TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድ ለከተሞች ቀን ክብረ በዓል ያስተላለፉት መልዕክት።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምዕራብ ወለጋ🔝

ጠ/ሚር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ከኦሮምያ ርዕሰ መስተዳድር #ለማ_መገርሳ ጋር በመሆን በምዕራብ ወለጋ የቄለም ወለጋ ዞን ካሉ ወረዳዎች አንዷ የሆነችው ቤጊ ወረዳ የማኅበረሰብ አባላት ጋር ውይይት እያደረጉ ነው።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ🔝

ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ የሶማሊላንድ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲንና ልዑካቸውን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

ሁለቱ ወገኖች በሀገራቱ መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ይበልጥ ስለማጠናከር፣ በሶማሊላንድ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ደኅንነት ስለማስጠበቅና በሰላምና ደኅንነት ዙሪያ ተባብሮ ስለመሥራት ተወያይተው ስምምነቶች ላይ ደርሰዋል።

ፕሬዝዳንት ሙሴ በበኩላቸው ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ለቀጣናው ውሕደት የወሰዷቸውን ርምጃዎች በማንሣት አስተዳደራቸው ከሶማሊያ መንግሥት ጋር በይብልጥ ተቀራርቦ አብረው እንዲሠሩ ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ያቀረቡትን ጥሪ እንደሚቀበሉ ገልፀዋል። በተጨማሪም ወደፊት በጋራና በተናጠል ቀጣይ ውይይቶችን ለማካሄድ ተስማምተዋል። ሲያጠቀልሉም ሁለቱ ወገኖች ስለ ወደብ አጠቃቀምና ሌሎችም የኢኮኖሚ ትሥሥር ላይ ተወያይተዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞የካቲት 13/2011 ዓ.ም. #ሼር #Share @tikvahethiopia

የለገጣፎ -ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር አረንጓዴ ቦታዎችን፥ የወንዝ ዳርቻዎችን፥ ከፈቃድ ውጭ የተያዙ እና ካሳ ተከፍሎባቸው ግንባታ የተካሄደባቸው ናቸው ያላቸውን ቤቶች እያፈረሰ ውሏል።
.
.
በሃዋሳ ከተማ ነገ ለሚካሄደው የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ #ይፋጠንልን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን የሃዋሳ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባደረገው ክትትል በተሽከርካሪ አካል ውስጥ በረቀቀ መንገድ #ተደብቆ ወደ አዲስ አበባ የገባ 4 መትረዬስ ጠብመንጃ እና ከ46 ሺ በላይ ጥይት መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን አስታውቋል፡፡
.
.
ዛሬ ጠዋት ጠቅላ ፍርድ ቤት የፌደራል ፖሊስ አቤቱታን ውድቅ በማድረግ ከእስር እንዲፈቱ ትእዛዝ የተሰጠላቸው አቶ #ኢሳያስ_ዳኘው ሌላ ክስ ተመስርቶባቸው ማረሚያቤት ወርደዋል።
.
.
በምዕራብ ጎንደር ዞን #መቃ በተባለች አነስተኛ ከተማ በትንሹ 17 ሰዎች በትናንትናው ዕለት በአካባቢው ነዋሪዎች #መታገታቸውን የዐይን እማኝ ተናግረዋል።
.
.
ነገ ለሚደረገው #ሰላማዊ_ሰልፍ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ከዞን ፖሊስ፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና #ከፌደራል_ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ሰልፉ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች በቂ ጥበቃ ያደርጋል።
.
.
ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ የሶማሊላንድ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲንና ልዑካቸውን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
.
.
የደኢህዴን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ከየካቲት 12/06/2011 ዓ.ም ጀምሮ #በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
.
.
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) ለተፈናቀሉ ወገኖች 5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
.
.
የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን እና ሬድዮ /ኢሳት/ ጋዜጠኞች ዛሬ ኢቢሲን ጎብኝተዋል።
.
.
የሀረሪ ብሄራዊ ሊግ ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡ ማዕከላዊ ኮሚቴው ለሁለት ቀናት  በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባም በአራት አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
.
.
አክሱም ሽረ እንደስላሴ መስመር ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡ የትራፊክ አደጋው ከሽረ እንደስላሴ ወደ አክሱምና ከአክሱም ወደ ሽረ እንደስላሴ  ሲጓዙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች #በመጋጨታቸው ያጋጠመ ነው ተብሏል፡፡
.
.
በህገ ወጥ ግንባታዎች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ህግን መሰረት ያደረገ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ሃላፊ ዶክተር #ሚልኬሳ_ሚደግሳ ተናግረዋል።
.
.
በለገጣፎ_ለገዳዲ ከተማ ቤታቸው #የፈረሰባቸው ዜጎች ችግር ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ fbc፣ etv፣ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት፣ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ፣ wazemaradio፣ የጀርመን ራድዮ፣ OBN፣ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ በአሁኑ ሰዓት ከአፋር፣ ከሶማሌ፣ ከሐረሪ፣ ከቤንሻንጉል ጉምዝና ከጋምቤላ ክልል አጋር ፓርቲዎች የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ጋር #ውይይት እያካሄዱ ነው።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከአጋር ፓርቲዎች የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ጋር በነበራቸው ውይይት ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ በመደመር እሳቤ የመለወጥና አብሮ የማደግን አስፈላጊነት አሥምረውበታል። ተሳታፊዎቹም ለግል ዕድገት፣ እምነት፣ ርኅራሄ እና በተለይም ማኅበረሰባቸውን ለመምራት ገንቢ ዕሴቶችን እንዲያበለጽጉ አበረታተዋቸዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ገበታ_ለሸገር

እራቱን ለመታደም የምትፈልጉ...

ለቢዝነስ ባለቤቶች፣ የኩባንያ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅት ኃላፊዎችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት፦

ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት ለመደገፍና ከጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አሕመድ ጋር ገበታ ለመቅረብ sheger@pmo.gov.et ላይ ፍላጎትዎን እንዲገልፁ ጥሪ ቀርቧል።

የእራቱ ዋጋ በሰው -- ብር 5ሚሊዮን!

ሙሉ ስምዎን፣ ድርጅትዎን፣ የተንቀሳቃሽ ስልክ ቁጥርዎን ሲልኩ በሸገር ገበታ ለመታደም የመመዝገቢያ ቅጽ ይላክሎታል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Adwa123 - ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ 123ኛው የዐድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን በተመለከተ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያስተላለፉት መልእክት::

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ ዛሬ ጠዋት ለአንድ ቀን ይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ የገቡትን የሶማሊያውን ፕሬዝዳንት #መሐመድ_አብዱላሂ_መሐመድን በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተቀብለዋቸዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኬንያ(ናይሮቢ)🛫

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድና የሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ ከኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር #ለመወያየት በአሁኑ ወቅት ወደ #ናይሮቢ ኬንያ አቅንተዋል።

ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድ በሶማሊያና ኬንያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት እንደ ምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ሊቀ መንበርነታቸው በቅርበት በመከታተል ወደ #ዕርቅ የሚመጡበትን መላ እያፈላለጉ ነው።

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ የኬንያው ፕሬዚዳንት ኬንያታና የሶማሊያው አብዱላሂ መሐመድ ወደ ኢትዮጵያ ለይፋዊ ጉብኝት በዘለቁ ወቅት ከሁለቱም ጋር ባደረጉት ምክክር፤ ይህንን የኬንያና የሶማሊያ መሪዎች የፊት ለፊት ውይይት ለማመቻቸት ወስነው ነበር። ይህ የውይይት መድረክም በሁለቱ መካከል ያለውን የተካረረ ውጥረት ያረግባል ተብሎ ይታመናል።

ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ አለም አቀፍ #የሴቶችን_ቀን በተመለከተ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተዘጋጀ ዝግጅት ተካፍለዋል።

#PMOEthiopia
#InternationalWomensDay
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ📞ዶናል ትራምፕ

ጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አሕመድ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በስልክ ተወያዩ። ሁለቱ መሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 302 ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች ቤተሰቦች የኀዘን መግለጫ ተለዋውጠዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጠንካራ ተቋም መሆኑን አድንቀው በተፈለገበት ቦታ ሁሉ የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኝነታቸውን አስታውቀዋል። ፕሬዝዳንቱ በማስከተልም በኢትዮጵያ ባለፉት ወራት ለተካሄዱ ሁሉን አቀፍ ለውጦች ያላቸውን ድጋፍ ገልፀዋል። ሁለቱ መሪዎች ውይይታቸውን በሀገራቱ መካከል ያለውን ረጅም ጊዜ የዘለቀ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተው አጠናቅቀዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሚመለከተው ሁሉ🔝

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ስለማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ያስተላለፉት መልዕክት::

Via PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኦዴፓ ለ29ኛ ዐመት ምስረታ በዓሉ ባወጣው መግለጫ ሁሉም ዜጎች በእኩልነት የሚኖሩባት ሀገር ለመመስረት እታገላለሁ ብሏል፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር #ዐቢይ_አሕመድ ዜጎች የእኔ ማለት ትተው የእኛ ማለት እንዲጀምሩ የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አሕመድ መጋቢት 19 ቀን 2011 ከአገር ውስጥና ከውጭ #ጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ምላሾች👆

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድ ከጋዜጠኞች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ከሰጡት ምላሽ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

• አዲስ አበባ የሁሉምናት እንጂ የአንዱ ብቻናት የሚለው ትክክል አይደለም።

• በህገመንግስቱ የተቀመጠው የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ያለው የልዩ ጥቅም መብት ግን ሊረጋገጥ ይገባል፤ የሚለውን ሀሳብ ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ሰው ሊደግፈው የሚገባ ነው።

• ኢህአዲግ የቀድሞ ጥምረቱ አለ፤ ብዙዎች የተለያየን የሚመስላቸው የልዩነት ሀሳቦች ሲኖሩ አራቱ ፓርቲዎች በውስጣዊ ውይይት ብቻ ይገድቡት የነበረው ሂደት ቀርቶ ፓርቲዎቹ የልዩነት አቋማቸውን በአደባባይ መግለፃቸው ነው ጥምረቱ የሌለ የሚያስመስለው።

• ይህ አካሄድ ወደፊትም ይቀጥላል ሆኖም ተግባራዊ የሚሆነው በጋራ የወሰነው ሀሳብ ነው

• ይበልጥ ወደ አንድ ለመወሃድ የጀመርነው ሂደትም ይቀጥላል።

• የፌደራል መንግስት ተዳክሟል ለማለት መለኪያው መሆን ያለበት ሀገር ስትወረር መመከት ሲያቅተው ዲፕሎማሲያዊ ስራዎችን በብቃት መመከት አልችል ሲል ነው።

አሁን ግን በዚህ መልኩ የሚገለፅ አንዳችም ተግዳሮት አልገጠመንም በክልሎች የሚፈጠሩ ችግሮች ላይ ጣልቃ የማንገባው ክልሎች በራሳቸው መፍታት አለባቸው ብለን ስለምናምን ነው፤ ይህ ደግሞ ተገቢ ነው።

• ከኤርትራ ጋር ያደረግነው ስምምነት መሰረት ያደረገው ሰላምን ነው፤ በቀጣይ ኢኮኖሚ: ንግድ እና መሰል በሆኑ ጉዳዮች ላይ ለመስማማት በሂደት ላይ ነን፤ ስለዚህ ከህዝብ የተደበቀ ሌላ ስምምነት የለንም፡፡

• ዲያስፖራው አሁንም ሀገሩን ለመደገፍ የጀመረውን መንገድ ሊገፋበት ይገባል፤ ይሁን እንጂ በማህበራዊ ሚዲያ በሚወጡ መረጃዎች ተስፋ የመቁረጥ ነገር ይታያል ይህ ተገቢ አይደለም ሁሉም ነገር ቀድሞ በተግባባንበት መልኩ እየተተገበረ ነው፤ ስለሆን ወደ ኋላ ማለት አይገባም

• በኮዬ ፌጬ የኮንደሚኒዮም ግንባታ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ወሰን ያለው ውዝግብ ተፈቶ ለኮንዶሚኒዮም ባለእድለኞች ቤቶቹ እንዲተላለፉ እየተሰራ ነው

• በኦዲፒና በአዴፓ እንዲሁም በኦዲፒ በራሱ ውስጥ አንድነት እንጂ ምንም አይነት የተለየ ልዮነቶች የለም ነግር ግን በመካከላቸው የልዮነት ሀሳብ ይኖራሉ እነሱንም በመነጋገር እየፈታን ነው

• ከለውጡ በሃላ ኢኮኖሚው በሚፈለገው ደረጃ ውጤቶች ያልታየው ኢኮኖሚው ችግር ውስጥ ሆኖ ስለተቀበልነው እሱን የማስተካከል ስራ እየተሰራ ቆይተናል፡፡ በዚህም በርካታ ሀገራት ድጋፍ ስላደረጉ ውጤት ማግኘት ተችሏል፡፡

• አሁን ላይ ኢኮኖሚው ከታመመበት ሁኔታ ላይ ወጥቶ ጤናማ ሆኗል፡፡

• የአማራና የትግራይ ክልል ውጥረት በቀጣይ በእርግጠኝነት የሚረግብና ወደ ሰላም የሚመለስ ነው፡፡ ሁሉቱም ወገን በኦሮሚያና በሶማሊያ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ያመጣውን ኪሳራ ስለሚያውቁ መካከላቸው ያለው ልዮነት በሰላም ይፈታሉ፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንዳትታለሉ...

(የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት)

በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አሕመድ የተፃፉ በሚል በየቦታው #እየተሰራጩ ያሉ መፅሃፍትን በተመለከተ በርካቶች እየጠየቁን ይገኛሉ። በመሆኑም አሁን ገበያ ላይ የወጣ አንድም መፅሀፍ አለመኖሩን እንገልፃለን። ወደፊት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚወጡ የህትመት ውጤቶችን ጽ/ቤቱ በይፋ የሚያሳውቅ ሲሆን ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ በሀሰተኛ ህትመቶች እንዳይታለል እናስገነዝባለን።

#PMOEthiopia
@tsegabwolse @tikvahethiopia
#update በጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ የሚመራውና ለ"ሸገርን ማስዋብ" ፕሮጀክት ገንዘብ የሚያሰባስበው የ"ገበታ ለሸገር" አስተባባሪ ኮሚቴ ዛሬ ከቀትር በኋላ ተገናኝቶ የደረሰበትን ደረጃ ተወያይቷል። ኮሚቴው እጁ ላይ ያለውን ሥራ አጠናቅቆ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውጤቱን ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፕሬዝዳንት ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ እና ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ በ43ኛው የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሠልጣኞችና የቡድን መሪዎችን ዛሬ ማምሻውን በተደገ የእራት ግብዣ ላይ አመሰገኑ። አትሌቶቹ ለሀገራቸው 5 ወርቅ፣ 3 ብርና 3 የመዳብ ሜዳልያዎችን በማስገኘት ከ63 ተሳታፊ ሀገራት በሜዳሊያ ሰንጠረዥ 1ኛ ደረጃ ላይ እንድትሆን አስችለዋል። ጠ/ሚሩ ለኮሚቴው አመራርና አብላጫ ውጤት ላስመሰገቡ አትሌቶች የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት አበርክተዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድ ከጤና ባለሙያዎች ጋር ባደረጉት ዉይይት ለተቀሩት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የጠሚ/ር ጽ/ቤትና የጤና ሚኒስትር ባለሙያዎችን ያካተተ #ታስክፎርስ ተቋቁሞ በመስራት ላይ ይገኛል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia