TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና~አዴፓ⬇️

ብአዴን(አዴፓ) ዛሬ ምሽት በሚያካሂደው የማዕከላዊ ኮሚቴነት ምርጫ ባይወዳደሩ ያላቸውን 13 አመራሮች መነሻ አቀረበ፡፡

ድርጅቱ በማዕከላዊ ኮሚቴነት የማይወዳደሩ ብሎ ያቀረበው በትምህርት፣ በአምባሳደርነት እና በክብር የተሰናበቱ የድርጅቱ አባላት በሚል
ነው፡፡

• በትምህርት የሚሰናበቱ አቶ ዓለምነው መኮንን፣አቶ ለገሰ ቱሉ ፣አቶ ጌታቸው ጀምበር፣ አቶ ኢብራሂም ሙሀመድ፣አቶ ደሳለኝ አምባው እና ወይዘሮ ባንቺ ይርጋ መለሰን ባይወዳደሩ ብሎ መነሻ አቅርቧል፡፡

• በክብር ደግሞ አቶ #ደመቀ_መኮንን ፣አቶ ከበደ ጫኔ፣ አቶ መኮንን የለውም ወሰን፣ወይዘሮ ፍሬህይወት አያሌው እና አቶ ጌታቸው አምባየን በክብር ቢሰናበቱ ብሎ አቅርቧል፡፡

• በአምባሳደርነት እያገለገሉ ያሉትን አቶ ካሳ ተክለብርሀንና ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰን ከውድድሩ ውጭ ቢሆኑ ብሎ ማዕከላዊ ኮሚቴው መነሻ አቅርቧል፡፡ ማዕከላዊ ኮሚቴው ያቀረበውን ማሻሻያ ሲያስረዳ በፌዴራል ደረጃ የሚገኙ አመራሮች ካላቸው የስራ ጫና ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው በክልሉ እንዲሰሩ ታሳቢ በማድረግ እና የአመራር መተካካት አስፈላጊ በመሆኑ ብሏል፡፡

ለትምህርት የተላኩት ደግሞ ፓርቲውን በረዥም ጊዜ ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ #ማዕከላዊ ኮሚቴው ይህንን መነሻ ይዞ ቀርቧል፡፡

ከላይ የተጠቀሱት 13 አመራሮች ለቀጣይ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባይወዳደሩ ብሎ መነሻ አቅርቧል፡፡

ዛሬ ምሽት 65 አባላትን ያካተት የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ይመረጣል፡፡

ከተመረጡት ውስጥም 13 ለብአዴን(አዴፓ) ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ፣ 9 ደግሞ ለኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ይመረጣሉ፡፡የማዕከላዊ ኮሚቴው ምርጫ ከእራት በኋላ ይቀጥላል፡፡

ብአዴን ስያሜውን ወደ #አዴፓ መቀየሩ ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ⬆️በዛሬው ዕለት #ማዕከላዊ_እስር_ቤትን የጎበኙ የTIKVAH-ETHIOPIA የቤተሰብ አባላት ከላይ ያሉትን ፎቶዎች #አጋርተውናል!

እርሶስ ማዕከላዊን ጎብኝተው ነበር? ፎቶዎችን ያጋሩ!

ፎቶ©ABEBA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማዕከላዊ እስር ቤት⬆️#የTIKVAH_ETH ቤተሰብ አባላት #ማዕከላዊ_እስር_ቤትን ተዘዋውረው እየጎበኙ እኛም በያለንበት የእስር ቤቱን ሁኔታ በስልካችን ላይ እንድናየው እያደረጉን ይገኛሉ።

ፎቶ📸CAN

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወንድ ህፃናትን የደፈሩ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ ፦

#አርባ_ምንጭ :

በ10 ዓመት ህጻን ላይ የግብረ-ሰዶም ወንጀል የፈጸመ ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አሳወቀ፡፡

ተከሳሽ አቶ ተመኘሁ ጣሰው የተባለ በከተማው የድልፋና ቀበሌ ነዋሪ የሆነ የ39 ዓመት ግለሰብ በቀበሌው ነዋሪ የሆነውን የ10 ዓመት ህጻን ላይ የግብረ - ሰዶም ወንጀል መፈጸሙን ፍርድ ቤቱ በሰነድና በሰው ማስረጃ አረጋግጧል።

ወንጀሉን ለየት የሚያደርገው በአከባቢው ያልተለመደ እና የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ በማስፈራራት ተከሳሽ ወንጀሉን እየፈጸመ መቆየቱና በመጨረሻ በአርባ ምንጭ ከተማ ሼቻ ቀበሌ "ገሮ መኝታ ቤት" ወንጀሉን እየፈጸመ እያለ በአከባቢው ህብረተሰብ ጥቆማ ሊያዝ መቻሉ ነው።

በወንጀል ህግ ቁጥር 631 ንዑስ 1 ሀ መሠረት በአቃቤ ህግ ክስ ቀርቦ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ወንጀሉን ስለመፈጸሙ የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማጣራት በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።

#ማዕከላዊ_ጎንደር

በአማራ ክልል በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዐቃቤ ሕግ መምርያ የግብረ ሰዶም ወንጀል የፈፀመውን ግለሰብ በእስራት ቀጥቷል።

ተከሳሽ አቶ የምስራች ዓባይ ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቀኑ 5:00 ላይ ታች አርማጭሆ ወረዳ ሙሴ ባንብ ቀበሌ የ8 ዓመት ሕፃን ወንድ ልጅ አስገድዶ ደፍሯል፡፡

የሙሴ ባንብ ንዑስ ወረዳ ፍርድ ቤት የተከሳሽን የወንጀል ድርጊት በሰው እና በሕክምና ማስረጃ ማረጋገጥ ችሏል፡፡

ተከሳሽ የወንጀል ሕግ ቁ631/1/ለ/ ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

መልዕክት ፦

ወላጆችና አሳዳጊዎች ህጻናት ለወንጀል ተጋላጭ እና ራሳቸውን ለመከላከል ስለማይችሉ የጥቃት ሰለባዎች እንዳይሆኑ የልጆቻቸሁን አዋዋል ልትከታተሉና ልትቆጣጠሩ ይገባል።

በህጻናት ላይ የተለየና አጣራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥም ለሚመለከተው አካል ጥቆማ ስጡ።

[ይህ መረጃ የተሰባጠረው ከአርባ ምንጭ ኮሚኒኬሽን ፣ የአርባ ምርጭ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት አቶ አለማየሁ አልታዬ እና ከአዲስ ዘይቤ /Addis Zeybe/ ደረገፅ ነው]

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UN እ.ኤ.አ. ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት እና በሰብአዊ ድጋፍ አጋሮች አማካኝነት ከ17,000 ሜትሪክ ቶን በላይ የእርዳታ እህል ትግራይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዛሬ አሳውቋል። ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ተጨማሪ በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#WFP

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ...

(የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) የዛሬ ሪፖርት)

- የዓለም ምግብ ፕሮግራም #አራቱም የተከፈቱትን የመንገድ ኮሪደሮች በመጠቀም ስራ ከጀመረበት እኤአ ከህዳር 15 ጀምሮ በ96 የጭነት መኪናዎች 170 ሺህ ሰዎችን ሊመግብ የሚችል ከ2,400 ሜትሪክ ቶን በላይ ምግብ እንዲሁም 100,000 ሊትር ነዳጅ ወደ ትግራይ አጓጉዟል።

- በWFP የሚመራው የሎጂስቲክስ ክላስተር 250 ሜትሪክ ቶን የሰብአዊ ድጋፍ ካርጎ ከጎንደር፣ ኮምቦልቻ እና ሰመራ ለስምንት ተባባሪ አጋሮች የህክምና ቁሳቁሶችን ጨምሮ በአየር እንዲጓጓዝ አመቻችቷል።

- ካለፈው እኤአ ነሃሴ ወር መጫረሻ በኃላ የWFP የUNHAS የመንገደኞች በረራ ዛሬ ወደ #መቐለ አድርጓል። በረራውን ደረገው ከፌዴራል ፍቃድ ካገኘ በኃላ ሲሆን ወደ መቐለ መደበኛ የUNHAS በረራ መቀጠል አለበት ብሏል።

- WFP ፤ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ እና ደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ወረዳዎች በአማራ በኩል አዲስ የሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎት ቢያገኙም ወደ አንዳንድ የትግራይ #ምስራቃዊ እና #ማዕከላዊ ዞኖች አሁንም መግባት ውስን መሆኑንና እስከ 170 ሺህ የሚደርሱ እናቶችና ህፃናት የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው WFP አሳውቋል።

- ወደ ትግራይ የሚያስገቡ መንገዶች ከተከፈቱ ወዲህ WFP በሰሜን ምእራብ ዞን ማይ ፀብሪ እና በደቡብ ዞን አላማጣ ላሉ ከ100,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች እህል ማቅረቡን ገልጿል። በህዳር ወር መጀመሪያ ላይም በመቐለ 540,000 ሰዎችን ደርሷል። ከህዳር ወር መጀመሪያ ጀምሮ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ፤ በትግራይ ክልል የምግብ ድጋፍ ከሚያስፈልጋቸው 2.1 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ መድረስ የቻለው 29 በመቶውን መሆኑን ገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/WFP-11-25

@tikvahethiopia