TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያካሂደውን የሰብል ምርጥ ዘር ስርጭት በመቀጠል በግጭቱ ለተጎዱ 15,000 አርሶ አደር አባወራዎች ድጋፍ አቅርቧል።

አርሶ አደሮቹ በላዕላይ ማይጨው ከሚገኙ 8 ቀበሌዎች እና በማዕከላዊ ትግራይ ዞን በአድዋ ወረዳ ከሚገኙ 4 ቀበሌዎች የመጡ ናቸው። ኮሚቴው ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 10 ኪሎ ግራም የጤፍ ዘር እና 2.5 ኪሎ ግራም የማሽላ ዘር ድጋፍ አድርጓል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
" ገንዘባችንን ተበላን "

ገንዘባችንን ተበላን ያሉ እጅግ በርካታ ወጣቶች የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመልዕክት መቀበያን @tikvahethiopiaBOT አጨናንቀዋል።

እኚሁ አባላት ገንዘባችን ተበላን ያሉት እራሱን ' FIAS 777 ' እያለ በሚጠራው ድርጅት ነው።

ይሄ FIAS 777 የሚባለው " በኮሚሽን የሚሰራ ስራ " በማለት የበርካቶችን ገንዘብ ሲቀበል ነበር።

ስለዚህ FIAS 777 ከዚህ በፊት የቀረበውን ያንብቡ : t.me/tikvahethmagazine/15060

አሁን ላይ እነዚሁ አካላት የበርካቶችን ገንዝብ ተቀብለው ፦
- አድራሻቸውን ማጥፋታቸው
- የቴሌግራም ገፆቻቸውን እና ዌብሳይታቸውን መዝጋታቸውን
- ኤጀንት የሚባሉትን ማግኘት እንዳልተቻለ ተገልጾልናል።

ይሄ ድርጅት ነኝ የሚለው አካል ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ምዝገባ እንዳካሄደ ገልጾ ነበር ሲያስነግር የነበረው ነገር ግን የተመዘገበበት ማስረጃ የለም።

አሁን ላይ ገንዘባችንን ተበላን ያሉ የቴሌግራም ግሩፕ ከፍተው ቀጣይ ማድረግ ስላለባቸው ሂደት እየተነጋገሩ ሲሆን በቁጥራቸው ከ2000 ይልቃል።

አንድ ሰው ከ3 ሺ ብር አንስቶ እስከ 30 ሺ ብር ድረስ ገቢ ያደረገባቸውን የባንክ ማስረጃዎችን መመልከት ችለናል። አንዳንዶች በዚህ ሂደት ተበድረው ጭምር ነው ገንዘብ ሲልኩ የነበሩት።

እነኚሁ አካላት አንድም በዚህ ተደራጅተው ሲሰሩ የነበሩ አከላት እንዲጠየቁና ሌሎችም በመሰል ድርጊቶች እንዳይጨብረበሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ይሄ FIAS 777 የተባለው አድራሻውን ፣ ቢሮው ፣ ኃላፊው ስለማይታወቅ ጉዳዩን ለመከታተልና ለመጠየቅ አልተቻለንም።

ገንዘባቸውን ስለተበሉ አካላት በምን ህግ አግባብ እንደሚታይ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር እንጥራለን።

አሁንም ጥንቃቄ !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ገንዘባችንን ተበላን " ገንዘባችንን ተበላን ያሉ እጅግ በርካታ ወጣቶች የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመልዕክት መቀበያን @tikvahethiopiaBOT አጨናንቀዋል። እኚሁ አባላት ገንዘባችን ተበላን ያሉት እራሱን ' FIAS 777 ' እያለ በሚጠራው ድርጅት ነው። ይሄ FIAS 777 የሚባለው " በኮሚሽን የሚሰራ ስራ " በማለት የበርካቶችን ገንዘብ ሲቀበል ነበር። ስለዚህ FIAS 777 ከዚህ በፊት…
#ተጨማሪ

በ " FIAS 777 " በሚል የሚንቀሳቀሱ አካላት አጭበረበሩን ካሉት መካከል እጅግ በጣም በጥቂቱ ፦

📩 " 40000 ብር ተበልቻለሁ "

📩 " በFIAS እኔም 30 ሺህ ብር ተብልቻለሁ "

📩 " እኔም ገንዘቤን ተበልቻለሁ ፤ ተበድሬ ነበር የገባሁት በሰዎች ጉትጎታ ኤጀንቶቹም አድራሻቸውን አጥፍተዋል "

📩 " በFIAS 777 የተዘረፉ በሚያውቋቸው ኤጀንቶች ላይ ክስ ለመስረት እያተዘጋጁ ነው "

📩 " ዘንድሮ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ የምመረቅ ዘንድሮ ነበር ነገርግን ከቤተሰብ ለመመረቂያ ልብስ ብር አስልኬ fias777 ለተባለ አጭበርባሪ platform ልኬ ምንም ብር ሳይገባልኝ በሉት። ከተቻለ እርምጃ እንዲወሰድበት አሳስባለሁ። በተጨማሪ ሌሎች የማጭበርበሪያ መንገዶችን ለምሳሌ ፦ HDU, DH አና የመሳሰሉ platform እየተጠቀሙ ስለሆነ ማንም እንዳይጭበረበር "

📩 " የመንግስት ያለህ እኛ የFIAS ተጠቃሚወች ድርጅቱ ሀገረ መንግስቱ እውቅና የሰጠው ነው ተብለን ነው የገባንበት ሊንኩ ከተዘጋ ጀምሮ ገንዘብ ገቢና ወጭ እሚያደርጉልን ኤጀንቶች ቴሌግራም አካውንታቸውን ድሌት አርገው ከኛ ጋ የተጻጻፋትን አጥፍተው ነው ውሀ ሽታ የሆኑት በመቶ ሽወች የሚቆጠር ገንዘብ vIP Upgrade ያደረጉ ልጆች እያበዱ ነው። "

📩 " እዚህ ኢትዮጵያ ሲያስተባብሩ የነበሩት ይታወቃሉ ፤ ልብስ ለብሰው በአደባባይ ሲታዩም ነበር ፤ እንዴት እና ገንዘቡን የት እንዳደረሱት ይጠየቁ "

📩 " 30 ሽህ ብር አንድ ብር ሳላወጣ ተበልቻለው ባንክ የከፈልኩበትን ደረሰኝ ማቅረብ እችላለሁ "

📩 " በሰው በሰው ገብቼ 30 ሺህ ብር ተበልቻለሁ ፤ ስለድርጅቱ አንዳች ነገር አላውቅም "

📩 " እሄ website በ internet ነው እሚሰራው ግባ ብሎ በማላቀዉ ነገር fias 777 lay ኣስገብተዉ አሁን ላይ እስከ100 ሺህ ሚገመት ብር ከሰዉ ኣስበድረው ኣስበልተውኛል:: የ bank full መረጃ አለኝ "

📩 " ህጋዊ በመምሰል በጦርነት እና በዚህ በኑሮ ውድነት የሚሠቃየውን ሚስኪኑን ማህበረሰባችንን ዘርፎ ስለጠፋው fias777 ስለሚባል ድርጅት መናገር ፈልጋለሁ። አብዛኛው ሰው ትርፋ አገኛለሁ በሚል መንፈስ ከሰው በመበዴር፣ መሬት በመሸጥ፣ ቋሚ ንብረቶቹን ሳይቀር በመሸጥ ለዚህ ድርጂት መጀመሪያ አካባቢ ከ1000 እስከ 30,000 ብር ገቢ ያዴረጉ ሲሆን አሁን በቅርቡ ሊዘጉት አካባቢ ዴግሞ እስከ 180,000 ብር ድረስ ለዚህ ድርጅት ገንዘባቸውን ገቢ በማድረግ ገንዘባቸው የውሀ ሽታ ሁንዋል "

(ውድ ቤተሰቦቻችን ፦ ይህ ከብዙ በጥቂቱ ከተላኩት ውስጥ የቀረበ ሲሆን አብዛኛው ሰው በሰው በሰው መግባቱን እና አሁን ስራውን እንሰራለን የሚሉ አካላት መጥፋታቸውን የሚጠቁም ነው ፤ ተበላ የተባለው ገንዘብም እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው። የሚመለከተው አካል ገንዘብ ገቢ በተደረገባቸው አካውንቶች መሰረት ሰዎችን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።)

ከዚህ በፊት በኦንላይን በሚሰራ ስራ በርካታ ትርፍ እናስገኛለን እያሉ ስለሚንቀሳቀሱ አከላት ጥንቃቄ እንዲደረግ መልዕክት መተላለፉ የሚዘነጋ አይደለም ፤ አሁንም በሌላ ስም የሚንቀሳቀሱ አሉ ጥንቃቄ ይደረግ።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ

" FIAS 777 " የተባለ ሰዎችን ትርፋማ አደርጋለው በሚል ከበርካቶች ኤጀንት በሚላቸው አካላት በኩል ገንዘብ ሲሰበስብ ከርሞ ዛሬ አድራሻውን ጥፍትፍት አድርጓል።

#ሌሎችም፦ መሰል ስራ የሚሰሩ አሉ፤ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ ከዚህ በፊት ያሰራጨነውን በድጋሚ ለማቅረብ ወደድን ፦

#REPOST

" የተለያዩ ገንዘብ የማግኛ ማትረፊያ መንገዶች " እየተባለ በዲጅታል ሚዲያው በኩል ከቀርብ ጊዜ ወዲህ በርካቶች እጅግ በስፋት እየተከሰቱ ነው።

እነዚህ አካላት ፍቃድ ይኑራቸው አይኑራቸው ፤ የመስሪያ አድራሻቸው ይታወቅ አይታወቅ ፣ የሚመራቸው / የሚያስተባብራቸው ግለሰብ ይኑር አይኑር የሚለውን በግልፅ ለማወቅ አዳጋች ነው።

ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ከዚህ በፊትም እንዳልናችሁ ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችል እንቅስቃሴ ውስጥ ስትገቡ / ኢንቨስት ስታደርጉ እነዚህ ጥያቄዎች እንድትጠይቁ አደራ እንላለን ፦

1. ድርጅቱ / ተቋሙ እውቅና ያለው ፣ ፍቃድ ያለው ነው ? የሚሰራበትን ፍቃድ በይፋ አሳውቋል ?

2. በትክክል የሚታወቅ አድራሻቸው የት ነው ? ቢሯቸው ?

3. ለሚደርስብኝ ማንኛውም አይነት ነገር ማንን ተጠያቂ ማድረግ እችላለው ?

4. የሚሰራው ስራ ምን ያህል ቀጣይነት አለው ? ነገ እንደማይቆም ምን ማስተማመኛ አለ ? ይህንን ማንስተማመኛ ማን ይሰጠኛል ? የሚሉ ጥያቄዎችን መጠየቅ ያስፈልጋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የማጭበርበር እና የማታለል ድርጊቶች እየሰፉ በመሆናቸው ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

ብዙሃንን ሊጠቅም ያሚችል ማንኛውም ህጋዊ ስራ በሚስጥር፣ በድብቅ ፈፅሞ ሊሰራ አይችልም እና ውድ ቤተሰቦቻችን ማንኛውም እንቅስቃሴ ስትጀምሩ ከላይ የተዘረዘሩ ጥያቄዎችን በቅድሚያ መልስ እንዳያገኙ አድርጉ።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UN የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምዕራብ ወለጋ የተፈጸመውን አሰቃቂ የጅምላ ግድያ ላይ ባለሥልጣናት ፈጣን፣ ገለልተኛ እና ጥልቅ ምርመራ እንዲያካሂዱ ጠየቀ። የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ኃላፊ ሚሼል ባችሌት " በቶሌ መንደር የተፈጸመው የጭካኔ ግድያ እና የነዋሪዎች በጥቃቱ ምክንያት ተገድዶ መፈናቀል ዘግንኖኛል " ብለዋል። ቅዳሜ ዕለት ምዕራብ ኦሮሚያ ውስጥ የተፈጸመው ጥቃት እማኝን ባልደረባቸው እንዳነጋገሩ…
#Update

ከሰሞኑን ጥቃት የተፈፀመበት የምዕራብ ኦሮሚያ ጊምቢ ወረዳ ሁኔታ ምን ይመስላል ? የህብረተሰቡስ ጥያቄ ምንድነው ?

(ከምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ቲክቫህ አባላት)

- አባሴና ወደ ተባለበት አካባቢ አልፎ አልፎ የተኩስ ድምፅ ይሰማል።

- በሰኔ 11ዱ ጥቃት የተጎዱ ሪፈር እየተደረጉ ነው።

- እስካሁን (ዛሬ ጥዋት ድረስ) በህይወት ለተረፉ ወገኖች በበቂ ደረጃ አስፈላጊ እርዳታ አልደረሰም።

- በመጠለያ ያሉ ወገኖች ወደ አርጆ ጉደቱ ውስዱን ቢሉም መከላከያ እኛ እያለን ምንም አይፈጠርም ብሏል፤ አሁን የጥቃት ስጋት ባይኖርም መከላከያው ከወጣ ታጣቂዎች ተመልሰው መጥተው ጥቃት ሊያደርሱ ይችላሉ የሚል ስጋት አለ። ህብረተሰቡ መከላከያ በመኖሩ ከስጋት ነፃ ቢሆንም መከላከያው አረጋግቻለሁ ብሎ ከወጣ ሌላ ጥቃት ሊፈፀም ይችላል የሚል ስጋት አለው።

- ማህበረሰቡ ወደበፊት ቦታ ለመመለስ ሌላ ጥቃት እንደማይደርስብን ምን ዋስትና አለን ? በተጨማሪ በባለፈው ሰኔ 11 ጥቃት ያየነው ነገር እንድንመልስ የሚያደርግ አይደለም ብሏል። ገበሬውም ለምንድነው ገብተን የምናርሰው ተመልሰው መጥተው ጥቃት ያደርሱብናል የሚል ስጋት አለው።

- የተጠያቂነትን ጉዳይ በተመለከተ ደግሞ አካባቢውን ከሚያስተዳድሩት አንዳቸውም በክልል፣ በዞን ፣ በወረዳ፣ ደረጃ መጠየቃቸውን አልሰማንም። የዞን እና የወረዳ አካላት የፀጥታ ችግር እንዳለ ያውቃሉ ፣ ማህበረሰቡም እየፈራ ነበር ወደ ፌደራል ወደላይ አካል ሪፖርት የሚያደርግ አልነበረም። አይደለም ሊጠየቁ ስምምነት ያላቸው ነው የሚመስለን ፤ ለስም መንግስት የሾማቸው ነገር ግን ተገዢነታቸው ለታጣቂዎቹ ነው የሚመስለው።

- ፍትህ ሚወርደው ከታች እስከላይ ያሉ ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ አካላት ሲጠየቁ ብቻ ነው። ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀውን ቡድን የሚረዳ አካል አለ ፤ እነሱን መጠየቅ ሳይቻል እንዴት ፍትህ ይሰፍናል ?

- አሁንም ፤ ከነነፍሳቸው #ወደጫካ ይዘዋቸው የሄዱ ህፃናት፣ ወጣቶች ብዙ አሉ። እነዛ እስካሁን በህይወት ይኑሩ አይኑሩ የሚታወቅ ነገር የለም። አንዳንዶቹ መከላከያ ወደጫካው እየገባ እየተታኮሰ ሲሄድ ሬሳቸው ተገኝቷል።

- አሁን ድረስ ሰፈር ውስጥ ያልተገኙ ብዙ ሰዎች አሉ፤ እንትና የታለ እየተባለ ሲጠየቅ የሌለው ብዙነው። አስክሬናቸው ያልተገኘ በህይወትም በአካባቢው የሌሉ ፤ ወደጫካ ተተወሰዱ ናቸው።

- ታጣቂዎቹ ከመንግስት የፀጥታ ኃይል በላይ ሆነው አይደለም ፤ ነገር ግን የሚረዳቸው የሚደግፋቸው አካል አለ፤ ይሄ ሁሉ አመት እንዲህ ስቃይ የበዛው ከጀርባ የሚደግፋቸው በመኖሩ ነው። በተለይ ደግሞ የአካባቢው የፀጥታ ኃይል አንዳችም የሚያደርገው ነገር የለም ፤ መከላከያው ሲመጣ ነው ሁኔታዎች የሚቀየሩት።

- ማህበረሰቡ መጀመሪያም ታጣቂዎች በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱ አሳውቆ ነበር። ከቶሌ እስከ ጉተን መስመር ድረስ እየመጡ እየተዝናኑ ወደጫካ ይመለሱ ነበር ፤ አንድ አሸባሪ የተባለ የታጠቀ ኃይል ንፁሃን ያሉበት አልያም አስተዳድራለሁ የምትለው ግዛት ውስጥ ገብቶ እንደፈለገ ሆኖ ሲወጣ እርምጃ ካልወሰድክ ትርጉሙ ሌላ ነው።

- ታጣቂዎች ጥቃት እየፈፀሙ ያሉት በጥላቻ ፣ ባለፈ ታሪክ ተነስቶ በብቀላ መንፈስ ነው፤ እንጂ አንድም የስልጣን ሆነ የፖለቲካ ግብ ያላቸው አይመስልም። ስልጣን ይዞ ለማስተዳደር ከሆነ የሚያስተዳድሩትን ማህበረሰብ አይገድሉም።

- አሁን የሟቾች ቁጥርን በተመለከተ የተለያዩ ቁጥር መውጣቱ በጫካ የተገደሉትን ፣ አስክሬናቸውን ያልተገኘ በመኖሩ ነው እስካሁን ግን የሰፈሩ ሰው ወደ 600 አካባቢ መቅበሩን ገልጿል። ገና ግን ያልተገኙ አሉ።

- መንግስት በሽብርተኛ ድርጅትነት የፈረጀው " ሸኔ " ያለምንም ድብብቆሽ በግልፅ ነበር ሲኖር የነበረው። ዬሳዲምቱ ላይ እራሱ ካምፕ ነበራቸው በግልፅ ነው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ክልሉ ይህ ሁሉ ሲሆን አያውቅም ማለት አይቻልም። የቀበሌ ሊቀመንበር በታጣቂዎች ተይዞ እየተገረፈ ፤ ያሉበትም ሚንቀሳቀሱበትም እያታወቀ መፍትሄ አለመሰጠቱ ድጋፍ እንዳለው ማሳያ ነው።

- አሁን ላይ የተለያዩ የዓለም አቀፍ ተቋማት ለአብነት እንደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት አይነት መንግስት ላይ ጫና ካላሳደሩ መፍትሄ ይመጣል ብለን አንጠበቅም ፤ እንዲሁ የሰዎች ሞት እንደተለመደ ያልፋል።

* (ሰኔ 11 ቀን 2014 በምዕራብ ወለጋ በተፈፀመው ጥቃት በርካታ ንፁሃን አብዛኛዎቹ ሴቶች እና ህፃናት መገደላቸው ይታወሳል። መንግስት ለግድያው ተጠያቂ ሽብርተኛ ድርጅት ያለውን " ሸኔ " (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) ሲል የታጣቂ ቡድኑ በበኩሉ ጭራሽ በአካባቢው አልነበርኩም ፤ ጥቃቱን የመንግስት ኃይሎች ናቸው የፈፀሙት ሲል ማስተባበሉ ይታወሳል ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምዕራብ ወለጋ የተፈጸመውን አሰቃቂ የጅምላ ግድያ ላይ የመንግስት ባለሥልጣናት ፈጣን፣ ገለልተኛ እና ጥልቅ ምርመራ እንዲያካሂዱ መጠየቁ አይዘነጋም)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ

እንደ FIAS 777 አይነት ሌሎች ተመሳሳይ ስራ የሚሰሩ ስላሉ ገንዘባችሁን እንዳትበሉ አደራ እንላለን።

በተለይ አሁን ያሉብንን ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ተገን በማድረግ በርካታ ወጣቶችን የሚያጭበረብሩ፤ ትንሽ ሰዎች እየከበሩ ሌሎች ብዙሃኑ ባዷቸውን የሚቀሩበት የማታለል ስራዎች በስፋት እየተስተዋለ ነው።

በትንሽ ብር ብዙ ታተርፋላችሁ፣ ዘመናዊ ስራ ነው፣ ከኢኮኖሚ ችግራችሁ በቶሎ ትላቀቃላችሁ እያሉ ወጣቶች ንብረታቸውን ሽጠው፣ ከሰው ተበድረው ገንዘብ ከከፈሉ በኃላ የውሃ ሽታ እየሆነባቸው ነው።

አንድ የቤተሰባችን አባል ልክ FIAS 777 እንደሚባለው አይነት HDUHDU በሚባል ተመሳሳይ ድርጅት እስከ 70,000 የተበሉ የሚያውቃቸው ብዙ ሰዎች መኖራቸውን ጠቁሞ እነዚህም አካላት ዛሬ ደብዛቸውን ማጥፋታቸውን ገልጿል።

አንድ ሌላ የቤተሰባችን አባል በዚህ HDUHDU በሚባለው እስከ 93000 ብር ድረስ የተበሉ ብዙ ጓደኞች እንዳሉት ገልጾ በርካታ ወጣቶች ብዙ ለማግኘት ሲሉ ያላቸውን ገንዘብ እና ጊዜያቸውን እያጡነውና ይጠንቀቁ ብሏል።

ሌሎች ከላይ ከተገለፁት ባለፈ ስም እየቀያየሩ በርካቶችን ገንዘብ የሚቀበሉ በሂደቱ ትንሽ ሰው አትርፎ ብዙሃኑ ያለውን የሚያጣበትን ስርዓት የዘረጉ ስላሉ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ዋነኛዋቹ ሰዎች ውጭ ናቸው እየተባለ የሚነገር ሲሆን ገንዘብ የሚሰበሰበው እዚህ ኢትዮጵያ ባሉ ኤጀንቶች ነው።

ሁሌም ወደ ሆነ እንቅስቃሴ ሲገባ ህጋዊ እና ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ ማጣራት ያስፈልጋል ፤ አሁን አሁን እየመጡ ያሉ ህገወጥ ድርጊቶች የሰዎችን ገንዘብ በመብላት ባለፈ ወዳጆችን እርስ በእርስ እንዲኮራረፉም እያደረገ ነው ፤ ህጋዊ መንገድ ብቻ እንከተል እንላለን።

(ማስረጃዎቻችሁን ለሚመለከታቸው አካላት ለማድረስ እና ምላሽ ካለ ለማሳወቅ እንጥራለን)

@tikvahethiopia
#እገታ

ከኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ወደ አዲስ አበባ እየመጡ የነበሩ 4 የሕዝብ ማመላለሻና 1 የጭነት ተሸከርካሪዎች መታገታቸው ተሰምቷል።

ተሳፋሪዎቹ ከደራ ወረዳ ጉንዶ መስቀል ከተማ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላይ ሳሉ መታገታቸው የተገለፀ ሲሆን እገታው የተፈፀመው በሂደቡአቦቴ ወረዳ ወዘሚ በሚባል መንደር ነው።

የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ ውብሸት አበራ 4 የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችና 1 የጭነት መኪና መታገታቸውን አረጋግጠዋል።

የመንግስት የጸጥታ ኃይል ወደስፍራው መሄዱን ያነሱት አቶ ውብሸት እስካሁን 230 ሰዎች ከእገታው መለቀቃቸውን ተናግረዋል።

በአጠቃላይ በተሸከርካሪዎቹ ውስጥ ምን ይህል ሰዎች እንደተሳፈሩ ከጉንዶ መስቀል መረጃ እየሰበሰቡ እንደሆነ ያነሱት ገልፀው፤ የተለቀቁ ቢኖሩም አሁንም የታገቱ እንዳሉ ማወቃቸውን ተናግረዋል።

እገታው የተፈጸመው መንግስት ሸኔ እራሱን ደግሞ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ በሚጠራው ቡድን እንደሆነም ነው የገለፁት። ተሸከርካሪቹ የታገቱበት አካባቢ በብዛት ቡድኑ የሚንቀሳቀስበት ነው ብለዋል።

አሁን በእገታ ላይ ያሉ ሰዎችን ትክክለኛ ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ መሆኑን ገልፀዋል።

የደራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የታገቱት ሰዎች ጨለንቆ እንደተወሰዱ ገልጸው በስፍራው መንግስት " ሸኔ " እራሱን ደግሞ " የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት " ብሎ የሚጠራው ቡድን #ማሰልጠኛ እንዳለው ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አበበ ገረሱ ይህንን ጉዳይ እንዳልሰሙና በአካባቢው ”ሽፍታ ይንቀሳቀስ ይሆናል” እንጅ ሌላ ችግር የለም ሲሉ ተናግረዋል።

የደራ ፍቼ አዲስ አበባ መንገድ ለ8 ወራት ያህል ተዘግቶ የነበረ ሲሆን አገልግሎት መስጠት የጀመረው በቅርቡ ነው ተብሏል።

ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ

@tikvahethiopia
#WorldBank #Ethiopia

የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር የ600 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍና የብድር ስምምነት መፈራረሙን አገለፀ።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ፥ ከ600 ሚሊየን ዶላሩ ውስጥ 200 ሚሊየን ዶላሩ በድጋፍ መልክ ሲሆን 400 ሚሊየን ዶላሩ በብድር መልክ መሆኑን ገልጿል።

ስምምነቱ በኢትዮጵያ ያለውን የስርአተ ምግብ ለማሻሻል እና የምግብ እጥረት አደጋን ለመቀነስ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#ተራኪ

የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ - ሙሉ የመጽሐፍ ትረካ 🎧

17 ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ ታሪኮች ከራሱ ከልብ ጠጋኙ ዶክተር ፈቀደ አግዋር በማስታወሻነት ቀርቦላቿል። ሙሉ የመጽሐፉን ትረካ፤ ተራኪ ላይ ያድምጡ!

ተራኪ - መተግበሪያን ከጉግል ፕሌስቶር እና አፕ ስቶር ላይ ያውርዱ!
⬇️Google Play | ጉግል ፕሌስቶር - bit.ly/3CTALq3
⬇️App Store | አፕ ስቶር - https://apple.co/3AVp0i3
Telegram - https://publielectoral.lat/terakiapp
☎️ አብረውን መስራት ለሚፈለጉ ደራሲያን በ +251920958300 | +251911637874