TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Tigray, #Mekelle 📍 ትላንትና በጉዞ ላይ እንደነበሩ የተነገረላቸው አስፈላጊ የሆኑ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶችን የጫኑት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ተሸከርካሪዎች የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ደርሰዋል። ሁሉም (50ውም) ተሸከርካሪዎች በሰላም ነው መቐለ የደረሱት። ምን ይዘዋል ? ➡️ 1,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴ እና ጥራጥሬ ፤ ➡️ 700 ሜትሪክ ቶን የጤና ፣ የተመጣጠነ ምግብ…
#WFP #USA #Ethiopia #TigrayRegion

የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ወደ ትግራይ ክልል #ተጨማሪ ኮንቮይዎችን ለመላክ ዝግጁ መሆኑና ፍቃድም እንዳለው ገልጿል።

ቀጣዩ የሰብዓዊ እርደታ ኮንቮይ በተቻለ ፍጥነት በሰላም እንዲሄድ በአፋር ክልል ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ አሜሪካ ትላንት በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ ፤ ከ1,700 ሜትሪክ ቶን በላይ ነፍስ አድን ሰብአዊ እርዳታ ትግራይ መግባቱ መልካም ዜና ነው ብላለች።

የእርዳታው እንዲደስ ትብብር ያደረጉትን የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪዎች እና የአፋር ክልል አስተዳዳሪዎችን እንደምታደንቅም ገልፃለች።

በተጨማሪም ፤ አሜሪካ የትግራይ ኃይሎች ከአፋር ክልል ኤሬብቲ መውጣታቸውን እንደምትደግፍ ገልፃ ከሌሎችም የአፋር አካባቢዎች የትግራይ ኃይሎች ቢወጡ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብላለች።

አሜሪካ በትላንት መግለጫዋ የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ ባለስልጣናት አሁን በታየው ለውጥ ቀጥለው ግጭቱን በድርድር፣ በዘላቂነት መፍታት የሚችሉበት መንገድ ማግኘት አለባቸው ብላለች።

ይህ እንዲሆንም በትግራይ ክልል መሠረታዊ አገልግሎቶች መመለስ እንዳለባቸው እና አካታች ፖለቲካዊ አካሄድ መተግበር እንዳለበት ገልጻለች።

የአሜሪካ መግለጫ : https://www.state.gov/delivery-of-humanitarian-assistance-in-tigray/

@tikvahethiopia
ለምንድነው በዩክሬን እየተካሄደ የሚገኘው ጦርነት የዓለምን የምግብ ዋጋ እንዲህ እንዲጨምር ያደረገው ?

🌾 ዩክሬን እና ሩስያ በአለም የስንዴ ኤክስፖርት 1/3 የሚሸፍኑ ሀገራት ናቸው።

🪖 በሁለቱ ሀገራት መካከል ጦርነቱ ሲቀሰቀስ የስንዴ ኤክስፖርት ሊቋረጥ ችሏል።

📈 በ2 ሳምንታት ውስጥ ብቻ የስንዴ ዋጋ በ28 በመቶ ከፍ ብሏል ፤ ይህም ሪከርድ የሆነ የዋጋ ጭማሪ የተመዘገበበት ነው።

🌍 በጦርነቱ ምክንያት የታየው የዋጋ ጭማሪ በተለይ ከውጭ ሀገር በሚገባ ምርት ላይ ጥገኛ የሆኑ ሀገራትን ክፉኛ ጎድቷቸዋል።

#WFP

@tikvahethiopia
#WFP #Ethiopia

የግጭት ማቆም ውሳኔ ይፋ ከተደረገበት ከመጋቢት ወር ጀምሮ ወደ ትግራይ ክልል ከሚገባው እርዳታ #ከፍተኛ መጠን ያለው ቁሳቁስ በዚህ ሳምንት ወደ ክልሉ መግባቱን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል።

በዚህ ሣምንት ወደ ትግራይ የገባው 15 ሺህ ቶን ምግብ እና ሌሎች የነፍስ አድን አቅርቦቶች ሲሆን አሁንም ተጨማሪ እርዳታ ወደ ክልሉ እያመራ መሆኑን WFP ገልጿል።

ኤድሪያብ ቫን ደር ክናፕ (በዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ቢሮ ኃላፊ) ፥ " ፍጥነቱ አሁን እየጨመረ ስለሆነ በዚህ ወር መጨረሻ በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ 30 ሺህ ሜትሪክ ቶን ምግብ እና የምግብ ሸቀጦች ወደ ትግራይ ይደርሳል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ። እቅዳችን በሰኔ ወር መጨረሻ 100 ሺህ ቶን ምግብ ለማድረስ ነው " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የረድኤት ድርጅቶች አፋርን ጨምሮ በአጎራባችን ክልሎች ቀውሶች እየተባባሱ በመሆናቸው እጅ እያጠራቸው ፤ የእርዳታ ክምችታቸውም እየተመናመነ መሆኑን ጠቁመዋል።

የዩክሬን ጦርነት እና ሌሎችም በዓለም ዙሪያ የታዩት ቀውሶች የለጋሾችን የረድዔት አቅም እየቀነሰው መሆኑ የታገለፀ ሲሆን WFP በሚቀጥለው 6 ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ ለሚያስፈልገው የእርዳታ አቅርቦት የ522 ሚሊዮን ዶላር እጥረት እንደሚያጋጥመው ገልጿል።

ከዚህ ውስጥ 220 ሚሊዮን ዶላር ትግራይን ጨምሮ በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል ለሚሰራው የረድኤት ስራ የሚውል ነው።

ኤድሪያብ ቫን ደር ክናፕ ፤ " ያለን ክምችት በጣም በፍጥነት እያለቀ ነው። ስለዚህ ስጋታችን ይህን አውንታዊ ድባብ ፈጥረን እነኚህን መተላለፊያዎች ከፍተን መልሰን ማቆም ሊኖርብን ነው እናም ሁሉ ነገር ከሚያዚያ በፊት ወደነበረው ስፍራ ሊመለስ ነው " ብለዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/VOA-05-21

@tikvahethiopia
#Tigray

#ሰብዓዊነት ሲባል የግጭት ማቆም ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ #ከፍተኛ ነው የተባለው የሰብዓዊ እርድታ ወደ ትግራይ ተጓጉዟል።

አርብ ዕለት ከአፋር ሰመራ ከተማ 215 የምግብ እርዳታ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ አቅንተዋል።

የግብረ ሰናይ ተቋማት በትግራይ ክልል 5.2 ሚሊዮን ሰዎችን ለመመገብ በየሳምንቱ በ500 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተጫነ የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ክልሉ ሊደርስ እንደሚገባ እየገለፁ ይገኛሉ።

በሌላ በኩል ፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ትግራይ ክልል ገብተው በነዳጅ እጦት ምክንያት ቆመው የነበሩ ተሽከርካሪዎቹ ከትግራይ እየወጡ እንደሆነ በዚህ ሳምንት አመልክቷል።

ተሽከርካሪዎቹ ባለፈው ዓመት 2021 ወደ ክልሉ ገብተው የነበሩ ከድረጅቱ የተገኘው መረጃ ያመልክታል።

የተሽከርካሪዎቹ ከትግራይ ክልል መመለስ በሃገር አቀፍ ደረጃ ያለውን ሰብዓዊ አቅርቦት ለማሻሻል እንደሚያግዝም ድርስክቱ ገልጿል።

#ኤፒ #WFP

@tikvahethiopia
#WFP #ETHIOPIA

የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ወደ ትግራይ እና በግጭት ወደ ተጎዱ አካባቢዎች ኮንቮይዎችን መላክ መቀጠሉን እንደገፋበት አመልክቷል።

በሚያዝያ/ግንቦት በ1,045 የጭነት ተሽከርካሪዎች አማካኝነት 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ቶን ምግብ ማቅረብ መቻሉንና 350 ሺህ ሰዎችን በህይወት አድን ምግብ መድረስ መቻሉን ድርጅቱ አሳውቋል።

ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ቀጣይነት ያለው የአቅርቦት ፍሰት እንዲኖር እና ድጋፍ እንዲደርሳቸው ለማድረግ ከባለሥልጣናት ጋር እየሰራ መሆኑንም ገልጿል።

@tikvahethiopia
#WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በአፋር ክልል እስከ 1.2 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ለረሃብ የመጋለጥ አደጋ እንዳንዣበበባቸው አመልክቷል።

ድርጅቱ ፤ በክልሉ ላሉ 630,000 ሰዎች ወሳኝ የምግብ አቅርቦት ስርጭት እያካሄደ መሆኑን ገልጿል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም " አምስተኛውን ዙር የምግብ እርዳታ ለሁሉም ማድረስ ጨርሰናል እና ቀጣዩን ዙር በቅርብ ጊዜ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነን " ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አሁኑኑ የተሰረቀውን ነዳጅ መልሱ " - WFP የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ድርጅታቸው ለእርዳታ ሥራው የሚያውለውን 570,000 ሊትር ነዳጅ " የትግራይ ባለሥልጣናት ሰርቀዋል " ብለዋል። " ምግብ ለማድረስ ነዳጅ ከሌለን በሚሊዮኖች ይራባሉ " ያሉት ቢዝሊ ድርጊቱን " የሚያስቆጣ እና አሳፋሪ " ብለውታል። አሁኑን የተሰረቀው ነዳጅ እንዲመለስ ጠይቀዋል። @tikvahethiopia
#WFP #UN

" ነዳጁ በቅርቡ በWFP የተገዛ እና ከመሰረቁ ጥቂት ቀናት በፊት መቐለ የደረሰ ነበር " - WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ከመቐለ ተሰረቀ ባለው ነዳጅ ጉዳይ ላይ በዋና ዳይሬክተሩ ዴቪድ ቢዝሊ በኩል ማብራሪያ ሰጥቷል።

ዋና ዳይሬክተሩ ትላንት ጥዋት የተዘረፈው ነዳጅ ከግማሽ ሚሊዮን ሊትር  በላይ (12 ታንከር) መሆኑንና የታጠቁ ቡድኖች ወደ WFP ግቢ ገብተው መውሰዳቸውን ገልፀዋል።

ነዳጁ በቅርቡ በWFP የተገዛ እና ከመሰቀሩ ጥቂት ቀናት በፊት የደረሰ መሆኑን አስረድተዋል።

WFP ያለ ነዳጁ ምግብ፣ ማዳበሪያ፣ መድሃኒት እና ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎችን በመላው ትግራይ ሊያደርስ እንደማይችል ገልጸዋል።

በተጨማሪም ጄነሬተሮችን እና ተሽከርካሪዎች ለማንቀሳቀስ እንደሚቸገር የገለፀው WFP 5.2 ሚሊዮን የሚደርሰውን ረሃብ የተጋረጠበትን ህዝብ ለመድረስ እንቅፋት እንደሚሆንበት አስረድቷል።

የነዳጁ መሰረቅ በግጭት ሳቢያ እየተፈተነ ያለውን በትግራይ ያለውን ማህበረሰብ ወደ ረሃብ አፋፍ ይገፋል ብለዋል።

የትግራይ ባለስልጣናት በአስቸኳይ የነዳጅ ክምችቱን እንዲመልሱ አሳስበዋል።

ህወሓት በበኩሉ " ከወራት በፊት ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ያበደርኩትን ነዳጅ መልሼ ወስድኩ እንጂ ዘረፋ አልፈጸምኩም " ሲል መልሷል።

ዋና ዳይሬክተሩ መሰል አስተያየት ከመስጠታቸው በፊት ዝርዝር ሁኔታውን ማጣራት ነበረባቸው ብሏል።

ከ600 ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ ለWFP አበድርያለሁ ያለው ህወሓት " በነበረን ስምምነት መሠረት ያበደርነውን ነዳጅ ተመላሽ እንዲሆን ነው የጠየቅነው " ሲል ገልጿል።

የወሰድነው ነዳጅ እንደ ሆስፒታል ፣ ክሊኒክ እና ሌሎች የጤና ማዕከላትን ለማንቀሳቀስ ጥቅም ላይ ይውላልም ሲሉ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተርን ክስ አጣጥሏል።

@tikvahethiopia
#WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ትግራይ ክልል በረራ ማድረጉን ዛሬ ገልጿል።

ይህ ጉዞ ከ6 ሳምንታት በኋላ የመጀመሪያው ነው።

ድርጅቱ 34 ሰራተኞቹን ከክልሉ ማስወጣቱን ገልጿል።

ተጨማሪ በረራዎች በመጪዎቹ ቀናት በማድረግ ሰራተኞቹን ከመቐለ ለማስወጣት ቀጠሮ መያዙንም የዓለም ምግብ ፕሮግራም አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UN እ.ኤ.አ. ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት እና በሰብአዊ ድጋፍ አጋሮች አማካኝነት ከ17,000 ሜትሪክ ቶን በላይ የእርዳታ እህል ትግራይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዛሬ አሳውቋል። ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ተጨማሪ በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#WFP

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ...

(የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) የዛሬ ሪፖርት)

- የዓለም ምግብ ፕሮግራም #አራቱም የተከፈቱትን የመንገድ ኮሪደሮች በመጠቀም ስራ ከጀመረበት እኤአ ከህዳር 15 ጀምሮ በ96 የጭነት መኪናዎች 170 ሺህ ሰዎችን ሊመግብ የሚችል ከ2,400 ሜትሪክ ቶን በላይ ምግብ እንዲሁም 100,000 ሊትር ነዳጅ ወደ ትግራይ አጓጉዟል።

- በWFP የሚመራው የሎጂስቲክስ ክላስተር 250 ሜትሪክ ቶን የሰብአዊ ድጋፍ ካርጎ ከጎንደር፣ ኮምቦልቻ እና ሰመራ ለስምንት ተባባሪ አጋሮች የህክምና ቁሳቁሶችን ጨምሮ በአየር እንዲጓጓዝ አመቻችቷል።

- ካለፈው እኤአ ነሃሴ ወር መጫረሻ በኃላ የWFP የUNHAS የመንገደኞች በረራ ዛሬ ወደ #መቐለ አድርጓል። በረራውን ደረገው ከፌዴራል ፍቃድ ካገኘ በኃላ ሲሆን ወደ መቐለ መደበኛ የUNHAS በረራ መቀጠል አለበት ብሏል።

- WFP ፤ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ እና ደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ወረዳዎች በአማራ በኩል አዲስ የሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎት ቢያገኙም ወደ አንዳንድ የትግራይ #ምስራቃዊ እና #ማዕከላዊ ዞኖች አሁንም መግባት ውስን መሆኑንና እስከ 170 ሺህ የሚደርሱ እናቶችና ህፃናት የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው WFP አሳውቋል።

- ወደ ትግራይ የሚያስገቡ መንገዶች ከተከፈቱ ወዲህ WFP በሰሜን ምእራብ ዞን ማይ ፀብሪ እና በደቡብ ዞን አላማጣ ላሉ ከ100,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች እህል ማቅረቡን ገልጿል። በህዳር ወር መጀመሪያ ላይም በመቐለ 540,000 ሰዎችን ደርሷል። ከህዳር ወር መጀመሪያ ጀምሮ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ፤ በትግራይ ክልል የምግብ ድጋፍ ከሚያስፈልጋቸው 2.1 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ መድረስ የቻለው 29 በመቶውን መሆኑን ገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/WFP-11-25

@tikvahethiopia
#WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ሲያቀርበው የነበረው እርዳታ በተወሰነ መልኩ ማቅረብ መጀመሩ ተገለፀ።

በተመድ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ኢትዮጵያ ሲያቀርበው የነበረው የሰብአዊ እርዳታ ከአምስት ወራት ብኋላ እጅግ አነስተኛ በሚባል መልኩ እርዳታ መላክ መጀመሩን " አሶሸትድ ፕሬስ " ገልጿል።

ድርጅቱ ለአሶሸትድ ፕሬስ እንደገለፀው ፤ በትግራይ 4 አካባቢዎች በመቶ ሺህ እርደታ ፈላጊ ዜጎች ላይ አዲሱ የተቋሙ አሰራር ትግበራ ሙከራ በሐምለ መጨረሻ መጀመሩን አሳወቋል።

የተለያዩ ተቋማት ፣ ሃይማኖት መሪዎች እና የተለያዩ አካላት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለተቸገሩ ወገኖች ሲያቀርብ የነበረው  እርዳታ ማቋረጡን ተገቢ አለመሆኑ እና ከሞራል አንፃር ኢሞራላዊ ነው ብለው ሲተቹት እንደነበር ያወሳው ዘገባው በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ በምግብ እጦት ምክንያት በትግራይ የሞት አደጋ ማጋጠሙን አስታውሷል።

የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት / USAID ኃላፊ የሆኑት ሳማንታ ፓወር በበኩላቸው ፤ " ተፈጠሩ የተባሉ ችግሮችን በማጣራት እንዲሁም እርዳታው ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች በትክክል መድረሱን ማረጋገጥ ተገቢ ነው " ያሉ ሲሆን የሰብአዊ እርዳታው በአጭር ግዜ ለማስጀመር ጥረት ይደረጋል ማለታቸው ተዘግቧል።

ከአምስት ወራት በፊት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ለኢትዮጵያ ሲያቀርበው የነበረው የሰብአዊ  ድጋፍ ስርቆትና ላልተገባ ተግባር ውሏል በመባሉ እንዲቆም መደረጉን የሚታወስ ነው።

መረጃው የድምፂ ወያነ ነው።

@tikvahethiopia