TIKVAH-ETHIOPIA
#ENDF የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ ለህ/ተ/ም/ቤት እንዲላክ ተወሰነ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት አሁን በሥራ ላይ ያለውን የመከላከያ ሰራዊት አዋጅ የሚተካ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ይፀድቅ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል። የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን ውሳኔ ካሰለፈባቸው ጉዳዮች አንዱ የመከላከያ…
" ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን "

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፦

" በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሲካሄዱ የቆዩት ግጭቶች #በሰላማዊ_መንገድ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ፣ በአገሪቱ የልማት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ለማስቻል ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለም/ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡ "

@tikvahethiopia