TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከሟቾች መካከል ሴቶች እና ህፃናት ይገኙበታል " - የቲክቫህ አባል ዛሬ በቄለም ወለጋ ለምለም ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተጨፍጭፈዋል። እሱና ቤተሰቦቹ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ አባል ዛሬ የተፈፀመው ጭፍጨፋ እጅግ በጣም አሳዛኝ እንደነበር ገልፆ በርካታ ሰው ተገድላል፤ ሴቶች እና ህፃናትም ይገኙበታል ብሏል። በአካባቢው ኔትዎርክ ይሰራ ነበር አሁን ላይ እየሰራ አይደለም ቤተሰቦቼ…
የቄለም ወለጋው ጥቃት ...

" ... ጥቃት አድራሾቹ እጅግ በጣም የታጠቁ እና የተደራጁ ናቸው።

እዛ ያለው ማህበረሰብ ምስኪን ገበሬ ነው የዕለት ጉርሱን ዳፋ ቀና ብሎ የሚያገኝ ነው።

መብራት እንኳን በቅጡ የሌለው አካባቢ ነው። ከቦቀሎ እና ማሽላ እንጀራ በዘለለ የማይበላ ፤ በኑሮው የተጎሳቆለ ማህበረሰብ ነው እንኳን ጥይት እና ገጀራ ሊገባው ! እጅግ ምስኪን ማህበረሰብ ነው ።

ሰው ወዳድ ናቸው ፤ እንግዳም ተቀባይ ናቸው ፤ ያላቸውን አውጥተው የሚያስተናግዱ ናቸው። ፍርድ ከላይ ነው ፤ ፍርድ ከአላህ ነው ለዛ ማህበረሰብ ይሄ አይገባውም ነበር።

በሚያሳዝን ሁኔታን የማህበረሰቡን ሮሮ፣ ጩኸት ማን እንደሚሰማው አናውቅም። ጥቃት አድራሾቹን ማን ሃይ እንደሚላቸውም አናቅም።

ለማን አቤት እንደምንል ግራ የሚገባ ነው። ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ነው ባለፈው ከፍ ብሎ ጊምቢ አካባቢ በጣም ብዙ ሰው በተሰመሳሳይ ሁኔታ ተጨፍጭፏል።

ዘር እየተመረጠ ሰው የሚጨፈጨፍበት ጊዜ ላይ ደረስን ፤ ለማን አቤት እንደምንል አናውቅም " - በአከባቢው ቤተሰቦቹ ያሉ የቲክቫህ አባል ከተናገርው በጥቂቱ

ከላይ ያለው መልዕክት እየተላኩት ካሉ በርካታ መልዕክቶች አንዱ ነው። ቤተሰቦቻቸው እዛ ያሉ የቲክቫህ አባላት መልዕክት እየላኩ ነው።

ዛሬ ጭፍጨፋ በተፈፀመበት አካባቢ አስክሬን የመሰብሰብ ስራ እየተሰራ ሲሆን ፤ መከላከያውም በቦታው አለ ተብሏል።

እጅግ በርካታ ሰዎች ፤ ምንም ማያውቁ ምስኪን ህፃናት እና ሴቶችን ጨምሮ የተጨፈጨፉት። በርካቶች ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ መቻራ መሄዳቸውን ለማውቅም ተችሏል።

አሁንም አጠቃላይ ቀጠናውን ደህንነት ማረጋገጥ ካልተቻለ ሌላ ጥቃት ይፈፀማል የሚል ስጋት አይሏል።

(ውድ ቤተሰቦቻችን መልዕክቶችን አደራጅተን እንደጨረስን እንልካለን)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከሟቾች መካከል ሴቶች እና ህፃናት ይገኙበታል " - የቲክቫህ አባል ዛሬ በቄለም ወለጋ ለምለም ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተጨፍጭፈዋል። እሱና ቤተሰቦቹ በአካባቢው ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ አባል ዛሬ የተፈፀመው ጭፍጨፋ እጅግ በጣም አሳዛኝ እንደነበር ገልፆ በርካታ ሰው ተገድላል፤ ሴቶች እና ህፃናትም ይገኙበታል ብሏል። በአካባቢው ኔትዎርክ ይሰራ ነበር አሁን ላይ እየሰራ አይደለም ቤተሰቦቼ…
" በትንሹ 150 ሰዎች ተገድለዋል "

ቢቢሲ አፍሪካ ዛሬ ማምሻውን ይዞት በወጣው ዘገባ በኦሮሚያ ክልል፣ ሀዋ ገለን ወረዳ በተፈፀመው ጥቃት በትንሹ 150 ሰዎች መገደላቸውን ገልጿል።

ቢቢሲ አፍሪካ ፤ የአይን እማኞች ጥቃቱ በሀዋ ገላን ወረዳ መፈፀሙን እንደገለፁለትና በአካባቢው ላይ በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር አክሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በትንሹ 150 ሰዎች ተገድለዋል " ቢቢሲ አፍሪካ ዛሬ ማምሻውን ይዞት በወጣው ዘገባ በኦሮሚያ ክልል፣ ሀዋ ገለን ወረዳ በተፈፀመው ጥቃት በትንሹ 150 ሰዎች መገደላቸውን ገልጿል። ቢቢሲ አፍሪካ ፤ የአይን እማኞች ጥቃቱ በሀዋ ገላን ወረዳ መፈፀሙን እንደገለፁለትና በአካባቢው ላይ በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር አክሏል። @tikvahethiopia
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን በሃዋ ገላን ወረዳ (መንደር 20 እና መንደር 21) ላይ ቁጥራቸው ያልተረጋገጠ ንፁሀን ዜጎች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ መፈጸሙን ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል።

ኮሚሽኑ ሁኔታውን እየተከታተለ መሆኑና እና ከአካባቢው ተርፈው የሸሹ ሰዎችን ማረጋገሩን አመልክቷል።

ኮሚሽኑ ጥቃቱ ያደረሱት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ሸኔ) አባላት መሆናቸውንና ግድያውም ከጥዋት አንስቶ መጀመሩን ምንጮቼ አመልክተዋል ብሏል።

ኢሰመኮ የመንደር 20 እና መንደር 21 ነዋሪዎች በዋናነት የአማራ ብሄር ተወላጆች መሆናቸውን መረዳቱንም ገልጿል።

የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ወደ አካባቢው መድረሳቸው ተነግሯል ያለው ኢሰመኮ ነዋሪዎቹ ግን ወደ ሌላ ቦታ ሄደው መጠለላቸውን ቀጥለዋል ሲል ሁኔታውን አስረድቷል።

የኢሰመጉ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ " በአካባቢው የቀጠለው የጸጥታ ችግር እና በነዋሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው ብሔር ተኮር ግድያ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲሉ አሳስበዋል።

ተጨማሪ የንፁሃንን ሞት ለመከላከል መንግስት የፀጥታ ኃይሉን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ያለበት እስካሁን አልታወቀም " የገጣሚ በላይ በቀለ ወያ ቤተሰቦች ልጃቸው አሁንም የት እንዳለ ማወቅ እንዳልቻሉ ገልፀዋል። በልጃቸው አድራሻ አለመታወቅ ሳቢያ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የወደቁት ቤተሰቦች ልጃቸውን የወሰደ አካል በሰላም እንዲመልስ እየጠየቁ ይገኛሉ። " ጥፋት ካለበት አይጠየቅ እያልን አይደለም " ያሉት ቤተሰቦቹ መንግስት አስሮትም ከሆነ አድራሻውን እንዲያሳውቃቸው ህግን ባከበረ መልኩ…
#Update

ለቀናት ያህል የት እንደነበር ያልታወቀው ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ ትላንት ምሽት ወደቤቱ መመለሱ ታውቋል።

ገጣሚ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ፤ " ከልዑል እግዚአብሔር ቀጥሎ ላዘናችሁልኝ ፣ ለራራችሁልኝ ፣ ለተጨነቃችሁልኝ ፣ ድምፅ ለሆናችሁኝ ሁሉ ከልቤ አመሠግናለሁ ። በህይወት ወደ ቤቴ ተመልሻለሁ ። ደህና ነኝ " ኢትዮጵያ ለዘልዓለም ትኑር " ሲል ፅፏል።

ገጣሚው በማን ፣ እንዴት እንደተወሰደ እንዲሁም የት እንዳነበረ በዝርዝር አልፃፈም።

ባለፉት 7 ቀናት ያለበት ባለመታወቁ እናት እና አባቱ አጠቃላ ቤተሰቦቹ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ወድቀው እንደነበር እና መንግስትም ሆነ ሌላ አካላ ልጃቸውን በሰላም እንዲመልስላቸው ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#DireDawaUniversity

በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጊዚያዊነት ተመድበው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ነባር ተማሪዎች " ግቢው ውጡ አለን " ሲሉ ቅሬታቸውን አድርሰውናል።

ተማሪዎቹ "ግቢውን ለቀን እንድንወጣ ተነግሮናል"፣ "የምግብ አገልግሎትም ተቋርጦብናል" ሲሉ ቅሬታቸውን ያቀርባሉ።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት መገርሳ ቃሲም (ዶ/ር) ተከታዩን ምላሽ ሰጠውናል።

"መደበኛ ነባር ተማሪዎች በግቢው መቆየት የሚችሉት እስከ ሰኔ 30/2014 ዓ.ም ብቻ ነው። ከሰኔ 30 በኋላ ዩኒቨርሲቲው የክረምት ተማሪዎችን ይቀበላል። በመሆኑም መደበኛ ነባር ተማሪዎችን የምናቆይበት አሰራር የለም።"

"በኮቪድ-19 ምክንያት የተደራረቡና የምንቀበላቸው 5 ሺህ የሚሆኑ የክረምት ተማሪዎች አሉብን። በቅርቡ የተቀበልናቸው የመጀመሪያ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች በግቢው ውስጥ ነው የሚገኙት። ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ የበጀት እጥረት ገጥሞናል።"

በመሆኑም ሁሉም መደበኛ ነባር ተማሪዎች ግቢውን ለቀው እንዲወጡ መወሰኑን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

ተቋሙ በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት ነው የሚሰራው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተማሪዎቹ የዩኒቨርሲቲውን ውሳኔ ሊያከብሩ ይገባል ብለዋል።

More : @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#SUDAN #DrWorknehGebeyhu የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በሱዳን የአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ዋና ፀሀፊው በስራ ጉብኝታቸው ከሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን አሳውቀዋል። በውይይቱ ኢጋድ ማክሰኞ ዕለት በኬንያ፣ ናይሮቢ…
#Update

እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት ይደረጋል ያተባለው የኢጋድ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል።

በዚሁ ስብሰባ ላይ የአባል ሀገራት መሪዎች ናይሮቢ እየገቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል።

ናይሮቢ ከደረሱ መሪዎች መካከል የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የሱዳኑ ወታደራዊ አስተዳደር መሪ እና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ይጠቀሳሉ።

ከኢጋድ ስብሰባ ጎን ለጎን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን በወቅታዊ ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

የዛሬው የኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት የሚደረግ ስብሰባ ሲሆን የቀጣናው ጉዳይ ላይ በመሪዎች አማካኝነት ይመከርበታል።

መሪዎች ቀጠናውን በሚያሳስቡ ጉዳዮች ላይ ፣ ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት ስለሆኑ ጉዳዮች ፣ በድርቁ ሁኔታ ላይ በጥልቀት ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Photo Credit : IGAD & PMOEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#SUDAN

ሲቪል አስተዳደሩን ገልብጠው ሙሉ በሙሉ ስልጣን ከተቆጣጠሩ ጊዜ አንስቶ በሱዳናውያን ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ እያስተናገዱ ያሉት ሌ/ጄነራል አብዳልፈታህ አልቡርሃን ጦሩ ቦታውን እንደሚለቅ ተናግረዋል።

ትላንት ሰኞ ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን በቴሌቫዥን ቀርበው የሱዳን ጦር ኃይል አገሪቱ ወደ ሲቪል አስተዳደር እንድትመለስ ለማድረግ ቦታውን ይለቃል ብለዋል።

የአገሪቱ ጦር ኃይል ሱዳን ወደ ዴሞክራሲ ለምታደርገው ሽግግር እንቅፋት እንደማይሆንና ምርጫ እንዲደረግ ወስኖ እየሰራ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ጨምረውም በአገሪቱ ያለውን ፖለቲካዊ ቀውስ ለማብቃት ከሲቪል ቡድኖች ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ ጦር ሠራዊቱ የሚያደርገውን ተሳትፎ እንደሚያቋርጥ አሳውቀዋል።

ነገር ግን አገሪቱ ውስጥ ምርጫ ስለሚደረግበት እንዲሁም ጦር ኃይሉ ሥልጣን ስለሚያስረክብበት ሂደት የጊዜ ሰሌዳ ምንም አላሉም።

በሱዳን ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲመሰረት የሚጠይቁት ተቃዋሚ ሰልፈኞች ሠራዊቱ ከፖለቲካው እንዲወጣ በመጠየቅ ለወራት የዘለቀ ተቃውሞ ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወሳል ሲል ቢቢሲ ፅፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ችሎት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በ100 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቅ በፍርድ ቤት ብይን ተሰጠ። የ ሳምንታዊው “ ፍትሕ ” መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የ100 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ ጉዳዩን በውጭ ሆኖ እንዲከታተል የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብይን ተሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ብይኑን በአብላጫ ድምጽ ያስተላለፈው በዐቃቤ ህግ በኩል የቀረበውን መቃወሚያ ውድቅ በማድረግ…
" ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አልተፈታም " - ቤተሰቦቹ

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቤተሰቦች ፖሊስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን እንዲያከበር ጠየቁ።

ትናንት ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም 1ኛ የፀረ ሽብርና የህገ መንግስት ጉዳዮች የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በ100 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ከእስር እንዲፈታ መወሰኑ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎም ቤተሰቦቹ ለዋስትና የተጠየቀውን ብር አስይዘው የመፈቻ ወረቀቱን ይዘው አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን (ሦስተኛ) ቢሄዱም ፍቺውን የሚያስፈፅም አካል ባለመኖሩ ፖሊስ ጋዜጠኛ ተመስገንን ሳይፈታው እንዳሳደረው ገልፀዋል።

በዛሬው ዕለትም ቤተሰቦቹ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን (ሦስተኛ) ቢገኙም እስካሁኑ ሰዓት ድረስ አራት የሚሆኑ መርማሪ ፖሊሶች፥ የመርማሪ ፖሊስ ሀላፊዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነሩን ማግኘት እንዳልቻሉ ገልፀዋል።

በዚህም እስካሁን ድረስ ፍርድ ቤቱ የወሰነው የፍቺ ጉዳይ መቋጫ አላገኘም ብለዋል።

የሚመለከታቸው አካላት ህግ እና የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲከበር ጫና እንዲፈጥሩ ጠይቀዋል።

Via Tariku Desalgn

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት ይደረጋል ያተባለው የኢጋድ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል። በዚሁ ስብሰባ ላይ የአባል ሀገራት መሪዎች ናይሮቢ እየገቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። ናይሮቢ ከደረሱ መሪዎች መካከል የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የሱዳኑ ወታደራዊ አስተዳደር መሪ እና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ይጠቀሳሉ። ከኢጋድ ስብሰባ ጎን ለጎን ጠ/ሚ ዶ/ር…
#SUDAN #ETHIOPIA

የኢትዮጵያ እና የሱዳን ጉዳይ !

ኢትዮጵያ እና ሱዳን በመካከላቸው ያሉ ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸው ገለፁ።

ኬንያ ፤ ናይሮቢ የሚገኙት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከጄኔራል አብዱል ፈታሕ አል-ቡርሃን ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " ሁለቱ ሀገራት በሰላማዊ መንገድ ሊሠሩባቸው የሚችሉ በርካታ የትብብር መሠረቶች እንዳሏቸው አረጋግጠናል " ብለዋል።

" ያለን ትሥሥር ከየትኛውም መከፋፈል የሚበልጥ ነው " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " ሁለታችንም ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮችን #በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታችንን ገልጸናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
#ዝርፊያ

የኤሌክትሮኒክ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ዜጎች በተለያየ ጊዜ ዘረፋን ጨምሮ እስከ ግድያ የሚደረስ ወንጀል ይፈፀምባቸዋል።

ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት ሲፈፀም ሰምተናል።

ከሰሞኑን አንድ በዚሁ በኤሌክቶኒክ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ሚሰራ ሰራተኛ ዝርፊያ እንደተፈፀመበት አመክቷል።

ስሙ ሚኪያስ ተፈሪ የተባለው ወንድማችን ራሱንና ቤተሰቡን ለማስተዳደር የሚሰራባትን መኪና ይዞ ቆሞ ሥራ ሲጠባበቅ ነበር (ባለፈው ረቡዕ ምሽት)።

ከአገግልሎት ሰጪ ድርጅቱ ተደውሎ ከሳሪስ ጀሞ ሥራ እንዲሄድ ይጠየቃል ፤ የድርጅቱን ትእዛዝ ተቀብሎ ሦስት ሰዎችን አሳፍሮ ወደታዘዘበት ጀሞ ይሄዳል።

ደንበኞቹ ያሉበት ጀሞ ደረሱ። " ሂሳብ ስንት ቆጠረ?" ብለው ጠየቁ። ሂሳቡን ነገራቸው። እነርሱ ግን በያዙት ስለት አስፈራርተው መኪናውን ነጥቀው ተሰውሩ።

ሚኪያስ ቤተሰቡን የሚያስተዳድርበትን መኪና በዚህ መንገድ ተነጥቋል። ሚኪያስ ለፖሊስ ጣቢያ ድርጊቱን አሳውቋል። እስከዛሬ ሰኞ ድረስ አንዳችም ፍንጭ አልተሰማ።

መኪናው ከላይ በፎቶው የተያያዘ ሲሆን ታፋልጉት ዘንድ ጥሪ አቅርቧል ፤ (0922875988)

በሌላ በኩል ፤ በመሰል ስራ ላይ እራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን የሚያስተዳድሩ ወገኖች በተደጋጋሚ የሚሰሙት ዝርፊ እና ወንጀል ለስራቸው ስጋትን እየፈጠረ መሆኑን በመግለፅ የደህንነት ጉዳይ ይታሰብበት ፤ ወንጀለኞችንም ተከታትሎ አድኖ መያዝ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopia
#AASTU

የጸጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች የመጡ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች " ትምህርት ስለተጠናቀቀ ግቢውን ለቃችሁ ውጡ እንደተባሉና ችግር ላይ መሆናቸውን" ገልጸውልናል።

በተለይ ከትግራይ ክልል የመጡ የቅድመ እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመመለስ ትራንስፖርት አለመኖሩ እንዲሁም ሌሎች ምክንያቶችን በማንሳት መቸገራቸውን ያስረዳሉ።

በጉዳዩ ዙሪያ የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም ዐቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር አለምእሸት ገብረወልድ ተከታዩን ምላሽ ሰጠውናል።

"መደበኛ ነባር ተማሪዎች እስካሁን በግቢው ነው የሚገኙት። ማንም የወጣ ተማሪ የለም።"

"የዩኒቨርሲቲው አመራሮች በጉዳዩ ዙሪያ እየመከሩ ነው። የትኞቹ ተማሪዎች ናቸው መቆየት ያለባቸው በሚለው ላይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እየተወያዩ ነው።"

"ዩኒቨርሲቲው የጸጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎች የትኞቹ ናቸው የሚለውን ማጣራት ካደረገ በኋላ ውሳኔው እንደሚያሳውቅ" ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

More : @tikvahuniversity
የነዳጅ ድጎማ !

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በአዲሱ የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ሥርአት ተጠቃሚ የማይሆኑ ተቋማትና ተሽከርካሪዎች በ4 ወራት ጊዜ ውስጥ ከመንግሥት የሚያገኙት የነዳጅ ድጎማ ሙሉ ለሙሉ ተነስቶ ዋጋውን ራሳቸው እንደሚሸፍኑ አስታውቋል።

ለ3 ወራት ግን መንግስት ከሚገዙት ነዳጅ ውስጥ ከ25 እስከ 75 በመቶ ዋጋ እንደሚደጉም ዛሬ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተነግሯል።

በሌላ በኩል ፤ ድጎማ የሚደረግላቸው የሕዝብ ትራንስፖርት ሰጪ ተሽከርካሪዎች ድጎማ ደግሞ በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ እንደሚነሳ ተገልጿል።

በዚህም መንግሥት በየስድስት ወሩ ተፈፃሚ በሚያደርገው ሥርዓት መሰረት 10 በመቶ ድጎማን እያነሳ የሚሄድ ሲሆን በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ በድጎማ የሚደገፋ የሕዝብ ትራንስፖርት ሰጪ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ የሚወጡ ይሆናል ተብሏል።

መረጃው የኢትዮ ንግድ እና ኢንቨስትመንት መድረክ እና WMCC ነው።

@tikvahethiopia