TIKVAH-ETHIOPIA
#UN እ.ኤ.አ. ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት እና በሰብአዊ ድጋፍ አጋሮች አማካኝነት ከ17,000 ሜትሪክ ቶን በላይ የእርዳታ እህል ትግራይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዛሬ አሳውቋል። ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ተጨማሪ በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#WFP

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ...

(የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) የዛሬ ሪፖርት)

- የዓለም ምግብ ፕሮግራም #አራቱም የተከፈቱትን የመንገድ ኮሪደሮች በመጠቀም ስራ ከጀመረበት እኤአ ከህዳር 15 ጀምሮ በ96 የጭነት መኪናዎች 170 ሺህ ሰዎችን ሊመግብ የሚችል ከ2,400 ሜትሪክ ቶን በላይ ምግብ እንዲሁም 100,000 ሊትር ነዳጅ ወደ ትግራይ አጓጉዟል።

- በWFP የሚመራው የሎጂስቲክስ ክላስተር 250 ሜትሪክ ቶን የሰብአዊ ድጋፍ ካርጎ ከጎንደር፣ ኮምቦልቻ እና ሰመራ ለስምንት ተባባሪ አጋሮች የህክምና ቁሳቁሶችን ጨምሮ በአየር እንዲጓጓዝ አመቻችቷል።

- ካለፈው እኤአ ነሃሴ ወር መጫረሻ በኃላ የWFP የUNHAS የመንገደኞች በረራ ዛሬ ወደ #መቐለ አድርጓል። በረራውን ደረገው ከፌዴራል ፍቃድ ካገኘ በኃላ ሲሆን ወደ መቐለ መደበኛ የUNHAS በረራ መቀጠል አለበት ብሏል።

- WFP ፤ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ እና ደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ወረዳዎች በአማራ በኩል አዲስ የሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎት ቢያገኙም ወደ አንዳንድ የትግራይ #ምስራቃዊ እና #ማዕከላዊ ዞኖች አሁንም መግባት ውስን መሆኑንና እስከ 170 ሺህ የሚደርሱ እናቶችና ህፃናት የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው WFP አሳውቋል።

- ወደ ትግራይ የሚያስገቡ መንገዶች ከተከፈቱ ወዲህ WFP በሰሜን ምእራብ ዞን ማይ ፀብሪ እና በደቡብ ዞን አላማጣ ላሉ ከ100,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች እህል ማቅረቡን ገልጿል። በህዳር ወር መጀመሪያ ላይም በመቐለ 540,000 ሰዎችን ደርሷል። ከህዳር ወር መጀመሪያ ጀምሮ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ፤ በትግራይ ክልል የምግብ ድጋፍ ከሚያስፈልጋቸው 2.1 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ መድረስ የቻለው 29 በመቶውን መሆኑን ገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/WFP-11-25

@tikvahethiopia