#Tigray

የኢትዮጵያ መንግሥት እና የዓለም ምግብ ፕሮግራም በትግራይ ክልል በጋራ ሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ #ስምምነት ላይ ደርሱ።

ስምምነቱ የመጣው የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ከተመድ የዓለም ምግብ ድርጅት ሥራ አስፈጻሚ ዴቪስ ቤስሊ (ዶ/ር) ጋር በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለው የሰብአዊ ድጋፍ ሁኔታ በጋራ የመስክ ጉብኝት ማደረጋቸውን ተከትሎ ነው።

የኢትዮጵያ መንግሥትና የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድግፉ በስፋት እና በተፋጠነ መልኩ እንዲከናወን መስማማታቸው የአለም ምግብ ፕሮግራም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

በተመሳሳይም በመስክ በተካሄደው ምልከታ መቐለ የሚገኘው የእህል ማከማቻ ለቀጣይ 2 ወራት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎችን መመገብ የሚያስችል የምግብ ክምችት መኖሩን ባለሥልጣናቱ ማረጋገጣቸውን የሠላም ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አሳውቋል። (ኢብኮ)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia