TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Adwa123 #አድዋ123-አዲስ አበባ🔝

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ123ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓድዋ ድል በዓል ለየት ባለ መልኩ እንደሚያከብር ቀደም ብሎ መግለፁ ይታወሳል፡፡

በዚህም የአድዋ ተጓዦችን በክብር ከመሸት የጀመረው የከተማ አስተዳደሩ ተግባር በዓሉን ለማድመቅ የተዘጋጁ ፕሮግራሞችን እና በዕለቱ የተዘጋጁ ስነ-ስርዓቶች ላይ የፕረስ ሴክረታሪዋ ወ/ሪት #ፌቨን_ተሾመ እና የከተማ አስተዳደሩ የባህል የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ረ/ፕሮፌሰር #ነብዩ_ባዬ ለጋዜጠኞች ማብራርያ ሰጥቷል፡፡

በዚህም ሐሙስ(በ21-06-2011ዓ.ም) በብሄራዊ ቤተ-መዛግብት የፊልም ፌስቲቫል ይደረጋል፡፡

ዓርብ (በ22-06-2011ዓ.ም) በዓሉን በተመለከተ የስነ-ጥበብ ድግስ በጣይቱ ሆቴል ተዘጋጅቷል፡፡

በበዓሉ ዕለት ማለትም (በ23-06-2011ዓ.ም) ጠዋት ላይ በጊዮርጊስ አደባባይ የተለመደው የዓድዋ ሰመዓታትን የማስታወስ እና የማወደስ ስነ-ስርዓት ይደረጋል፡፡

በመቀጠልም በዓሉ ከሚደረግበት የጊዮርጊስ አደባባይ እስከ ዓድዋ ድልድይ የሚደረገው የእግር ጉዞ እና ዓርበኞችን እና የበዓሉ ታዳሚዎችን ግብር የማብላት ስነ-ስርዓትም በቅደም ተከተል ከዚህ ቀድሞ በነበረው መልኩ የሚከናወን ይሆናል፡፡

በመጨረሻም የበዓሉ ቀን ከሰዓት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ አዘጋጅነት የ"አድዋ ፌስቲቫል!" የሙዚቃ ድግስ ተዘጋጅቷል፡፡

የሙዚቃ ድግሱ መግቢያ በነፃ ሲሆን በፌስቲቫሉ ላይ በርካታ የሃገራችን የኪነ-ጥበብ ፈርጦች የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ስለዚህ የከተማችን ነዋሪዎች በዚህ የሃገራችን ህዝቦች የድል በዓል የሆነውን የዓድዋ ድል በዓል ፌስቲቫል ላይ እንዲታደሙ እና በዓሉን በደማቅ ሁኔታ በጋራ እንድናከብር ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጥሪውን ያቀርባል፡፡

Via @mayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Adwa123 - ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ 123ኛው የዐድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን በተመለከተ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያስተላለፉት መልእክት::

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስጦታ!

@medachat ነገ በድጋሚ የሚካሄደውን የሮፍናንን "የኔ ትውልድ" የሙዚቃ ኮንሰርት እንድታደሙ ለ10 የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ነፃ ትኬት አዘጋጅቶልናል!

በሜዳ ቻት እስከ ምሽቱ 5 ሰዐት ድረስ #Adwa123 ብላችሁ ለላካችሁ 10 ሰዎች ትኬቶቹን እናስረክባለን!

MedaChat App ስልኮት ላይ ተጭኗል?? ካልተጫነ በዚህ ያገኛሉ www.bit.ly/medachatapp

በመቀጠል በሜዳ ቻት APP በኩል በ @tsegab_wolde የMedaChat UserName #Adwa123 ብላችሁ ላኩልኝ!

ማሳሰቢያ፦ መልዕክቱን አንዴ ብቻ ላኩ! ተደጋግሞ ቢላክ ተቀባይነት የለውም! አንዴ ብቻ!! -- #Adwa123
የትኬት አሸናፊዎች...

1.Sofonias
2.Eyasu
3.Nuh
4.Yonas
5.አቤል
6.ayalew
7.yonatan
8.Filagot
9.Daniel
10.Anwar

ነገ ቃና ስቱዲዮ - የሮፍናንን "የኔ ትውልድ" ኮንሰርት በክብር እንድትታደሙ ሜዳ ቻት ትኬታችሁን ያስረክባችኃል!

ሁላችሁንም ለተሳትፏቹ እናመሰግናለን!
መልካም በዓል ይሁንልን!! #Adwa123

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እኛስ

የጥንት አባቶቻችን ያለብሄር፣ ያለዘር፣ ያለቋንቋ፣ ያለሀይማኖት ልዩነት ወራሪውን የጣልያን ጦር አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው፤ በደም በአጥንታቸው ይህቺን ሀገር #አስከብረው ለኛ #አስረክበውናል

የዛሬዎቹ ትውልዶች እኛስለቀጣዩ ትውልድ ምን ይሆን የምናወርሰው? የትኛዋን ሀገር ነው የምናወርሰው?

ወገኖቼ ለመጪው ትውልድ ክፍፍል እናውርስ? አንድ የሚያደርገንን ሰውነትን ረስተን በብሄር መቧደንን ለልጆቻችን እናውርስ? ንገሩኝ...በዘር መከፋፈልን እናውርስ? አለመከባበርን እናውርስ?? መሰዳደብን እናውርስ? ቁጭ ብሎ ማውራትን እናውርስ? አለመደማመጥን እናውርስ?

ቆይ ምን ሰርተን አለፍን እንበል

አድዋ የነፃነት ምልክት ብቻ አይደልም፤ አድዋ የኢትዮጵያዊያን #አንድነት እና ጠንካራ #ትስስር መገለጫም ጭምር ነው።

አድዋን ስናከብር...እኛስ ለቀጣዩ ትውልድ ምን እናውርስ? እኛስ ለኢትዮጵያ ምን ሰርተን እንለፍ? የሚሉትን ጥያቄዎች እራሳችንን #እየጠየቅን መሆን አለበት።

በTIKVAH-ETH ስም ሁላችሁንም እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ!

ሰላም፤ ፍቅር፤ አንድነት!
#Adwa123 #አድዋ123
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Adwa123 #አድዋ123

"አድዋ የሙዚቃ ፌስቲቫል"-በመስቀል አደባባይ የተዘጋጀውን ይህን #የሙዚቃ_ፌስቲቫል በOBN ቴሌቪዥን #በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅማ #Adwa123🔝

ጅማ ላይ አባት እና እናት አርበኞች እንዲሁም #የጅማ_ዩኒቨርሲቲ የትያትር ጥበባት መምህራን እና ተማሪዎች በዓሉን አንድላይ #በደመቀ ሁኔታ አብረውታል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"አድዋ የሙዚቃ ፌስቲቫል"- በፋና ቴሌቪዥን መከታተል ትችላላችሁ! #Adwa123 #አድዋ123

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ🔝

"#ኤርሚ የጉዞ አድዋ ተጓዥ #በሰላም አዲስ አበባ ገብቷል። #Adwa123 #አድዋ123"

"ኤርሚ ካስተላለፈው መልክት ኢትዮጵያን አናውቃትም በFB እንደምናየው አይደለም እኔ ያየዋት ኢትዮጵያ ፍፁም ፍቅር የሆኑ ህዝቦች ያሉበት ሀገር ናት።"

Via Shinshaw(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia