TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"...ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ለመርዳት ተጨማሪ ጥረት መደረግ ይኖርበታል" - የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC)

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በመተባበር በግጭት ለተጎዱ በሺዎች ለሚቆጠሩ ቤተሰቦች የውኃ፣ ምግብ እና መሰረታዊ ቁሳቁሶች አቅርቦት ላይ እየሰሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።

በዚህ መሰረትም በቀርቡ በአፋር ክልል ከ16,000 በላይ ለሆኑ ሰዎች የመሰረታዊ የቤት ውስጥ ቁሳቁስ አከፋፍለዋል፡፡

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ለመርዳት ተጨማሪ ጥረት መደረግ ይኖርበታል ብሏል።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የአፍሪካ ቀጠና ዳይሬክተር ፓትሪክ ዩሱፍ ፥ “የግጭቱ ውጤት በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ክልሎች ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ነው፡፡ እኔም የሚደርሰው ጉዳት በጣም አሳስቦኛል፡፡ የተፈናቀሉ ሰዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እየኖሩ ይገኛሉ፡፡ አንዳንዶቹ በጣም በተጨናነቁ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ነው የሚተኙት ሌሎቹ ደግሞ በጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ እየኖሩ ነው” ብለዋል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
ICRC በደሴ ድጋፍ እያደረገ ነው።

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት ከቆቦ፣ ወልዲያ፣ መርሳ እና ላሊበላ ተፈናቅለው በደሴ ከተማ ተጠልለው ለሚገኙ 36,000 ሰዎች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁስ ፣ የንጽህና መጠበቂያዎችን እና መጠለያን ያካተተ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
ICRC ለቄለም ወለጋ ዞን ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረገ።

ባሳለፍነው ሳምንት ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ወይም በምዕፃረ ቃሉ #አሲአርሲ በደንቢዶሎ በመገኘት ከ2 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ በግጭት የተጎዱ እና ከቄለም ወለጋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።

የተደረገው ድጋፍ የገንዘብ ድጋድ ሲሆን በአባወራዎች እና በሴቶች የሚመሩ ቤተሰቦች መሠረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት እንዲረዳቸው የታሰበ መሆኑ ተገልጿል።

ICRC አሁን ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ ሁለተኛ ዙር እንደሆነ ገልጿል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
#ICRCEthiopia

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተው ግጭት በርካታ ሰዎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እንዳይኖራቸው አድርጓል።

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ #በንፋስ_መውጫ አካባቢ የተጎዳውን የውሃ አቅርቦት ለመጠገን የሚረዱ ቁሳቁሶችን ማቅረቡን አሳውቋል።

በዚህም ከ50 ሺ በላይ የሚሆኑ በደቡብ ጎንደር የሚገኙ በብጥብጥ የተጎዱ ሰዎች የውሃ አቅርቦት እንደሚኖራቸው አይሲአርሲ ጠቁሟል።

@tikvahethiopia
#Tigray : ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ (አይሲአርሲ) በትግራይ ክልል በሆስፒታሎች እና ሌሎች የጤና ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ 15,000 የጤና ሰራተኞች እና ሕሙማን ለ2 ወራት የሚሆን የመሠረታዊ የምግብ አቅርቦቶችን ማሰራጨት መጀመሩን ዛሬ አስታውቋል።

አይሲአርሲ ፥ "ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት ማግኘት እንዲቀጥሉ የሕክምና ሠራተኞችን መደገፍ አስፈላጊ ነው" ብሏል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ : በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት የጤና መሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡

በአማራ ክልል የደብረ ዘቢጥ ጤና ጣቢያ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁሟል፡፡ በዚህም ህሙማን በህክምና እና መድኃኒት እጥረት #እየሞቱ ይገኛሉ፡፡

የህክምና መሰረተ ልማቶች እና ባለሞያዎች የጦርነት ኢላማ መሆን የለባቸውም፡፡

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
#ICRCEthiopia

የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በቅርቡ በኦሮሚያ እና ሱማሌ ክልሎች በሚገኙት በጭናቅሰን እና ቱሊጉሌድ አካባቢዎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።

ICRC ድጋፍ ያደረገው ከ8,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሲሆን ድጋፉ ፦
- የማዕድ ቤት እቃዎች፣
- ምንጣፎች፣
- መጠለያ፣
- ብርድልብስ፣
- ጀሪካኖች፣
- የሶላር መብራቶች እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ነው።

በተመሳሳይም ባለፈው ወር በእነዚሁ አካባቢዎች ከ6,000 በላይ ለሆኑ ሰዎች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁስ እና የገንዘብ ድጋፍ አድርጎ ነበር።

@tikvahethiopia
#Tigray #Amhara

ባለፈው ሳምንት በትግራይ ክልል የሚገኙት የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ቡድኖች በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው በመቐለ ከተማ ለተጠለሉ ከ900 በላይ ለሆኑ ሰዎች የሚያገለግሉ መሰረታዊ የቤት ውስጥ ቁሳቁስ እና የንጽህና መጠበቂያዎችን በድጋፍ አበርክተዋል፡፡

በተጨማሪም የተፈናቀሉት ሰዎች ከተነጣጠሉት የቤተሰብ አባል እና ወዳጆቻቸው ጋር እንዲገናኙ ለማገዝ ከ180 በላይ ነጻ የስልክ ማስደወል አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡

በሌላ በኩል ፦ በአማራ ክልል ላሊበላ ከተማ የሚገኘው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ቡድን ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመተባበር ከ6,000 በላይ ለሆኑ በግጭት ለተጎዱ ሰዎች የቤት ውስጥ መገልገያ እና መጠለያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉ በዋናነት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ነፍሰጡር እና የሚያጠቡ ሴቶች ቅድሚያ የሰጠ ነው፡፡

ተጨማሪ መረጃ ፦ ትላንት የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የኢትዮጵያ ልዑክ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር ያለውን የሰብዓዊ ተግባራት አጋርነት በማደስ እና በማጠናከር እ.ኤ.አ በ2022 ዓ.ም በግጭት እና ብጥብጥ የተጎዱ ሰዎችን በጋራ ለማገዝ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
#ICRCEthiopia

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት በግጭት ለተጎዱ አርሶ አደሮች ድጋፍ ሰጥቷል።

በደቡብ ወሎ ዞን በተሁለደሬ እና በአምባሰል ወረዳዎች ለሚገኙ 10,000 አባወራዎች 10 ኪሎ ግራም የጤፍ ዘር እንዲሁም የእርሻ ግብዓቶችን ለሟሟላት የሚጠቅም የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
#ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያካሂደውን የሰብል ምርጥ ዘር ስርጭት በመቀጠል በግጭቱ ለተጎዱ 15,000 አርሶ አደር አባወራዎች ድጋፍ አቅርቧል።

አርሶ አደሮቹ በላዕላይ ማይጨው ከሚገኙ 8 ቀበሌዎች እና በማዕከላዊ ትግራይ ዞን በአድዋ ወረዳ ከሚገኙ 4 ቀበሌዎች የመጡ ናቸው። ኮሚቴው ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 10 ኪሎ ግራም የጤፍ ዘር እና 2.5 ኪሎ ግራም የማሽላ ዘር ድጋፍ አድርጓል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Tigray , #Mekelle 📍

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) የህክምና ቁሳቁሶችን እና የተለያዩ እንደ የጤፍ ዘር እንዲሁም መሰረታዊ የሆኑ የቤት ቁሳቁሶችን ያካተተ ሰብዓዊ እርዳታውን ይዞ መቐለ፣ ትግራይ ዛሬ ገብቷል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
#Tigray

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ እና ማእከላዊ ዞኖች በግጭት የተጎዱ የውሃ አውታሮችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የውሃ ፓምፖች ፣ ጄኔሬተሮች እና የውሃ ማጣሪያ ኬሚካሎችን በመለገስ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረጉን አሳውቋል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ወደ ትግራይ ክልል በህገወጥ መንገድ ሊያልፍ የነበረ ከ8ነጥብ 8ሚሊዮን ብር በላይ ጥሪ ገንዘብ በቁጥጥር ስር መወሉን የፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል። በሰርዶ የፍተሻ ጣቢያ የሚገኝው የፌዴራል ፖሊስ ፤ በአፋር ክልል በኩል ወደ ትግራይ ክልል የሰብአዊ ድጋፍ ይዞ በመጓዝ ላይ ከነበረ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪ መኪና በህገወጥ መንገድ ሊያልፍ የነበረ ከ8 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሪ ገንዘብ በቁጥጥር…
#ICRCEthiopia

" ካልተፈቀደው ገንዘብ እና እቃዎች ጋር ምንም ግንኙነት የለንም ፤ ድርጊቱንም እናወግዛለን " - ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ሰብአዊ እርዳታ በጫኑ ተሸከርካሪዎች ውስጥ ያልተፈቀደ ጥሬ ገንዘብ እና እቃዎች ማስተላለፍን አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልጿል።

" በአፋር ክልል በሰርዶ ኬላ ጣቢያ ላይ አንድ በኪራይ የመጣ መኪና አሽከርካሪ ገንዘብ እና ሌሎች ያልተፈቀዱ ዕቃዎችን ሲያጓጉዝ የተገኘበት ሰብአዊ እርዳታ የጫነ ተሸከርካሪ በጣም አስፈላጊ የሆኑ የህክምና እና የእርዳታ ቁሳቁሶችን ወደ ትግራይ በማጓጓዝ ላይ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑን አውቃለሁ " ብሏል የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ።

ያልተፈቀደው ገንዘብ እና እቃው በመደበኛው አሰራር ሰብአዊ እርዳታ በጫነው ተሸከርካሪ ላይ በተደረገው ፍተሻ በባለስልጣናት የተገኘ ሲሆን በኪራይ የመጣው መኪና አሽከርካሪም ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር ውሏል ሲልም አስረድቷል።

" የተከራየነው የንግድ መኪና አሽከርካሪ ሰብአዊ እርዳታውን በጣም ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ማጓጓዝ ላይ ብቻ ትኩረት መስጠት ይገባው ነበር " ያለው ኮሚቴው " ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ከዚህ ያልተፈቀደ ገንዘብ እና እቃዎች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፤ ድርጊቱንም አጥብቆ ያወግዛል " ሲል ገልጿል።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በመላው ኢትዮጵያ በትጥቅ ግጭት እና በሌሎች ሁከቶች ምክንያት የተጎዱ ሰዎችን ለመከላከል እና መርዳትን ብቻ የሚፈልግ የሰብአዊ ድርጅት መሆኑም ገልጾ ይህ በኪራይ ያመጣው የከባድ መኪና አሽከርካሪ ያጋጠመው ኹነት በሰብአዊ ተግባሩ እና በአስፈላጊ እርዳታዎች እንቅስቃሴ ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር እየሰራ መሆኑ አሳውቋል።

ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሙሉ በሙሉ በትብብር እየሰራ ስለመሆኑ አስረድቷል።

@tikvahethiopia
#ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ማግኘት ህይወታቸውን እንደሚታደግ ገልጾ ፦ በሐይቅ፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ ኮምቦልቻ፣ አይደር፣ ማይጨው፣ ዓዲግራት፣ መሆኒ፣ ሽሬ፣ ኣክሱም፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ዋድላ፣ ባህር ዳር፣ ደባርቅ፣ ጎንደር፣ ነቀምት፣ ጊምቢ እና ደምቢዶሎ ሆስፒታሎች ያሉትን የአንድ መስኮት የአገልግሎት ማዕከላትን በመደገፍ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

በሌላ በኩል ኮሚቴው በጤና ድንገተኛ አደጋዎች ፈጣን እና ውጤታማ የሆነ ምላሽ ለመስጠት ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር በቅርበት በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ 14 የክልል እና ዞን የኢቀመማ ቅርንጫፎች የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ መሳሪያዎችን እና የአምቡላንስ አቅርቦቶችን ድጋፍ ማድረጉ አሳውቋል።

ከዚህም በተጨማሪ ፤ ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች #ተቀብረው_ሳይፈነዱ_የሚቀሩ ፈንጂዎች በሰዎች አካል ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ የሚገልፀው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ተጎጂዎችን ለመርዳት በኢትዮጵያ ውስጥ በባህር ዳር፣ ደሴ፣ አሶሳ፣ አሰላ፣ ነቀምት፣ አርባምንጭ፣ መናገሻ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ፣ መቐለ እና ኪዩር ሆስፒታል የአካል ማገገሚያ ማዕከላትን በማጠናከር ላይ እንደሆነ ገልጿል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia