተኞች ጋር ውይይቶች መካሄዳቸውን ጠቁመዋል።

" ለሁሉም መልዕክተኞች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነበት ሆኖ የኢኮኖሚ ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል " ብለዋል። #EPA

@tikvahethiopia