#update ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ⬆️

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የቬትናም ፕሬዝዳንት የሆኑትን ትራን ዳይ ኩዋንግን አመሻሽ ላይ በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ሁለቱ አገራት በባህል፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ አጀንዳዎች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የሁለቱን አገራት ትብብር የበለጠ ለማጠናከር #ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡

ፈጣን እድገትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማሳካት ከቻሉት የምስራቅ እስያ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ቬትናም ከኢትዮጵያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ 1976 መሆኑ ይታወሳል፡፡

©የጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia