#WFP #ETHIOPIA

የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ወደ ትግራይ እና በግጭት ወደ ተጎዱ አካባቢዎች ኮንቮይዎችን መላክ መቀጠሉን እንደገፋበት አመልክቷል።

በሚያዝያ/ግንቦት በ1,045 የጭነት ተሽከርካሪዎች አማካኝነት 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ቶን ምግብ ማቅረብ መቻሉንና 350 ሺህ ሰዎችን በህይወት አድን ምግብ መድረስ መቻሉን ድርጅቱ አሳውቋል።

ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ቀጣይነት ያለው የአቅርቦት ፍሰት እንዲኖር እና ድጋፍ እንዲደርሳቸው ለማድረግ ከባለሥልጣናት ጋር እየሰራ መሆኑንም ገልጿል።

@tikvahethiopia