TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አላማጣ ቆቦ‼️

የትግራይን ክልል ከአማራ ክልል የሚያገናኘው አላማጣ ቆቦ መስመር ለተሽከርካሪዎች ከተዘጋ 5 ቀናት አስቆጥሯል። መንገዱ የተዘጋው በአላማጣ ከተማ #የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱላቸው በጠየቁ የቆቦ ከተማ ወጣቶች ነው ተብሏል።

የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምርያ እንዳስታወቀው ችግሩን #በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት #ውይይት እየተካሄደ ነው።

የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው - መንገዱ በመዘጋቱ ለስራቸውን #እንቅፋት እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ(የትላንት ምሽት ዘገባ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ቶሌራ አዳባ-ኦነግ‼️

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ እና የኦሮምያ ገዥ ፓርቲ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኦዴፓ/ በመተማመን እና በመግባባት መንፈስ እንደሚሠሩ የኦነግ ቃል አቀባይ አቶ #ቶሌራ_አደባ ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ በትጥቅ ትግል መቀጠል የሚፈልግ ካለ መንግሥት በሰላም አሳምኖ ለመመለስ ጥረት ማድረግ አለበት፤ ካለበለዚያ “መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ግዴታ ስላለበት በወሰነበት መንገድ ሁኔታውን መቆጣጠር ይችላል” ብለዋል።

በኦዴፓና በኦነግ መካከል ሰሞኑን የተደረሰው ስምምነት አዲስ አለመሆኑን የጠቆሙት አቶ ቶሌራ በግንባራቸውና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ሰኔ 1/2010 ዓ.ም. አሥመራ ላይ የተደረሰውን ባለሦስት ነጥብ ስምምነት በፈጠነ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።

የአሥመራው ስምምነት “ኦነግ #በሰላማዊ መንገድ ትግሉን በሃገር ቤት እንዲቀጥል ማድረግ ማስቻል፤ ካለው መንግሥትና በተለይም ከኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት ጋር የኦሮሞን ጉዳይ በተመለከተ መብቱንና ጥቅሙን ለማስከበር በጋራ የሚሠራበትን ሁኔታ በመደጋገፍ መሥራት የሚቻልበትን ሁኔታ ማመቻቸት፤ እንዲሁም የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ታጋዮች ትግላቸውን በመንግሥት ድጋፍ የሚቀጥሉበትን ሁኔታ በመመካከርና በመነጋገር ማመቻቸት” እንደሆነ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ቃል አቀባይ አመልክተዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዩኒቨርሲቲዎች ዳሰሳ 2‼️

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሃገሪቱ እየታየ ያለውን ሰላም ለማስቀጠል እና #ሁከትን ለመቀነስ ውይይት እያካሄዱ ነው፡፡

🔹ደብረ ማርቆስ ዩኒቭርስቲ

የመከላካያ ሚንሰትር ዴኤታ አምባሰደር ዘላለም ገብረ ዮሃንሰን ጨምሮ ከፌዴረል እና ከክልል የተወከሉ የመንግስት አካላት የምስራቅ ጎጃም ዞን እና የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር፣ የሃገረ ሽማግሌዎች ፣የሃማኖት አባቶች እና የጸጥታ አካላት በተገኙበት ምክክር አካሂዷል፡፡

🔹ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ

የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ #ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ከተማሪዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው፡፡የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው የሚነሱ የግጭት መንስኤዎችን ለይቶ ቅድመ መከላከል ለመስራት እና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ከተማሪዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው፡፡

🔹ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ

ከሕዳር 19 ጀምሮ የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ እና ተማሪዎች #በሰላማዊ የመማር ማስተማር ዙሪያ ከፌዴራል በተገኙ አወያዮች ምክክር አድርገዋል፡፡

‹‹የምንማረው ድህነትን በአንድነት ለማሸነፍ እንጂ ተፈጥሯዊ ስጦታዎቻችንን የልዩነት ምንጭ አድርጎ ለመራረቅ አይደለም፡፡›› የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተናገሩት...

‹‹በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን ኢትዮጵያዊነት ለአንድነታችን ማጠናከሪያ፤ ለቁርሾዎቻችን መታረቂያ ምክንያት እንዲሆኑ ጥያቄዎችን የመፍታት ባሕል ማድረግ አለብን፡፡›› አወያዮች ከተናገሩት የተወሰደ...

🔹ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከአማራ ክልል መንግስት እና ከሌሎች አካላት የተወጣጣው የሰላም ኮሚቴ በባሕር ዳር ለ14 ቀናት የሚቆይ ከሰላም መስፈን ጋር የተያያዙ ተግባራትን እየተከታተለ እና እያገዘ መሆኑን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን እና ስታራቴጂክ ኮሚዩኒኬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ዶር. #ዘውዱ_እምሩ ገልጸዋል፡፡

የሰላም ኮሚቴው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደት እና አጠቃላይ በከተማው ያለውን የሰላም ሁኔታ ገምግሟል፡፡ በዚህም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎችን በአግባቡ በመቀበል፣ መረጃ በመስጠት እና #የግጭት_ስጋቶችን በማስወገድ በጎ ስራ መስራቱን ተመላክቷል ነው ያሉት ዶር. ዘውዱ፡፡

‹‹ሰላም ቀላል የሚመስል ነገር ግን የሁላችንም እስትንፋስ ነው፡፡ ለሰላም የበኩላችንን እንወጣ››

‹‹ራሳቸውን አደራጅተው የአካባቢውን ጸጥታ የሚጠብቁ ወጣቶች የተማሪዎች ደህንነት የተጠበቀ እንዲሆን በጎ ስራ ሰርተዋል፡፡›› ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

.
.
©አማራ ብዙሀን መገናኛ ድርጅት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በጉጂ ዞን ይንቀሳቀሱ የነበሩ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር /ኦነግ/አባላት ከጫካ ወጥተው #በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰናቸውን ገለጹ፡፡ በዞኑ ሻኪሶና ጎሮዶላ ወረዳ የትጥቅ ትግል ሀሳብ የነበራቸው 20 የኦነግ አባላት ትጥቃቸውን በማስቀመጥ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ተመልሰዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 17/2011 ዓ.ም.

ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር #በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደሚከበር ተገልጿል፡፡
.
.
ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የዱባይ ማራቶን ጌታነህ ሞላ የቦታውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል። በሴቶች ኬንያውያን እኤአ ከ2006 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸንፈዋል፡፡
.
.

አቶ #በረከት_ስምዖንና አቶ #ታደሰ_ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
.
.
#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ አከናውነዋል።
.
.
በነጭ ሣር ፓርክ ላይ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት እሳት ተነስቶ 1 ሺ ሄክታር የሚሆን የፓርኩ ክፍል ወድሟል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ #የተቀሰቀሰው_ተቃውሞ ዛሬ ጥር 17/2011 ዓ.ም. ቀጥሎ ውሏል። የኢንተርኔት አገልግሎት ተዘግቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2 ዙር በተካሄደ ነፃ የስራ ዘመቻ 3.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ስራ መሰራቱን ተናግሯል።
.
.
የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የ100 ቀናት እቅዱን በአርባምንጭ ከተማ ገምግሟል።
.
.
በሱማሌ ክልል በተፈጠረው ግጭት እጃቸውን በማስገባት ወንጀል ሰርተው ከሀገር የወጡ ባለስልጣናትን ወደሀገር #በመመለስ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከተሸሸጉባቸው ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታውቋል።
.
.
በሳኡዲ አረቢያ በተለያየ ምክንያት ታስረው የነበሩ 368 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ አገራቸው ገብተዋል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የሕዝቡን አብሮነት እና ተቻችሎ የመኖር እሴት የሚሸረሽር በመሆኑ ሰላምን በማወክ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል።
.
.
በኢትዮጵያ #የመጀመሪያ የሆነ የሚዲያ ኤክስፖ በኤግዚብሽን ማዕከል ዛሬ ተከፍቷል።
.
.
የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ አቶ #ጌታቸው_አሰፋን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከክልሉ መንግሥት ጋር እየሰራ እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።
.
.
በጉጂ ዞን ይንቀሳቀሱ የነበሩ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር /ኦነግ/አባላት ከጫካ ወጥተው #በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰናቸውን ገልፀዋል።
.
.
የሱማሌ ክልል መሪ--አቶ #ሙስጠፋ_ኡመር-የፌዴራል ገንዘብ ሚኒስትሩን አቶ #አህመድ_ሺዴን-በይፋ በክልሉ መንግስት ላይ "ዓመፃ-ክህደት በመፈፀም" እጅግ ከባድ ወንጀል #ከሰዋል

ምንጭ፦ አዲስ ስታንዳርድ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ elu፣ ቢቢሲ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

.
.
አመሰግናለሁ! ሰላም እደሩ!!
ሀገራችን ቸር ትደር!!
ጥር 17/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተጠርጣሪዎቹ ከእስር እየተለቀቁ ነው‼️

የድሬደዋ አስተዳደር በቅርቡ በከተማው በተካሄደው ተቃውሞ እና ሁከት ጋር በተያያዘ #ጠረጠርኳቸው በሚል በቁጥጥር ስር ካዋላቸው ከሦስት መቶ በላይ ሰዎች የአብዛኞቹን ክስ በማቋረጥ በነፃ እየለቀቀ ይገኛል። ከቀናት አስር በኃላ በቂ ማስረጃ ባለመኖሩ የተለቀቁ ተጠርጣሪዎችና ቤተሰቦች እንዲሁም ወዳጆች በእምባ ተራጭተዋል፡፡ በከተማው ለቀናት የተከሰተውን ተቃውሞ ተከትሎ የፀጥታ ሀይሉ በወሰደው ሰፊ እርምጃ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን አፍሶ በመያዝ ከአስራ አምስት ቀናት በላይ በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው ሲመረመር ቆይቷል፡፡ ከነዚህ ተጠርጣሪዎች ሁለት መቶ አስራ ስምንት የሚሆኑትን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና ፖሊስ ውሰኔ ክሳቸው ተቋርጦ በነፃ እንዲለቀቁ ተደርጓል፡፡

ከሳምንት በፊት በሀላፊነት የተሾሙት የአስተዳደር ፖሊስ ኮምሽን ኮምሽነር ኮማንደር አለሙ መርጋ ተጠርጣሪዎቹ ስለተለቀቁበት ምክንያት አስረድተዋል፡፡

ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ተጠርጣሪዎችን በመልቀቅ ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ከመልቀቃቸው በፊት ከተጠርጣሪዎች ፣ ከቤተሰብና በነፃ ጥብቅና ቆመው ከነበሩ የህግ ባለሞያዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ኮምሽነሩ ስለውይይቱ ዓላማ ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ ቀናት በተካሄደው በዚህ ውይይት በከተማው የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎ በጅምላ ተይዘው የቆዩ ተጠርጣሪዎች ከድርጊቱ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት ሳይኖር ጭምር መሆኑነንና፣ በምርመራ ሂደትም ከመርማሪዎች ከብቃት ጋር የተያያዙ ችግሮች እንደነበሩ ተነስተዋል፡፡ ወጣቶቹም #በሰላማዊ መንገድ ትግላችንን እንቐጥላለል ብለዋል፡፡

ከህብረተሰቡ ለተነሱት ጉዳዮች በፖሊስ እና ዐቃቤ ህግ በኩል ተወስደው የሚታረሙ መሆኑ ተገልፇል፡፡ በሌላ በኩል ከዚሁ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው ፍ/ቤት ቀርበው ግዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ከነበሩና ዛሬ ፍርድ ቤት ከሚቀርቡ ዘጠና ተጠርጣሪዎች አብዛኞቹን ክስ በማቋረጥ መልቀቃቸው ለፍ/ቤቱ ተገልፃል፡፡

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ 107 ተፎካካሪ ፓርቲዎች #በሰላማዊ_መንገድ ለመፎካከር የሚያስችላቸውን የጋራ የአሰራር የቃልኪዳን ሰነድ ፈርመዋል።

Via Abrha Desta
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጃር ሸንኮራ----ፈንታሌ‼️

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ምንጃር ሸንኮራና በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌና በሦሰት ወረዳዎች መካከል በቦታ እና በግጦሽ መሬት ይገባኛል ምክንያት ሰሞኑን በተፈጠረ ግጭት የሰው ሕይወት መጥፋቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ።፡ መከላከያ ሰራዊት ወደ አካባቢው ገብቶ የማረጋጋት ሥራ እየሠራ መሆኑም ተመልክቷል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአረርቲ ከተማ ነዋሪ በስልክ ለጀርመን ራድዮ እንደተናገሩት በፊትም ከእሳር ግጦሽና ከውኃ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ አልፎ አልፎ ግጭቶች እንደሚስተዋሉ አመልክተዋል።

ባለፉት ሁለት ቀናት በኢዶ፣ ፊናናጆ፣ ቂሌ አርባና ክትቻ በተባሉ አካባቢዎች የታየው ግን ከሁሉም የከፋ ነበር ያሉት እኚህ የዓይን ምስክር ባለፉት 3 ቀናት ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንደነበርና በግጭቱም የሰው ሕይወት ጠፍቷል፤ የአካል ጉዳት ደርሷል፤ ንብረትም ወድሟል ብለዋል፡፡ የመከላከለያ ሰራዊት ወደ አካባቢው በመግባቱ ተኩስ መቆሙንና አሁን አንፃራዊ ሰላም እየታየ እንደሆነም አረጋግጠዋል።

ስለአካባቢው ሁኔታ እንዲስረዱኝ ለምንጃር ሽንኮራን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይትባረክ አብርሀም ሰልክ ደውዬ ጠይቂያቸው ነበር። ነገር ግን ስብሰባ ላይ ነኝ በሚል ዝርዝር መረጃ ለመስጠት አልፈቀዱም።

የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር አቶ መላኩ አላምረው በበኩላቸው ከግጦሽ መሬት ጋር በተያያዘ በአካበቢው ግጭት አልፎ አልፎ እንደሚከሰት ጠቅሰው ይህም የዛው አካል ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡ ሌላ የተለየ ፍላጎት ያለው አካል ነገሩን አባብሶት ከሆነ እንደሚጣራም አስረድተዋል።

በግጭቱ ከአማራ ክልል በኩል ሦስት ሰዎች ተገድለዋል፣ ሌሎች 3 ደግሞ ቆስለዋል ነው ያሉት። በሌላው ወገን በኩል ያለውን ጉዳት እንደማያውቁም ለባህርዳሩ ወኪላችን ዓለምነው መኮንን ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ከኦሮሚያ ክልል ጋር #በሚዋሰንባቸው በምንጃር ሸንኮራ ወረዳና በኦሮሚያ ፈንታሌና ቦሦት አካባቢዎች ተከስቶ የነበረውን ግጭት ለማስቆም መከላከያ ወደ አካባቢው እንዲገባ ተደርጓል። በአሁኑ ሰዓት የኦሮሚያም ሆነ የአማራ የጸጥታ አካላት አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ተደርጓልም ብለዋል።

የአማራ ክልል መንግሥት አሁንም ቢሆን ችግሩ #በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በስምምነት እንጅ #ግጭት በመቀስቀስ ይፈታል ብሎ እንደማምንና በሁለቱም ክልሎች የሚገኙ ኗሪዎችን ባካተተ መልኩ የማያዳግም መፍትሔ እንዲሰጠውም ይሠራል ብለዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት #መፍትሄ ይስጠን...
/የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች/

√በርካታ ተማሪዎች ከዶርማችን ውጪ ላለፉት ቀናት በአዳራሽ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ እያደርን ነው ግቢው በሩን ከፍቶ በሰላም ይሸኘን ሲሉ ተማሪዎች #በሰላማዊ_ሰልፍ እየጠየቁ ይገኛሉ።

ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ምላሽ ካገኘሁ ወደናተ አደርሳለሁ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅማ የቲክቫህ ቤተሰቦች...

"ዛሬ በጅማ ከፍተኛ ተቃውሞ ነበር፤ አክቲቪስትና የOMN ዳይሬክተር ጀዋር መሀመድ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ነው በሚል የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ደምፃቸውን #በሰላማዊ መንገድ ነው ያሰሙት። በአሁን ሰዓት በከተማው የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አልፎ አልፎ ይታያል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"...በምርጫው ዕለት በአገሪቱ ደም ለማፋሰስ የሚፈልጉ ኃይሎች ነበሩ ነገር ግን ሴራቸው ከሽፏል" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫውን #በሰላማዊ መንገድ በማከናወን በእለቱ ደም ለማፋሰስ ያቀዱ ኃይሎችን ሴራ አክሽፏል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ።

ቃል አቀባዩ ይህን ያሉት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው።

አምሳባሳደሩ በምርጫው ወቅት እና ከምርጫ በኋላ በአገሪቱ ደም እንዲፋሰስ የሚፈልጉ ኃይሎች እንደነበሩ አስታውሰዋል።

በምርጫው እለት የነበረውን ሂደት በርካታ አገር አቀፍ እና አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በስፋት ሽፋን የሰጡት መሆኑንም ገልጸዋል።

የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫው ታማኝና ሰላማዊ እንደነበር ማረጋገጡንም አክለው መናገራቸውን ኢዜአ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#NewsAlert

የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ።

በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ።

ዶ/ር ጌዲዮን ፓርቲው ሰላማዊ ውይይት ለማድረግ ዉሳኔ አሳልፏል ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፤ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተካሄደው ጦርነት መንግሥት ተገዶ የገባበት መሆኑን ገልፀው ፤ መንግሥት ይህንን ለመፍታት እየሠራ ስለመሆኑም አስረድተዋል ።

ፓርቲዉ ተጨማሪ ደም መፋሰስ እንዳይኖር ታሳቢ በማድረግ #ለሰላም_ቅድሚያ_ይሰጣል ነው ያሉት።

ዶክተር ጌዲዮን እንዳሉት ፓርቲዉ ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የሰላም አማራጩ፡-

1. ሕገ መንግሥታዊ እና ሕጋዊነትን የሚያስከብር መሆን አለበት፡፡

2. የሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ መሆን አለበት፡፡

3. በሀገር ዉስጥ መፍታት ካልተቻለ #በአፍሪካ_ሕብረት ጉዳዩ መታየት እንዳለበት በሥራ አስፈጻሚ እና በማእከላዊ ኮሚቴ ዉይይት ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል።

በተጨማሪም ትንኮሳዎች ካሉ ሕግ አስከባሪዉ አካል እርምጃ እንዲወሰድ ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። ሕዝቡም ለዚህ ተሳታፊ እንዲሆንም ጥሪ ማስተላለፋቸውን ከአሚኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት ይደረጋል ያተባለው የኢጋድ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል። በዚሁ ስብሰባ ላይ የአባል ሀገራት መሪዎች ናይሮቢ እየገቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። ናይሮቢ ከደረሱ መሪዎች መካከል የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የሱዳኑ ወታደራዊ አስተዳደር መሪ እና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ይጠቀሳሉ። ከኢጋድ ስብሰባ ጎን ለጎን ጠ/ሚ ዶ/ር…
#SUDAN #ETHIOPIA

የኢትዮጵያ እና የሱዳን ጉዳይ !

ኢትዮጵያ እና ሱዳን በመካከላቸው ያሉ ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸው ገለፁ።

ኬንያ ፤ ናይሮቢ የሚገኙት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከጄኔራል አብዱል ፈታሕ አል-ቡርሃን ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " ሁለቱ ሀገራት በሰላማዊ መንገድ ሊሠሩባቸው የሚችሉ በርካታ የትብብር መሠረቶች እንዳሏቸው አረጋግጠናል " ብለዋል።

" ያለን ትሥሥር ከየትኛውም መከፋፈል የሚበልጥ ነው " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " ሁለታችንም ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮችን #በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታችንን ገልጸናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UpdateAU የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመርን ዛሬ ተቀብለው ማነጋገራቸውን በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አሳውቀዋል። ሊቀመንበሩ አምባሳደር ማይክ ሐመርን ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም #በአፍሪካ_ኅብረት_የሚመራውን የሰላም ሂደት ዓለም አቀፍ አጋሮች እንዲደግፉ መስማማታቸውን…
#ETHIOPIA

ዛሬ እና ባለፉት ቀናት ምን ሆነ ?

- የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ከፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረዋል በተጨማሪ ከህወሓት መሪ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋርም በምን አይነት መልኩ  እንደተነጋገሩ ባይታወቅም ተነጋግረዋል (እንደ አሜሪካ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ)። ሐመር ዛሬም እዚሁ አዲስ አበባ ናቸው።

- አምባሳደር ሐመር ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ እና ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ጋር ተወያይተዋል።

- የአፍሪካ ህብረት በኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ላይ " ሙሉ እምነት " እንዳለው ገልጾ ኃላፊነታቸውን አራዝሟል።

- ኦባሳንጆ እና ሙሳ ፋኪ ተገናኝተው ተነጋግረዋል።

- ዛሬ  በአዲሱ ዓመት ደግሞ ከዚህ ቀደም በኦባሳንጆ ላይ እምነት የለኝም ያለው ህወሓት በአፍሪካ ህብረት መሪነት ከፌዴራል መንግስት ጋር እደራደራለሁኝ ሲል መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው ፦

• በአፍሪካ ኅብረት የሚመራ ተዓማኒ የሰላም ሒደት እንጠብቃለን ብሏል።

• በ " አፍሪካ ህብረት መሪነት " ለመደራደር ዝግጁ ነኝ ፤ ለድርድሩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ፣ ለአፋጣኝ እና በሁለቱም ወገኖች ስምምነት ተግባራዊ ለሚደረግ የተኩስ አቁም ዝግጁ ነኝ ብሏል።

• በ2ቱ ወገኖች ተቀባይነት የሚኖራቸው አደራዳሪዎች ፣ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች እና ዓለም አቀፍ ባለሞያዎች በሰላም ሂደቱ ሊሳተፉ ይገባል ብሏል።

• ተደራዳሪዎቹ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳይ እንደሆኑ ገልጾ በፍጥነት ተደራዳሪዎቹን ለመላክ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

• ለዚህ አሳዛኝ ግጭት ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ማምጣት የምንችለው #በሰላማዊ_ውይይት_ብቻ እንደሆነ እርግጠኞች ነን ብሏል።

➣ ዛሬ በ "ህወሓት" በኩል በወጣው መግለጫ ላይ ቅድመ ሁኔታዎች ተብለው የተዘረዘሩ ነጥቦች የሉም።

የ " ህወሓት " ን የዛሬ መግለጫ በተመለከተ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ መንግስት የተባለ ነገር የለም። ነገር ግን ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ መሆኑን በማረጋገጥ ፤ የሰላም ድርድር ኮሚቴውን አባላት በዝርዝር ማሳወቁ አይዘነጋም።

የሰላም ሂደቱ ተፈፃሚ የሚሆነው #በአፍሪካ_ህብረት ጥላ ስር ብቻ እና ብቻ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለፁ ይታወሳል።

በቅርቡ የኢትዮጵያ መንግስት ህወሓት ዳግም ጥቃት መክፈቱን ካሳወቀ በኃላም በተደጋጋሚ ባወጣቸው መግለጫዎች ለሰላም የዘረጋው እጅ እንዳልታጠፈና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ " ህወሓት " ወደ ተከፈተው የሰላም በር እንዲመለስ ግፊት እንዲያደርግ ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ENDF የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ ለህ/ተ/ም/ቤት እንዲላክ ተወሰነ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት አሁን በሥራ ላይ ያለውን የመከላከያ ሰራዊት አዋጅ የሚተካ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ይፀድቅ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል። የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን ውሳኔ ካሰለፈባቸው ጉዳዮች አንዱ የመከላከያ…
" ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን "

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፦

" በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሲካሄዱ የቆዩት ግጭቶች #በሰላማዊ_መንገድ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ፣ በአገሪቱ የልማት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ለማስቻል ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለም/ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡ "

@tikvahethiopia
#እናት #መኢአድ #ኢሕአፓ

ባለፈው ሳምንት ህዳር 27 ቀን 2015 እናት ፓርቲ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የኢትዮጵያ ሕዝቦች አቢዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የትብብር ሰነድ ፈረመዋል።

ስምምነቱ ዋነኛው ተግባር ምንድነው ? ፋይዳውስ ? ስለ ስምምነቱስ በጋራ ምን አሉ ?

" የትብብር ስምምነቱ ፓርቲዎቻችን በሚከተሉት አንኳር ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራና በትብብር እንዲሠሩ ማዕቀፋዊና ሞራላዊ ግዴታ ይጥልባቸዋል፡፡

በሀገራዊ መግባባት፣ በምርጫ፣ በሰላም ማስፈን እና መሰል ጉዳዮች  ላይ የጋራ አቋሞችን በማራመድ #በሰላማዊ_መንገድ በትብብር #እንታገላለን፡፡

በተለይ በየዕለቱ ለሚሞተው እና በድርሱልኝ ሲቃ ለሚቃትተው ወገናችን ድምጽ በመሆን ከገባበት ችግር እንዲላቀቅ መሥራት ከግንባር ቀደም ተግባሮቻችን ዋናው ነው፡፡ "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#OLF50

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር ግንኙነት አለው ?

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ፤ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን አስመልክቶ በሊቀ መንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ አማካኝነት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው  መግለጫ ወቅት ፓርቲው መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ ስለሚጠራው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ኦነሰ) የታጠቀ ቡድን ጋር ግንኙነት ያለው እንደሆነ ማብራሪያ ሰጥቷል።

አቶ ዳውድ ኢብሳ ምን አሉ ?

" የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር አሁን ላይ ግንኙነት አለው ወይ ለሚለው፤ ያ ሰራዊት የፖለቲካ ጥያቄ ያለው ሰራዊት ነው፡፡

አባላቶቹን ለምን እንደሚታገል አስተምሮ ነው ወደ ጦር የሚያሰማራው፡፡

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ደግሞ በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ ይህን ትግል #በሰላማዊ መንገድ እያካሄደ ነው፡፡

ይህ መንግስት አለመግባባቱ በተፈጠረ ጊዜ ኦነግን ገመድ ውስጥ አስገብቶ ሁለት ጥያቄዎችን ነው የጠየቀው፡፡ ትጥቅ አልፈታም ያለው ያ ሰራዊት የኔ ነው ወይስ አይደለም እንድንል፡፡

በወቅቱ ከአባገዳዎች ጋር ሆነን በኦሮሞ ባህል ማዕከል ባደረግነው ጉባኤ መንግስት ስምምነቱን አፍርሷል ብለን በማመናችንና ጦሩን ማስገባት ስርዓት ስላለው እኛ በወቅቱ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን ለአባገዳዎች ሰጥተን ነው ከመሃል የወጣነው፡፡ ከዚያን ቀን ጀምሮ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ከጦሩ ጋር ግንኙነት የለውም፡፡

ያን ተከትሎ በምርጫ ቦርድ በሕጋዊ መሰረት ብንንቀሳቀስም ይሄው ቤት ውስጥ እስከመታገት የሚደርስ ጫና ደርሶብናል፡፡ የኦነግ እንቅስቃሴ ግን በተለያየ መንገድ ቀጥሏል እንጂ አይገታም፡፡

አሁንም የምንጠይቀው መንግስት ሰላም እንዲወርድ ተቀምጦ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ግደታውን ይወጣ።

በኦሮሚያ ለሁሉም ዜጋ እኩል ክብር እንዲሰጥና መከባበር እንዲሰፍን እንጠይቅላለን። "

@tikvahethiopia
#Tigray

የትግራይ አስተዳደር በወቅታዊ ጉዳይ አቋሙ ምንድነው ?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ለማፍረስ ይቋምጣሉ " ያላቸውን በስም ያልጠቀሳቸውን ኃይሎች ዓላማ ለማክሸፍ ከፌዴራሉ መንግሥት ጋር ያለውን ግንኙነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

ይህንን የገለፀው ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ነው።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በስም ያልገለፃቸውና በአማራ ክልል ውስጥ ይገኛሉ ያላቸው ' ፅንፈኛ ' ሲል የጠራቸው ኃይሎችና አጋሮቻቸው " ትግራይ ላይ አሰበዉት የነበረውን የጥፋት አላማ የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዳከሸፈባቸው በአደባባይ የሚያማረሩበት ፤ ብሎም ከፌዴራል መንግስት ጋር ቀጥተኛ ጦርነት ውስጥ የገቡበት ሁኔታ ሲፈጠረ ፀረ ፕሪቶሪያና ፀረ ትግራይ አቋማቸውን በግልፅ በማራገብ ላይ ይገኛሉ " ብሏል።

" ይህን እንቅስቃሴ እንመራለን የሚሉ አመራሮችም ሆኑ አጋሮቻቸው እንዲሁም ያሰማሯቸው የሚድያ አፈቀላጤዎችና የርእዮተ አለም መሪዎች ፣ መከላከያ ሰራዊቱ በመውሰድ ላይ ያለውን እርምጃ ‘የህወሓት ቀጥተኛ ተሳትፎ አለበት’ በሚል በሬ ወለደ ጩኸት እየደረሰባቸው ላለው ሽንፈት የትግራይን ህዝብ ሰበብ ለማድረግ  ሲዳክሩ ይሰማሉ " ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ " የፌዴራል መንግስት በነዚህ ሀይሎች ላይ እየወሰዳቸው ላሉ እርምጃዎች የትግራይንም ሆነ የሌላውን ወገን የተለየ ድጋፍ ያስፈልገዋል ብለን አናምንም " ያለ ሲሆን " ይሁንና ግን ፀረ ሰላም አቋማቸውን ለማራመድ እስኳሁን ሲረጩት የነበረውን መርዝ  አልበቃ ብሎ የትግራይን ህዝብ በትልቁ በትንሹ ቋሚ ስራ አድርገውት ይገኛሉ " ብሏል።

ይህ ዘመቻ በፍፁም አሸናፊ ሊያደርግ አይችልም ፤ በህዝቦች መካከል ሊኖር የሚገባውንም ሰላማዊ ግንኙነት በእጅጉ የሚጎዳ ነው ሲል አሳስቧል።

" አሁንም ቢሆን መላው የትግራይ ህዝብ ሁሉም ችግሮች #በሰላማዊ_መንገድ እንዲፈቱ ያለው ቁርጠኛ አቋም እንደተጠበቀ ነው " ያለው ጊዜያዉ አስተዳደሩ " የፕሪቶሪያውን ስምምነት ለማፍረስ የሚቋምጡ ፅንፈኛ ሀይሎችና የቅርብም የሩቅም አጋሮቻቸው በህዝባችን ላይ የሚያደርጉትን ዘመቻ ለማክሸፍ ከፌዴራል መንግስት እስካሁን ድረስ እያደረግነው የመጣነውን አበረታች ግንኙነት አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል " ሲል አቋሙን ገልጿል።

(መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #USA

ዓለም አቀፍ ለጋሾች ያቆሙት የምግብ ርዳታ ይቀጥል ዘንድ በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና በአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን መካከል የስልክ ውይይት ተደረገ።

የሚኒስቴር መ/ቤቱ ቃል አቀባይ ማት ሚለር እንዳሳወቁት ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር የስልክ ውይይት አድርገዋል።

በዚህ ውይይት ወቅትም ፤ ዓለም አቀፍ ለጋሾች ያቆሙት የምግብ ርዳታ ይቀጥል ዘንድ ፣ የሰብአዊ ሁኔታ ቁጥጥር ተሻሽሎ ስለሚቀጥልበት አሠራር ላይ ተወያይተዋል።

በተጨማሪ አንተኒ ብሊንከን፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ " አሳስቦኛል "  ሲሉ ተናግረዋል።

በሁለቱ ክልሎቹ ያሉትን ችግሮች #በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት፣ የፖለቲካ ውይይትንና የሰብአዊ መብቶች መከበር አስፈላጊነትን አጽንዖት ሰጥተውበታል።

እውነተኛ ፣ ታማኝ እና ሁሉን አካታች የሽግግር ፍትሕ ሒደትን ለመፍጠር እየተከናወነ ያለውን ሥራ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመልካም እንደተቀበሉት ተጠቁሟል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከንና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፣ በአፍሪካ ቀንድ ስለሚታየው የጸጥታ ተግዳሮት፣ እንዲሁም አንዲት፣ ሰላማዊት እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት ያላቸውን የጋራ ግብ አስመልክቶም እንደተወያዩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤትን ዋቢ በማድረግ ቪኦኤ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ሺርካ

✦ " 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት (አያት ፣ ልጅ፣ የልጅ ልጅ ፣ የ39 ቀን ጨቅላ) ጨምሮ 17 ስዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል " - የቲክቫህ ቤተሰብ አባል

✦ " ከሟቾቹ ውስጥ ከ70 ዓመት አዛውንት እስከ 26 ቀን ህጻን ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል " - ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ (ለቪኦኤ)

✦ " ጥቃቱን ያደረሰው አሸባሪው ሸኔ ነው " - የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን (ለቪኦኤ)

✦ " እኛ ንፁሃን ላይ ጥቃት አላደረስንም " - የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ለቪኦኤ)

✦ " ባለሞያ መድበን ምርመራ ጀምረናል " - ኢሰመኮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ


በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ፤ ሺርካ ወረዳ ፤ በተፈጸመ ጥቃት ንጹሐን ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መሞታቸውን እና የዐይን እማኞችና መልክታቸውን ያደረሱ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

አንድ #የአካባቢው ነዋሪ የቤተሰባችን አባል በላኩልን መልዕክት ፤ " ህዳር 13 /2016 በግምት ከምሽቱ 2:30 አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ እና በታጠቁ ኢ - መደበኛ ሀይሎች በሽርካ ወረዳ ሶሌ ዲገሉ ጉና እና ጢጆ ለቡ በተባሉ የገጠር ቀበሌዎች በተፈፀመ ጥቃት 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት (አያት ፣ ልጅ፣ የልጅ ልጅ ፣ የ 39 ቀን ጨቅላ) ጨምሮ 17 ስዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ በተመሳሳይ ሰዓት በተፈፀመ በሌላኛው ጥቃት ደግሞ 11 በድምሩ 28 ሰው ሲልፍ ሁለት ህፃናት ደግሞ ቆስለው ህክምና ላይ ይገኛሉ " ሲሉ ገልጸዋል።

ቪኦኤ አማርኛ አገልግሎት ክፍል በጉዳዩ ላይ በሰራው ዘገባ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ሦስት ቀበሌዎች ሐሙስ ህዳር 13 እና ሰኞ ህዳር 17 ቀን በተፈጸመ ጥቃት #36_ሰዎች መሞታቸውን ገልጿል።

ከሟቾቹ ገሚሶቹ የሁለት ቤተሰብ አባላት መሆናቸውን በዘገባው ጠቅሷል።

ቃላቸውን የሰጡ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ ነዋሪ ፤ " ህዳር 13 ለ 14 አጥቢያ ለቡ በተባለው ቀበሌ ላይ 11 ሰው አንድ ላይ ሰብስበው እነዚህ ታጣቂዎች አንድ ላይ ረሽነዋል። ሶሌ ዲገሉ በተባለው ቀበሌ ደሞ 17 ሰው አስሩ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው ሰብስበው ረሽነዋል። እነዚህ 17ዱ በአንድ ጉድጓድ 11ቱ በአንድ ጉድጓድ ተቀብረዋል። የዚህን ሀዘን ሳንጨርስ እንደገና በሦስተኛው ቀን ለቡ በተባለው ቀበሌ የአንድ ቤተሰብ አባላት 8 ሰዎች ረሽነዋል። እነዚህም በአንድ ጉድጓድ ተቀብረዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ነዋሪው አክለው፤ " ከእነዚህ ከሟቾቹ ውስጥ ከ70 ዓመት አዛውንት እስከ 26 ቀን ህጻን ነፍሰጡር  እናቶች ይገኙበታል" ያሉ ሲሆን " የሦስቱ ቦታ ጥቃቶች በተመሳይ መልኩ ቤት እየገቡ አንድ ቦታ ያሉ ሰዎችን መረሸን ነው። ህጻን የለም አዋቂ የለም ገብተው መረሸን ነው። የአማርኛ ስም ያላቸው፣ የአማራ ስም ያላቸውና የኦርቶዶክስ እምነት አማኝ ላይ ያተኮረ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ጥቃቱን ማን እንደፈጸመ የተጠየቁት ነዋሪው " ምንም የሚታወቅ ነገር የለም የታጠቁ ኃይሎች ናቸው እከሌ ልንላቸው አንችልም። " ሲሉ ምላሻቸውን ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሓላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ፣ ለጥቃቱ መንግሥት ' ሸኔ ' እያለ ከሚጠራው (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሚለው ታጣቂ ቡድን) ተጠያቂ አድርገዋል።

ኃላፊው ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ " በሽርካ ወረዳ ሶሌ ዲገሉ፤ ጢጆ ለቡ፤ ሲላ ዋጂ አሸባሪው ሸኔ ንጹሐን ላይ ጥቃት ፈጽሟል። ከ2 ዓመት ህጻንን እስከ አቅመ ደካማ ሴቶችን ላይ አነጣጥሮ እኔ ባለኝ መረጃ የ27 ሰዎች ህይወት አልፏል " ብለዋል።

አክለውም " ይኼ አሸባሪ ቡድን ባሳለፍነው ሳምንት ቡኖ በደሌ ጨዋቃ ወረዳ ላይ በኢትዮጵያ የጸጥታ አካል በተወሰደበት እርምጃ ብዙ ኃይሉ ሙትና ቁስለጫ በመሆኑ ይሄንን ለመበቀል ብሎ በአርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ይሄንን ጥቃት ፈጽሟል።" ሲሉ ከሰዋል።

በመንግሥት " ኦነግ ሸኔ " የተባለውና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው የታጠቀ ኃይል ቃል አቀባይ የሆኑት ኦዳ ታርቢ ለቪኦኤ ኦሮምኛ ክፍል በሰጡት ምላሽ ውንጀላውን #አስተባብለዋል፡፡

" እኛ ኃይላችን በተባለው አከባቢ #በሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው እርምጃ፤ ያጠፋው የሰላማዊ ሰዎች ህይወትም የለም። ከህዳር 14 - 17 ድረስ በሥርዓቱ ኃይል ብዙ ሰው ተገሏል፤ ብዙ ቤትም ተቃጥሏል። ይህም በምስራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ነው የተፈጸመው አዛውንቶችም ተገለዋል። ይህንን ለማድበስበስ ነው ጣታቸውን በእኛ ላይ የሚጠቁሙት " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሓላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ግን ይህ ኃይል የሚፈጸጸምማቸውን ጥቃት መካድ ባህሪው ነው ሲሉ ገልጸውታል።

አስተያየታቸውን የሰጡን የቲክቫህ ቤተሰቦች ፤ " እዚሁ ወረዳ ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ ግድያ እንደነበረ ቢታወቅም በአካባቢው ያሉ የመንግስት ታጣቂዎች ለጉዳዩ የሰጡት ትኩረት አነስተኛ ስለነበር ይህ ሁሉ ሰው ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተጨፍጭፈዋል። የአካባቢው ህዝብም በአካባቢው ለመኖር ዋስትና ስለሌለው አካባቢውን ለቆ ለስደት እየተዳረገ ነው፡፡" ሲሉ ተናግረዋል።

በኦሮሚያ ክልል ፤ ምሥራቅ አርሲ ዞን ፤ ሽርካ ደረሰ ስለተባለው ጥቃት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን የኮሚሽኑ የክትትልና ምርመራ ስራ ክፍል ሲኒየር ዳይሬክተር ሚዛኔ አባተ (ዶ/ር)፣ " መረጃ ደርሶናል እያየነው ነው " የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

" አሁን ላይ በዝርዝር የምናገረው ነገር የለም። ነገር ግን እኛ ጉዳዮች እንደዚህ በሚደርሱን ሰዓት ጉዳዩን የሚከታተል ባለሙያ እንመድባለን፣ በዚህም ምርመራ እናደርጋለን። ያ ነገር የተጀመረ መሆኑን ነው መናገር የምችለው " ሲሉ ገልጸውልናል።

@tikvahethiopia