TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ⬆️

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የቬትናም ፕሬዝዳንት የሆኑትን ትራን ዳይ ኩዋንግን አመሻሽ ላይ በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ሁለቱ አገራት በባህል፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ አጀንዳዎች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የሁለቱን አገራት ትብብር የበለጠ ለማጠናከር #ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡

ፈጣን እድገትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት ከቻሉት የምስራቅ እስያ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ቬትናም ከኢትዮጵያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1976 መሆኑ ይታወሳል፡፡

©የጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኦነግ እና ኦፌኮ ተስማሙ⬆️

ኦፌኮ እና ኦነግ በዛሬው እለት በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸው #ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ያስታወቁት። በዚህም መሰረት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በኦሮሞ እና ኦሮሚያ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደሚሰሩ ነው በመግለጫው ያስታወቁት።

©OMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ፕሬዚዳንት #ሳህለወርቅ ወደ ደቡብ ሱዳን አቀኑ። ፕሬዘደንቷ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑት ባለፈው መስከረም በአዲስ አበባ የተፈረመውን የደቡብ ሱዳን የሰላም #ስምምነት ለማብሰር በተዘጋጀው ስነስርዓት ላይ ለመሳተፍ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኤርትራው ፕሬዝዳንት #ኢሳያስ_አፈወርቂ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የደረሱበትን የሰላም #ስምምነት አስመልክተው ነገ ከድምጺ ሃፋሽ ኤርትራ ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ጋር ቃለ ምልልስ እንደሚያደርጉ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል ዛሬ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ሰላም ስምምነቱን ከፈረሙ ወዲህ ስለ ዝርዝር ይዘቱ ይፋዊ መግለጫ ሲሰጡ የነገው የመጀመሪያቸው ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ WazemaRadio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦነግ‼️

የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦነግ አመራሮች ያደረጉትን #ስምምነት መሰረት በማድረግ ወደ ሃገር ገብተው ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ 1 ሺ154
የኦነግ ጦር አባላት እንደ #የፍላጎታቸው ወደ ስራ ሊሰማሩ ነው።

የኦሮሚያ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ እንዳሳወቀው፤ ስልጠና ሲወስዱ ከነበሩት የኦነግ ጦር አባላት ውስጥ 700ዎቹ በራሳቸው ፍላጎት የኦሮሚያን ፖሊስ እንቀላቀላለን በማለታቸው ግንዛቤ እንዲያገኙ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ እንዲገቡ ተድርገዋል።

የአጭር ጊዜ ስልጠና በመውሰድም የኦሮሚያን ፖሊስ የሚቀላቀሉ ይሆናል። የቀሩትም እንደየፍላጎታቸው በግል ስራ፣ በመንግስት ስራ እና የኦነግ ፖለቲካ አባል በመሆን ወደ ስራ ይገባሉ ተብሏል።

ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሶሳ🔝

የአማራ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ #ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ በአጎራባች ወረዳዎች ዘላቂ ሰላም ለመፈጠር፣ ችግሮች ሲያጋጥሙ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት እና በፖለቲካዊ ዘርፎችም በጋራ ለመሥራት ስምምነቱ ተፈርሟል ነው የተባለው።

ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ፣ አሠራሮችን በማሻሻል ለወከሉት ሕዝብ በግልጽነትና በተጠያቂነት ለማገልገል፣ የተጀመረውን ለውጥም አጠናክሮ ለማስቀጠል ነው ስምምነቱን የአማራና ቤኒሻንጉል ክልል ምክር ቤቶች ትላንት የተፈራረሙት፡፡

የጋራ መድረክ በመመሥረትም በዓመት ሁለት ጊዜ እየተገናኙ ለመምከር ምክር ቤቶቹ ስምምነት አድርገዋል፡፡ ስምምነቱ አንድ የጋራ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመገንባት የሚደረገውን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት መሆኑም ተነግሯል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የአማራና የትግራይ ክልል ክለቦች በሜዳቸው የሚጫወቱበትን አግባብ በተመለከተ ዛሬ ከክለቦቹ ጋር በአዲስ አበባ ተወያየ። በውይይቱ የሁለቱ ክልሎች የጸጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን ክለቦቹ #ስምምነት ላይ ደርሰዋል። በስምምነቱ በመሰረት ከሁለት አመት በኅላ ስሁል ሽሬ ወደ ባህርዳር በማቅና ከባህርዳር ከነማ ጋር ይጫወታል።

ምንጭ ኢትዮጵያ ላይቭ ሀፕዴት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በሰሜንና በምዕራብ ጎንደር ዞን ይንቀሳቀሱ የነበሩ ከ500 በላይ ታጣቂዎች ከመንግስት ጋር #ስምምነት ላይ በመድረሳቸው ዛሬ ወደ ቀያቸው መመለስ ጀምረዋል።

Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስምምነት ሊፈራረሙ ነው!

የአማራና ትግራይ ክልሎች ርዕሳ መስተዳድሮች ስምምነት ሊፈራረሙ ነው፡፡ የአማራና ትግራይ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች በሁለቱ ክልሎች መካከል እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት #ስምምነት ዛሬ በሂልተን ሆቴል ከደቂቃዎች በኋላ #ይፈራማሉ፡፡

‹‹ሕዝቡ ችግሩ የአማራና ትግራይ ክልሎች መንግሥታት ነው›› ማለቱንና በሁለቱ ክልል ሕዝቦች መካከል ችግሮች አለመኖራቸውን የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል፡፡

የሁለቱን ክልል መንግሥታት መሪዎች ችግሮች መፍትሔ ለመፈለግ ለስድስት ወራት ሕዝቡንና በየደረጃው ያሉ አመራሮችን ያወያዩት የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች አሁን ሁለቱም ርዕሰ መስተዳድሮች ችግሩን ለመፍታት ጫፍ መድረሳቸውን አስታውቀዋል፡፡

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶ.ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ናቸው ስምምነቱን ይፈራረማሉ፡፡

የማስማማት ሂደቱን የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በራሳቸው ተነሳሽነት እንደጀመሩት ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የሀገር ሺማግሌዎች ከስድስት ወራት በፊት በፈቃዳቸው ተገናኝተው ወደ ማሸማገል ሂደት መግባታቸውን ነው ያስረዱት፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህር_ዳር_ከነማ

የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋች እና ምክትል አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ባህር ዳር ከነማን ለማሰልጠን #ስምምነት ላይ ደርሷል፡፡ አሁን በኢትዮጵያ የወንዶች እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ዋሊዎቹ በምክትል አሰልጣኝት እየሰራ የሚገኘው ፋሲል ተካልኝ የጣናው ሞገድን ለማሰልጠን በቃል ደረጃ ተስማምቷል፡፡ ከዋሊያዎቹ ጋር ድሬዳዋ የሚገኘው ፋሲል ተካልኝ የባህርዳር ከነማ አሰልጣኝ ለመሆን እንደተስማማ የባህርዳር ከነማ እግር ኳስ ቡድን የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አማረ ዓለሙ ለአብመድ ገልጸዋል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ዛሬ ጠዋት ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን አሳውቀዋል፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎችን የሚያገናኙ ተመሳሳይ የውይይት መድረኮችን በማስቀጠል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት #ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልፀዋል።

ዶክተር አብይ ቀጣዩ ምክክር በ "ሀገራዊ መግባባት" ላይ የሚያተኩር ይሆናል ያሉ ሲሆን ሀገሪቱ ተረጋግታ በብልጽግና ጎዳና ግስጋሴዋን እንድትቀጥል ሰላማዊ ተሳትፎ ፣ ሀሳቦችን በግልጽ ለውይይት ማቅረብ እና የፖለቲካ አመራሮች መከባበር በእጅጉ አስፈላጊ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የውጭ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሶስትዮሽ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም በቬርቿል ተጀምሯል። የዛሬው ስብሰባ ሊጀመር የቻለው በደ/አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር ጥቅምት 11 ቀን 2013 ለሃገራቱ በጻፉት ደብዳቤ ባስተላለፉት ጥሪ መሰረት ነው። በዚህ መሰረት የኢትዮጵያ፣…
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሶስትዮሽ ስብሰባ !

(የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የውሃ፣ መሰኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የጋራ ፕሬስ መግለጫ)

የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር ቀደም ብሎ በጥቅምት 11 ቀን 2013 ዓ/ም ለሃገራቱ በጻፉት ደብዳቤ እና ባስተላለፉት ጥሪ መሰረት የኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትላንት ጥቅምት 17 በበይነ-መረብ ስብሰባ አካሂዷል፡፡

ስብሰባው አፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ስር እየተካሄደ ያለው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን የተመለከተው የሶስትዮሽ ድርድር በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ መክሯል።

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ክቡር ሲይርል ራማፎዛ ቀደም ብሎ በጥቅምት መጀመሪያ ከኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች ጋር በስልክ ባደረጓቸው ውይይቶች በተደረሰው መግባባት እና ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት ድርድሩን ለመቀጠል #ስምምነት ተደርሷል።

ሀገራቱ በሰባት (7) ቀናት ውስጥ ድርድሩን በማካሄድ በቀጣይ የድርድሩ አካሄዶች እና የጊዜ ሰሌዳ ላይ ስምምነት መድረስ፣ ሀገራቱ ላይ ልዩነት ባሏቸው ጉዳዮች ዙሪያ ልዩነቶችን ለማጥበብ እና ውጤቱንም ለውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ቀጣይ ስብሰባ ለማቅረብ መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡

የመጀመሪያው የቴክኒክ ስብሰባ በሱዳን የውሃ ጉዳይ ሚኒስትር ሰብሳቢነት እደሚከናወን ይጠበቃል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Tigray

የኢትዮጵያ መንግሥት እና የዓለም ምግብ ፕሮግራም በትግራይ ክልል በጋራ ሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ #ስምምነት ላይ ደርሱ።

ስምምነቱ የመጣው የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ከተመድ የዓለም ምግብ ድርጅት ሥራ አስፈጻሚ ዴቪስ ቤስሊ (ዶ/ር) ጋር በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለው የሰብአዊ ድጋፍ ሁኔታ በጋራ የመስክ ጉብኝት ማደረጋቸውን ተከትሎ ነው።

የኢትዮጵያ መንግሥትና የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድግፉ በስፋት እና በተፋጠነ መልኩ እንዲከናወን መስማማታቸው የአለም ምግብ ፕሮግራም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

በተመሳሳይም በመስክ በተካሄደው ምልከታ መቐለ የሚገኘው የእህል ማከማቻ ለቀጣይ 2 ወራት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎችን መመገብ የሚያስችል የምግብ ክምችት መኖሩን ባለሥልጣናቱ ማረጋገጣቸውን የሠላም ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አሳውቋል። (ኢብኮ)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EthioTelecom #SafaricomEthiopia

ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሰረተ ልማት መጋራት እንዲሁም ትስስር ላይ ያደጉት ዘርፈ ብዙ ድርድሮች በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገልጿል።

በቅርቡ በኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም መካከል #ስምምነት_ይፈረማል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በሌላ በኩል ፥ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሚያዚያ 1 /2014 አገልግሎት ለመጀመር እቅድ እንደነበረው ከዚህ በፊት መግለፁ ይታወሳል፤ ነገር ግን በተባለው ቀን አገልግሎት ያልጀመረ ሲሆን በቅርቡ አገልግሎት እንደሚጀምር ይጠበቃል።

ፎቶ ፦ ኢትዮ ቴሌኮም

@tikvahethiopia
" ... ከጌታቸው ጨምሮ ከራሳቸው ከTPLF ሰዎች አጣርቻለሁ ያ የተነገረው የድሮን ጥቃት የሚባለው ውሸት ነው " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ የተፈፀመ " የድሮን ጥቃት " የለም ሲሉ የኢትዮጵያ መንግስት ተደራዳሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ተናግረዋል።

ይህን የተናገሩት " የኢትዮጵያ ሚዲያ ሰርቪስ (ኢ ኤም ኤስ) " ለተባለና በኢንተርኔት ላይ ለሚሰራጭ ሚዲያ ነው።

" በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ አንዳንድ ክስተቶች ተፈጠሩ ሲባል መረጃ እንለዋወጣለን። ስምምነት ተፈራርመናል ስለዚህ የስልክ ችግር የለብንም። " ያሉት አምባሳደር ሬድዋን በኬንያ ናይሮቢ ፤ ከእነ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ከወታደራዊ አዛዦቹም ጋር መነጋገራቸውን እና የድሮን ጥቃት ተፈፀመ የተባለው ውሸት መሆኑን  ገልፀዋል።

" #ስምምነት_ከመፈረሙ_በፊት የነበረ (incident) ክስተትን ከስምምነት በኃላም ለማምጣት የሚሞክሩ አሉ። በዚህ ግጭት ውስጥ ገንዘብ ይከፈላቸው የነበሩ ጥሩ ሃብት ያፈሩበት ሰዎች አሁንም ግጭት እንዲቀጥል የማቀጣጠል ፍላጎት ያላቸው እንዳሉ እናያለን ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ፤ ከውስጥም በተለያየ መንገድ ስሜታዊ የሆነ ሰው ሊያራግበው ይችላል የትግራይ ሚዲያም ፤ የወያኔ ቴሌቪዥንም ሰርተውት ነበር" ብለዋል።

" በእኛ በኩል #ንግግሮችን ለማስተካከል ሞክረናል " ያሉት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን " አሁን ሰው ተስፋ እንዳያድርበት ወደፊትም ይሄን ነገር እንዲያመጣ ነው እንጂ ቁርሾውን በ 'Transitional Justice' በሂደት ይሄዳል ፣ በምህረት የሚታለፈው ይታለፋል መፀፀቱ ከታየ እውነት ከተናገረ ፤ የግድ በፍርድ ቤት ማለቅ ያለበት ከባድ ወንጀል የሆነ ወደ ፍርድ ቤት ይሄዳል፣ ተጠያቂነትንም የማህበራዊ ህክምናንም ትስስርንም እኩል የሚያማክል መንገድ አለን እሱ ይደረሳል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ያልነበረ ነገር እያጋጋሉ የውሸት ሚፅፉ አሉ ከራሳቸው ከTPLF ሰዎች አጣርቻለሁ ጌታቸውን ጨምሮ ያ የወጣው መግለጫ (የGSTS መግለጫ ማለታቸው ነው) የጋራቸው አቋም እንዳልሆነ፣  የተባለው የድሮን ጥቃትም ውሸት እንደሆነ አጣርቻለሁ " ብለዋል።

በስናይፐር ፣ በድሽቃ አልፎ አልፎ የተኩስ ልውውጥ ሊያጋጥም እንደሚችል የጠቆሙት አምባሳደሩ " ይሄ የተለመደ ነው፤ የሰላም ፊርማ ሲፈረም የተወሰኑ ቀናት እየሞተ እስከሚሄድ ድረስ የሰማም በስሜት ተውጦ እምቢ ብሎ ሊያደርገው ይችላል፣ ሳይሰማ የሚቀርም ያደርገዋል፤ ነገር ፈልጎ ነገሩ እንዲበላሽ  የሚፈልግም ሊያደርገው ይችላል በታንክ እና በመድፍ እንድካልሆነ ድረስ በድሽቃ እና በስናይፐሮች የሚደረግ አንዳንድ የተኩስ ምልልሶች እዚህም እዚያም ያጋጥማሉ " ሲሉ አስረድተዋል።

" ሰው ይሄንን (አንዳንድ ቦታዎች ላይ የሚያጋጥሙትን የተኩስ ልውውጦችን ማለታቸው ነው) ለመዘገብ የሚቸኩለውን ያህል ከTPLF ካምፕ ወደኛ ወታደር መጥቶ አብሮ በልቶ ፣ ... ፣ ተጫውቶ ፣ ፎቶ ተነስቶ የሚመለሰውን ለመዘገብ ፍላጎት የላቸውም እኛ ነን መግፋት ያለብን የሚል ነገር በሁለቱም በኩል አለ ካማንደሮቹ ይሄን ጉዳይ መልክ ካስያዙት በኃላ ሁሉ። የራሳቸውን Discipline ያሲዛሉ " ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia