TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Adwa123 #አድዋ123-አዲስ አበባ🔝

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ123ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓድዋ ድል በዓል ለየት ባለ መልኩ እንደሚያከብር ቀደም ብሎ መግለፁ ይታወሳል፡፡

በዚህም የአድዋ ተጓዦችን በክብር ከመሸት የጀመረው የከተማ አስተዳደሩ ተግባር በዓሉን ለማድመቅ የተዘጋጁ ፕሮግራሞችን እና በዕለቱ የተዘጋጁ ስነ-ስርዓቶች ላይ የፕረስ ሴክረታሪዋ ወ/ሪት #ፌቨን_ተሾመ እና የከተማ አስተዳደሩ የባህል የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ረ/ፕሮፌሰር #ነብዩ_ባዬ ለጋዜጠኞች ማብራርያ ሰጥቷል፡፡

በዚህም ሐሙስ(በ21-06-2011ዓ.ም) በብሄራዊ ቤተ-መዛግብት የፊልም ፌስቲቫል ይደረጋል፡፡

ዓርብ (በ22-06-2011ዓ.ም) በዓሉን በተመለከተ የስነ-ጥበብ ድግስ በጣይቱ ሆቴል ተዘጋጅቷል፡፡

በበዓሉ ዕለት ማለትም (በ23-06-2011ዓ.ም) ጠዋት ላይ በጊዮርጊስ አደባባይ የተለመደው የዓድዋ ሰመዓታትን የማስታወስ እና የማወደስ ስነ-ስርዓት ይደረጋል፡፡

በመቀጠልም በዓሉ ከሚደረግበት የጊዮርጊስ አደባባይ እስከ ዓድዋ ድልድይ የሚደረገው የእግር ጉዞ እና ዓርበኞችን እና የበዓሉ ታዳሚዎችን ግብር የማብላት ስነ-ስርዓትም በቅደም ተከተል ከዚህ ቀድሞ በነበረው መልኩ የሚከናወን ይሆናል፡፡

በመጨረሻም የበዓሉ ቀን ከሰዓት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ አዘጋጅነት የ"አድዋ ፌስቲቫል!" የሙዚቃ ድግስ ተዘጋጅቷል፡፡

የሙዚቃ ድግሱ መግቢያ በነፃ ሲሆን በፌስቲቫሉ ላይ በርካታ የሃገራችን የኪነ-ጥበብ ፈርጦች የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ስለዚህ የከተማችን ነዋሪዎች በዚህ የሃገራችን ህዝቦች የድል በዓል የሆነውን የዓድዋ ድል በዓል ፌስቲቫል ላይ እንዲታደሙ እና በዓሉን በደማቅ ሁኔታ በጋራ እንድናከብር ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጥሪውን ያቀርባል፡፡

Via @mayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia