TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት ይደረጋል ያተባለው የኢጋድ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል። በዚሁ ስብሰባ ላይ የአባል ሀገራት መሪዎች ናይሮቢ እየገቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። ናይሮቢ ከደረሱ መሪዎች መካከል የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የሱዳኑ ወታደራዊ አስተዳደር መሪ እና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ይጠቀሳሉ። ከኢጋድ ስብሰባ ጎን ለጎን ጠ/ሚ ዶ/ር…
#SUDAN #ETHIOPIA

የኢትዮጵያ እና የሱዳን ጉዳይ !

ኢትዮጵያ እና ሱዳን በመካከላቸው ያሉ ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸው ገለፁ።

ኬንያ ፤ ናይሮቢ የሚገኙት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከጄኔራል አብዱል ፈታሕ አል-ቡርሃን ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " ሁለቱ ሀገራት በሰላማዊ መንገድ ሊሠሩባቸው የሚችሉ በርካታ የትብብር መሠረቶች እንዳሏቸው አረጋግጠናል " ብለዋል።

" ያለን ትሥሥር ከየትኛውም መከፋፈል የሚበልጥ ነው " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " ሁለታችንም ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮችን #በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታችንን ገልጸናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia