TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሀዋሳ-ወቅታዊ ጉዳይ⬇️

ያልተጣራ ወሬ በህዝቦች መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ያደርጋል።

ከተማችን ሀዋሳ በርካታ ብሄሮችና ብሄረሰቦች #ተቻችለው እና #ተከባብረው የሚኖሩባት እንደሆነ ማንም የሚያውቀው ሀቅ ነው።

ይሁንና በቅርቡ በከተማው የተከሰተውን የፀጥታ ችግር መነሻ በማድረግ በከተማው ነዋሪዎቾ መካከል #ጥርጣሬ እና #አለመደማመጥ እንድፈጠር እንዲሁም ለዘመናት የከተማችን እሴቶች የሆኑት መከባበርና መቻቻል እንድሸረሸሩ እኩይ አላማ ያላቸው ግለሰቦች የተለያዪ የውሸት መረጃዎችን በማህበራዊ ገፅ ላይ እየለቀቁ እንዳሉ መረጃዎች ያሳያሉ።

ለአብነትም በ13/12/2010 በሀዋሳ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን የጫነ ተሽከሪካሪ ተይዟል ተብሎ የተለቀቀው #የሀሰት ወሬ እንደሆነ #ከፓሊስ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

#እውነታው የተያዘው ተሽከሪካሪ 15 ቦንዳ በህገ ወጥ መልኩ /ኮንትሮባንድ/ የገባ እቃ የጫነ እንደሆነ የተረጋገጠ ሲሆን ሌላው በህገ ወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶችን ለማፍረስ የተንቀሳቀሱ ፖሊሶች ተገደሉ ተብሎ የተለቀቀው ፎቶግራፍ የጥፋት ሀይሎች አቀነባብረው የለቀቊት
#የሀሰት_መረጃ እንደሆነ ለመጠቆም እንወዳለን።

በመጨረሻም የከተማችን #ፀጥታ እና #ሰላም እንዳይደፈርስ እንዲሁም በከተማው ህዝብ መካከል ጥርጣሬና አለመተማመን እንዳይፈጠር በዚህ በውሸት መረጃ ህብረተሰቡን በስጋት ላይ የሚትጥሉ አካላት #ከእኩይ ዲርጊታችሁ እንድትታቀቡ እያለ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር #ያሳስባል

የከተማችን ህዝብ በማህበራዊ ገፅ የፌክ አካውንት የከፈቱ አካላት በየጊዜው በሚያሰራጬት #የአሉባልታ ወሬ #እንዳይሸበር እናስታውቃለን።

©አቶ ደስታ ዶጊሶ #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን⬆️

‹‹ … በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የዶሮ እንቁላል ነው በማለት የተለያዩ የተሳቢ እንስሳትን እንቁላል ሲሸጡ የተገኙ ነጋዴዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ …. ›› ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያዎቸና ( በፌስቡክ ) የሚሰራጩ ዜናዎች #የሀሰት መሆናቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ተናግረዋል፡፡ ህብረተሰቡ መሰል ዜናዎችን ከማጋራት እንዲቆጠብና #እንዳይረበሽም ጭምር አሳስበዋል፡፡
.
.
.
ከሰዓታት ቀደም ብሎ ከጋዜጠኛ #ጌጡ_ተመስገን የተገኘ የሀሰት መረጃ ቀርቦ ነበር ይቅርታ ጠይቃለሁ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥንቃቄ⬆️አዲስ አበባ ከተማን ፍፁም የብጥብጥ አውድማ ለማስመሰል በርካታ ሰዎች በፌስቡክ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ከነዚህም መሀል በአክቲቪስት #ጃዋር_መሀመድ ስም #የሀሰት ገፅ ተከፍቶ ህዝቡን ለማበጣበጥ የሚሰሩ ሰዎች ስላሉ ጥንቃቄ ይደረግ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ ማጣራት በጀመረባቸውና ያለ ስራ ታጥረው የተቀመጡ መሬቶችን ለልማት የማዋል ስራ ላይ ሁሉም ቦታዎች ለተደራጁ ወጣቶች ይሰጣሉ የሚለው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው ሲል የከተማ አስተዳደሩ ለሽገር FM ገልጿል። የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ እንደተናገረው በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች በመንግስት ታጥረው የሚገኙ ቦታዎች በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች ይሰጣሉ በሚል #የሀሰት_መረጃ እየተሰራጨ በመሆኑ ነዋሪዎች በሀሰተኛ መረጃ መደናገር የላባቸውም ብሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ተወልደ‼️

"አቶ ተወልደ ገ/ማሪያም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀላፊነት ተነስተዋል የሚለውን ነገር ለማጣራት የአየር መንገዱ Chief Operating Officer (COO) የሆኑት አቶ መስፍን ጣሰው ጋር አሁን ደውዬ ነበር። በመልሳቸውም: "እኔ የማውቀው ነገር የለም። #የሀሰት ዜና ይመስለኛል። ቀኑ ሙሉውን ከአቶ ተወልደ ጋር ነው የዋልኩት።" ሌላ የአየር መንገዱ ሰራተኛ ጋር ጥይቄም "He is in duty" የሚል መልእክት ደርሶኛል። የቦርድ ስብሰባ ግን በዚህ ሰአት እየተካሄደ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። እስካሁን ያለው ነገር ይህን ይመስላል።"

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ኢሳት የተሰኘው የቴሌቭዥን ጣብያ በቢቢሲ በአመቱ #የሀሰት_ዜና ካሰራጩ ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ ገብቷል። ኢሳት የኦሮሞ ተወላጆች ሶማሌዎችን ጉድጓድ ውስጥ ሲከቱ የሚያሳይ ብሎ የለቀቀው ቪድዮ የሀሰት እንደነበርና ይህም በወቅቱ በኦሮሞዎች ላይ ጥቃት እንዲደርስ ምክንያት ሆኖ እንደነበር ዘግቧል።

🔹በወቅቱ ኢሳት ያሰራጨው የሀሰት ቪድዮ እንደሆነ እና ይቅርታ እንደጠየቀ አይዘነጋም።

A year in fake news in Africa:

https://www.bbc.co.uk/news/world-africa-46127868?fbclid=IwAR3-iV_hmwcfkRd9_hFFhDrYuvWSUynsLGPWoy0wWIFwLky1lZQYIC7MAJw

@Tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ‼️

ከሰሞኑ በሀገራችን በሚገኙ የተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ #ያልተፈፀመን ድርጊት የተፈፅመ በማስመሰል በተማሪዎች መካከል #መጠራጠርና አለመረጋጋት ተፈጥሮ የትምህርት ሂደቱን የማደናቀፍ ሙከራዎች እየተደረጉ ነው፡፡

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲም አንዲት ተማሪ ላይ በደረሰ #የአስገድዶ_መድፈር ጥቃት ህይወቷ አለፈ የሚል #የሀሰት መረጃ በማሰራጨት በተማሪዎች መካከል ድንጋጤና ተቃውሞ ተፈጥሮ #የብሄር ተኮር የቡድን ግጭት ለመቀስቀስ ሙከራ ተደርጎ ትናንት ምሽት ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ.ም በዋናው ግቢ ጥቂት ተማሪዎች በቡድን እንዲደባደቡ ምክንያት ሆኗል፡፡ በግጭቱ በተማሪዎች ላይ የከፋ ጉዳት አልተከሰተም፡፡

የመማር ማስተማር ሂደቱ ዛሬ በከፊል የተካሄደ ሲሆን በዩኒቨርሲቲያችንም ዛሬ የፀጥታ ችግር ያልተከሰተ ሲሆን የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታይ ተማሪዎችም ዓመታዊ የቅዱስ ሚካኤል የንግስ በዓልን ገንደ ጄይ አካባቢ በሚገኘው ቤተክርስቲያን ተገኝተው አክብረው ተመልሰዋል፡፡

በተማሪዎቹ መካከል ተከስቶ የነበረው ችግር ዳግም እንዳይከሰት ሊደረግ በሚገባው ጥንቃቄ ዙሪያ ከተማሪዎች ተወካዮችና የጸጥታ አካላት ጋር ዛሬ #ውይይት የተደረገ ሲሆን ተማሪዎችም ችግሩ ዳግም እንዳይከሰት የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለመፍጠር እንዲቻልም ነገ ህዳር 13 ቀን 2011 ዓ.ም የኃይማኖት አባቶች ፤ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በሚገኙበት የዕርቅና የይቅርታ መድረክ ለማዘጋጀት ተስማምተዋል፡፡

ከሰሞኑ በሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርም መግለጫ አውጥቷል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

ህዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

ዛሬ በብዛት ሼር እየተደረገ ያለ #የሀሰት ዜና የሱዳኑ መሪ ሀሰን አልበሽር ስልጣናቸውን ለቀቁ። የዜናው ምንጭ አፍሪካን ዴይሊ የሀሰት ዜናን ከትክክለኛው በመፐወዝ ይታወቃል።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ‼️

በድሬዳዋ ከተማ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የሕዝቡን አብሮነት እና ተቻችሎ የመኖር እሴት የሚሸረሽር በመሆኑ ሰላምን በማወክ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳሰበ፡፡

በድሬድዋ ከተማ ግጭት የተፈጠረው ጥር 13 ቀን 2011 ዓ.ም የጥምቀት ማግስት የቃና-ዘገሊላ በዓልን በሚያከብሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች በፈጠሩት ረብሻ ሳቢያ ነው፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ኡስማን በስልክ ለአብመድ እንደተናገሩት በዕለቱ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ችግር በሁለት እና ሦስት ቀናት ወደ ተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ተስፋፍቷል፡፡

‹‹ሃይማኖታዊ በዓሉን በመረበሽ የድሬዳዋ ከተማን አንድነት መሸርሸር እና አገራዊ ሰላምን ለማደፍረስ ታስቦ የተሠራ ነው›› ብለዋል ከንቲባው፡፡ ግጭቱን ሃይማኖታዊ መልክ እንዲኖረው ለማድረግ ፀብ የማጫር ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውንም ገልፀዋል፡፡ ከክብረ በዓሉ ቀደም ብለው ጭምር ዝግጅት ሲያደርጉ እንደነበርም ነው አቶ ኢብራሂም የጠቆሙት፡፡

ቀደም ብሎ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግም ሌላ የግጭት አጀንዳ እንደተነደፈ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ከንቲባው ገለጻ ችግሩን የሃይማኖት፣ የብሔር፣ የጎሳ እና የፖለቲካ መልክ ለማስያዝ ሙከራዎች ተደርገዋል፡፡

ሰላም በመደፍረሱ ምክንያት የዝርፊያ ወንጀሎች እየተባባሱ እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡

በተለይ ወደ ባንኮች ተደራጂቶ የመሄድ አዝማሚያ መኖሩን፣ መንገድ የመዝጋት፣ የግለሰቦች ቤትና ንብረት የማውደም እና የተወሰኑ የመንግሥት ተቋማት ላይ ጉዳት የማድረስ ሁኔታዎች በከተማዋ መስተዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡

የከተማዋን ሰላም ወደ ነበረበት ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ‹‹ለዚህም ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሠራ ነው፡፡ ከግጭቱ ጀርባ ስውር አጀንዳ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ከ80 በላይ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ ለሕግ የማቅረብ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል›› ነው ያሉት ከንቲባው፡፡

‹‹ችግሩ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኃይል አቅም በላይ በመሆኑ #የመከላከያ_ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊሶች ወደ ከተማዋ ገብተዋል›› ያሉት ከንቲባው ዛሬ በከተማዋ አንጻራዊ ሰላም መኖሩን አስታውቀዋል፡፡

‹‹አንድ ስፍራ ብቻ አሁንም ችግሩ አለ፤ የፀጥታ ኃይሎች ሰላም ለማስከበር ወደ ስፍራው አቅንተው ሰላም የማስከበር ሥራ እየሠሩ ነው›› ብለዋል አቶ ኢብራሂም፡፡

ድርጊቱ የድሬዳዋን ሕዝብ የዘመናት አብሮነት እና ተቻችሎ የመኖር እሴት የሚሸረሽር በመሆኑ ሰላምን በማወክ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል፡፡

በተለይ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው #የሀሰት_ወሬ የድሬድዋን ከተማ ብቻም ሳይሆን የሀገሪቱን ሰላም #ለማደፍረስ እንደ ቤንዚን የሚጠቀሙ ስውር የፖለቲካ አጀንዳ ያላቸው አካላት በመኖራቸው መጠንቀቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
FAKE NEWS‼️

"ሰበር ዜና!! የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል president ሙክታር ከድር እና የቀድሞ አፈጉባኤ አባዱላ ገመዳ ዛሬ ከመኖሬያ ቤታቸው በፌደራል ፖሊስ #ተይዘዋል!!ምንጭ፦ OBN"
.
.
የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ #አድማሱ ወሬው #የሀሰት መሆኑን ለAPው ጋዜጠኛ #ኤልያስ_መሰረት አረጋግጠዋል። አቶ አዲሱ አረጋም "fake news" ብለው በሜሴጅ ለአለም ኣቀፉ ጋዜጠኛ አሳውቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)

በርካታ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች እና ብዙ የሶሻል ሚድያ ተከታታይ ያላቸው ግለሰቦች የአፍሪካ ህብረት አማርኛን ስድስተኛ የስራ ቋንቋው አድርጎ እንደመረጠ ትናንት ሲፅፉ ነበር። እውን ሆኖ "እልል" ባስባሉን እያልኩ ነበር፣ ነገር ግን መረጃው #የሀሰት ነው።

ዛሬ በጠዋቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ቃል አቀባይ የሆነችው ኤባ ካሎንዶ ጋር ደወልኩ። በመልሷም፦

"የቋንቋ ምርጫ የመሪዎቹ አጀንዳ ላይ ጭራሽ አልነበረም። እርግጥ ጠ/ሚር አብይ ስለ አፍሪካ ሀገር በቀል ቋንቋዎች ጥቅም አውርተዋል። የኢኳቶርያል ጊኒው መሪም ቋንቋቸው የአፍሪካ ህብረት ቋንቋ እንዲሆን ይፈልጋሉ። ይህ ማለት ግን ሆኑ ማለት አይደለም። ስለዚህ ኤልያስ፣ አማርኛ የአፍሪካ ህብረት ኦፊሴላዊ ቋንቋ ሆነ የተባለው የሀሰት ዜና (fake news) ነው።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የፌደራል ስርዓት ጉዳይ ለድርድር አይቀርብም" --- ኦዲፒ
.
.
በፌደራል ስርዓቱ ላይ ከማንም ጋር #ለድርድር እንደማይቀመጥ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዲፒ) አስታወቀ። ፓርቲው በትናነትናው እለት ባወጣው መግለጫው፥ ኦዲፒ በአጀንዳነት ይዞ ከሚታገልባቸው ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛው የፌደራል ስርዓቱ ነው ብሏል።

ለፌደራል ስርዓቱ መምጣት ከፍተኛ ዋጋ ተከፍሎበታል ያለው ፓርቲው፥ ስርዓቱ ለድርድር የማይቀርብ መሆኑንም አስታውቋል በመግለጫው። በፌደራል ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ #የሀሰት_ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑንም ኦዲፒ በመግለጫው አስታውቋል።

በአሁኑ ወቅትም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የፌደራል ስርዓቱን ሊያፈርስ እንደሆነ እንዲሁም ህብረተሰቡ በፌደራል ስርዓት ላይ ያለውን እምነት እና ተስፋ እንዲቀንስ ከፍተኛ የሆነ የሀሰት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑንም ገልጿል።

የሀሰት ዘመቻው ሁለት ዓላማ ያለው ነው ያለው ኦዲፒ፥ ከእነዚህም አንደኛው የኢትዮጵያ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሁን ያለውን ለውጥ በጥርጣሬ እንደሚመለከቱ ማድረግ ነው ብሏል።

በዚህም የራሳቸውን ባህል፣ ቋንቋ፣ ማንነት እና ታሪክ ማሳደግን በትግል እና በመስዋእትነት ያገኙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች የፌደራል ስርዓቱ ሊፈርስ ነው በሚል በጥርጣሬ ተቃውሞ እንዲያስነሱ ታስቦ የሚደረግ ሴራ መሆኑንም ገልጿል።

በተጨማሪም የኦሮሞን ህዝብ “ተጨማሪ መብት ማግኘትህ ቀርቶ ከዚህ ቀደም የተገኘውን መብት ልታጣ ነው” በሚል በማደናበር እርስ በርስ ለማጋጨት ያለመ መሆኑንም አስታውቋል።

የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዲፒ) የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄን ለመመለስ እንደሚሰራ በመግለጽ፥ የአዲስ አበባ እና የአፋን ኦሮሞ ጉዳይም እየተሰራበት ያለ መሆኑን ገልጿል።

ከፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጥያቄዎች ላይም ትኩረት በመስጠት እየሰራበት መሆኑን ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል።

ኦዲፒ ለተጨማሪ ድል ይሰራል እንጂ ከዚህ ቀደም የተገኙ ድሎችን አያከሽፍም ያለው ፓርቲው፥ በፌደራል ስርዓት ጉዳይ ላይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥም ገልጿል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

በአርቲስት #ሙሉቀን_መለሰ "ህልፈት" ዙርያ የተሰራጨው መረጃ #የሀሰት ሆኖ ተገኝቷል።

Via ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት/ @eliasmeseret /
@tsegabwolde @tikvahethiopia