TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሁን⬆️የእንቦጭ አረምን አስመልክቶ ከተለያዩ አጋር አካላትጋር #ውይይት እየተካሄደ ነው። ውይይቱ በ2010 በጀት ዓመት የእንቦጭ አረም አወጋገድ አፈጻጸምንና በ2011 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ ዙሪያ ያተኮረ ነው። በ2010 የበጀት ዓመት በነበረው የእምቦጭ አረም አወጋገድ ዙሪያ በነበሩ ጥንካሬና ድክመቶች ላይ በአካባቢ ጥበቃ፣ የደን እና የዱር እንሰሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ኃላፊ ዶር. #በላይነህ_አየለ እየቀረበ ነው።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አላማጣ ቆቦ‼️

የትግራይን ክልል ከአማራ ክልል የሚያገናኘው አላማጣ ቆቦ መስመር ለተሽከርካሪዎች ከተዘጋ 5 ቀናት አስቆጥሯል። መንገዱ የተዘጋው በአላማጣ ከተማ #የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱላቸው በጠየቁ የቆቦ ከተማ ወጣቶች ነው ተብሏል።

የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምርያ እንዳስታወቀው ችግሩን #በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት #ውይይት እየተካሄደ ነው።

የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው - መንገዱ በመዘጋቱ ለስራቸውን #እንቅፋት እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ(የትላንት ምሽት ዘገባ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ‼️

ከሰሞኑ በሀገራችን በሚገኙ የተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ #ያልተፈፀመን ድርጊት የተፈፅመ በማስመሰል በተማሪዎች መካከል #መጠራጠርና አለመረጋጋት ተፈጥሮ የትምህርት ሂደቱን የማደናቀፍ ሙከራዎች እየተደረጉ ነው፡፡

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲም አንዲት ተማሪ ላይ በደረሰ #የአስገድዶ_መድፈር ጥቃት ህይወቷ አለፈ የሚል #የሀሰት መረጃ በማሰራጨት በተማሪዎች መካከል ድንጋጤና ተቃውሞ ተፈጥሮ #የብሄር ተኮር የቡድን ግጭት ለመቀስቀስ ሙከራ ተደርጎ ትናንት ምሽት ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ.ም በዋናው ግቢ ጥቂት ተማሪዎች በቡድን እንዲደባደቡ ምክንያት ሆኗል፡፡ በግጭቱ በተማሪዎች ላይ የከፋ ጉዳት አልተከሰተም፡፡

የመማር ማስተማር ሂደቱ ዛሬ በከፊል የተካሄደ ሲሆን በዩኒቨርሲቲያችንም ዛሬ የፀጥታ ችግር ያልተከሰተ ሲሆን የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታይ ተማሪዎችም ዓመታዊ የቅዱስ ሚካኤል የንግስ በዓልን ገንደ ጄይ አካባቢ በሚገኘው ቤተክርስቲያን ተገኝተው አክብረው ተመልሰዋል፡፡

በተማሪዎቹ መካከል ተከስቶ የነበረው ችግር ዳግም እንዳይከሰት ሊደረግ በሚገባው ጥንቃቄ ዙሪያ ከተማሪዎች ተወካዮችና የጸጥታ አካላት ጋር ዛሬ #ውይይት የተደረገ ሲሆን ተማሪዎችም ችግሩ ዳግም እንዳይከሰት የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለመፍጠር እንዲቻልም ነገ ህዳር 13 ቀን 2011 ዓ.ም የኃይማኖት አባቶች ፤ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በሚገኙበት የዕርቅና የይቅርታ መድረክ ለማዘጋጀት ተስማምተዋል፡፡

ከሰሞኑ በሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርም መግለጫ አውጥቷል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

ህዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ‼️

የተቋሙ ተማሪዎች በግቢው ውስጥ የተፈጠረው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ እና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉንም ያካተተ #ውይይት ሊደረግ ይገባል ብለዋል። ትላንት የተወሰኑ ተማሪዎች ተስማምተው ግቢው ውስጥ ሰላም ወርዶ የነበር ቢሆንም ምሽት ላይ ተማሪ ተጋጭቶ ነበር በዚህም የፀጥታ አካላት እርምጃ ውስደዋል ሲሉ ተማሪዎች ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አ.አ.ሳ.ቴ🔝የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (AASTU) ተማሪዎች ከፀጥታ አካላት ጋር #ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህዳሴው ግድብ‼️

በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የተለዩ ክፍተቶችን በማስተካከል
በፈረንጆቹ 2022 #እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ።

በዛሬው ዕለት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ አስመልክቶ #ውይይት እየተካሄደ ነው።

ጥልቅ ጥናትና ምርምር ስራ ሳይከናወንለት ግንባታው በመጀመሩ ምክንያት ግንባታ ጊዜው ሊጓተት እንደቻለ የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ታላቁ የኢትዮዽያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያስከተለው ጉዳት ሀገሪቷ በየዓመቱ 800 ሚሊየን ዶላር እንድታጣ አድርጓታል ተብሏል።

የግንባታው ስራው በአሁን ወቅት የሚገኝበት ደራጀም በዛሬው ዕለት እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት ወቅት ይፋ ሆኗል።

በዚህም በሳሊኒ ሲሰራ የነበረው የሲቪል ምህንድስናው ስራው 82 በመቶ ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራው ደግሞ 25 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል በውይይቱ ወቅት።

በአጠቃላይ የህዳሴ ግድብ ግንባታ 65 በመቶ መጠነቀቁ ተነግሯል። ከዚህ ባለፈ የግንባታው ፅህፈት ቤት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይልና ከውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስቴር የግንባታ ሂደቱን ለማፋጠን በትብብር እየሰሩ ይገኛሉ።

የህዝባዊ ተሳትፎን ፣ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ባለው የሶስትዮሽ ግንኙነት እና የኃይል ሽያጭ ትስስር ላይ ትኩረት ባደረጉ አራት ጉዳዮች ላይ ውይይቱ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከዛላምበሳ ግምባር የጦር መሳሪያ ጭነው ወደ መሀል ሀገር ሲንቀሳቀሱ #የታገቱ የመከላከያ ተሽከርካሪዎች #ተለቀዋል። የመከላከያ ተሽከርካሪዎቹ የተለቀቁት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር #ውይይት ተደርጎ ስምምነት ላይ በመደረሱ ነው።

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ላይቭ ሀፕዴት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፖሊስ በቂ ዝግጅት አድርጓል~ሀዋሳ‼️

በሃዋሳ ከተማ ነገ ለሚካሄደው የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ #ይፋጠንልን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን የሃዋሳ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ። 

የከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር #መስፍን_ዴቢሶ ለኢዜአ እንደገለጹት ነገ በሃዋሳ የሚካሄደውን ሰልፍ ተከትሎ #ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ዝግጅት ተደርጓል።

የከተማው ፖሊስ ከዞን፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ሰልፉ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች በቂ ጥበቃ ያደርጋልም ብለዋል፡፡

ፖሊስ አዛዡ እንዳሉት ከሪፈራል አደባባይ ጠዋት አንድ ሰዓት የሚጀመረው ሰላማዊ ሰልፍ መዳረሻው ከቀኑ ስድስት ሰዓት ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም ነው፡፡

ሰልፉ ወደ ብሉናይል የሚያወጣውን አስፓልት ይዞ ተስፋዬ ግዛው ህንጻ አደባባይ ሲደርስ ወደ ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም እንደሚገባና ማጠቃለያውን እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

በዚህ ምክንያት መንገዶቹ ለተሸከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ያሉት ኮማንደር መስፍን፤ በበቂ የፀጥታ ሃይል ጥበቃ እንደሚደረግም ገልጸዋል፡፡

የከተማው ነዋሪ በሰልፉ ምክንያት ስጋት ውስጥ እንዳይገባ በየክፍለ ከተማው #ውይይት መደረጉን ገልጸው ህዝቡም ለሰልፉ ሰላማዊነት የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡

የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ የሚዲያ ተጠሪ አቶ ሳሙኤል በላይነህ በበኩሉ የሲዳማ ብሄር በክልል የመደራጀት ህገ-መንግስታዊ ጥያቄውን ተከትሎ ህዝበ ውሳኔው በመዘግየቱ የተዘጋጀ ሰልፍ ነው” ብሏል።

ዓላማውም “ከዞን ምክር ቤት ጀምሮ በክልሉ ምክር ቤት ጸድቆ ለህዝበ ውሳኔ ለምርጫ ቦርድ የተላከው ሪፈረንደም ጥያቄ ዘግይቷል ይፋጠንልን” የሚል መሆኑን ተናግሯል።

ጥያቄው ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን ተከትሎ የቀረበ ቢሆንም ምላሹ በመዘግየቱ በዞኑ ካሉ ወረዳዎችና ከሃዋሳ ከተማ የተውጣጡ ነዋሪዎች መንግስትን በሰላማዊ መንገድ የሚጠይቁበት እንደሆነም ተናግሯል፡፡

“ሰልፉ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከከተማው ፖሊስና ከሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ጋር በቅንጅት እየሰራን ነው” ብሏል፡፡

በሰላማዊ ሰልፉ የመንግስት አካላት፣ የተለያዩ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችና የሰልፉ ደጋፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ‼️

ነገ ለሚደረገው #ሰላማዊ_ሰልፍ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ከዞን ፖሊስ፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና #ከፌደራል_ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ሰልፉ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች በቂ ጥበቃ ያደርጋል። ከሪፈራል አደባባይ ጠዋት አንድ ሰዓት የሚጀመረው ሰላማዊ ሰልፍ መዳረሻው ከቀኑ ስድስት ሰዓት ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም ነው፡፡

ሰልፉ ወደ ብሉናይል የሚያወጣውን አስፓልት ይዞ ተስፋዬ ግዛው ህንጻ አደባባይ ሲደርስ ወደ ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም እንደሚገባና ማጠቃለያውን እንደሚያደርግ ተናግሯል። በዚህ ምክንያት መንገዶቹ ለተሸከርካሪ #ዝግ ይሆናሉ እንዲሁም በበቂ የፀጥታ ሃይል ጥበቃ ይደረጋል፡፡ የከተማው ነዋሪ በሰልፉ ምክንያት #ስጋት ውስጥ እንዳይገባ በየክፍለ ከተማው #ውይይት መደረጉ ተገልጿል፤ ህዝቡም ለሰልፉ ሰላማዊነት #የበኩሉን እንዲወጣ ተጠይቋል፡፡

በተጨማሪ፦

የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ #ሀሰተኛ_መረጃዎች ራሱን እንዲያርቅ ጥሪ ቀርቧል። ነዋሪው ምንም አይነት ሰላም የማደፍረስ እንቅስቃሴ ካየ ለፀጥታ ሀይሉ #ጥቆማ እንዲያደርስ ጥሪ ተላልፏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ብቻዬን ብቀር እንኳ #ትግሌን እቀጥላለሁ" ጃል መሮ የኦነግ ጦር አዛዥ
.
.
በመንግሥትና በኦነግ መካከል በሽማግሌዎች አማካይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ በርካታ የግንባሩ አባላት ተሰማርተው ከነበሩባቸው ቦታዎች #በሰላም እየተመለሱ ቢሆንም በምዕራብ ኦሮሚያ የሚንቀሳቀሰው የኦነግ ኃይል አዛዥ ግን ይህንን ለመፈፀም ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።

በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተሰማርተው የሚገኙ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጦር አባላት የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትለው #ትጥቅ_ፈትተው ወደ ጦር ካምፖች ከመግባታቸው በፊት ወደተዘጋጁላቸው ጊዜያዊ ማቆያ ስፍራዎች በዚህ ሳምንት እየገቡ እንደሆነ እየተዘገበ ነው።

ሽምግልናውን የመሩትና ስምምነቱ ከፍጻሜ እንዲደርስ ጥረት እያደረጉ ያሉት አባገዳዎች እና የየአካባቢዎቹ ባለስልጣናት ለውሳኔው ተገዢ በመሆን ወደተዘጋጁላቸው ስፍራዎች ከነትጥቃቸው ሲመጡ አቀባበል እያደረጉላቸው ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትሎ ሁሉም የኦነግ ጦር አባላት እየተመለሱ እንዳልሆነ ከተመለሱት የኦነግ ጦር አባላት ተሰምቷል።

ለዚህም እንደምክንያት የሚጠቀሰው የምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር አዛዥ የሆነው ኩምሳ ድሪባ ወይም በትግል ስሙ በስፋት የሚታወቀው ጓድ መሮ የአባገዳዎችን ጥሪ አለመቀበሉ ነው።

በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኘው የኦነግ ጦር አዛዥ እንደሆነ በስፋት የሚነገርለት ኩምሳ ድሪባ (መሮ) ወይም መሮን ቢቢሲ ስለዚሁ ጉዳይ በስልክ አነጋግሮታል። እንደተባለውም መሮ ባለው ሁኔታ ስምምነቱን ተቀብሎ ለመግባት ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።

የአባገዳዎችን ጥሪ ለመቀበል እና እርቅ ለማውረድ ዝግጁ ስለመሆኑ ሲጠየቅም "የእርቅ የተባለው ኮሚቴ እኔን በአካል አግኝተው ለማነጋገር ፍላጎት የላቸውም። ትኩረት ያደረጉት ጦሩን አንድ በአንድ እጁን እንዲሰጥ ማድረግ ላይ ነው" በማለት እሱም እነሱን ለማግኘት ያደረገው ጥረት አለመሳካቱን ይናገራል።

እንዲያውም "ጦሩን የመበታተን ዓላማ ይዘው ነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት" ሲል ይከሳል።

የኦነግ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዳውድ ኢብሳ የእርቅ ኮሚቴውን በመደገፍ የኦነግ ጦር ጥሪውን ተቀብሎ ወደተዘጋጀለት ስፍራ እንዲሄድ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። የጦሩ መሪ መሮ የግንባሩ ሊቀመንበር ተገዢ መሆን አለመሆኑን ተጠይቆ ሲመልስ "ሊቀመንበሩ የእርቅ ኮሚቴውን ያሉት፤ 'የኦነግ ጦር የእናንተው ነው። ሂዱና አወያይታችሁ የሚሉትን ስሟቸው' ነው ያሉት" ብሏል።

ጨምሮም እንደተናገረው "እኔ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እንወያይ ነው ያልኩት እንጂ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ ጥቅም የለውም፤ የኦሮሞ ህዝብ መሰቃየት የለበትም ነው የምለው። እነሱ ግን የጦሩ አባላት የእጅ ስልክ ላይ እየደወሉ አንድ በአንድ ጦሩን የማፍረስ ሥራ ነው እየሰሩ የሚገኙት" ሲል ገልጸወል።

ያለው ችግር ከስር መሰረቱ ምፍትሄ አላገኘም ብሎ የሚያምነው መሮ አሁን እየተደረገ ያለው "በተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ሰዎችን አንድ በአንድ የማስኮብለል ሥራ ነው። ከዚህ የተለየን ጦር 5 በመቶ እንኳ አይሆንም። 95በመቶ አሁንም እንደታጠቀ ነው የሚገኘው" በማለት ተናግሯል።

"ወደፊት መራራ ትግል ማድረጋችንን እንቀጥላለን" ያለው መሮ "ብቻዬን ብቀር እንኳ #ትግል ማድረጌን እቀጥላለሁ እቅዴም ይሄው ነው" በማለት በትጥቅ ትግሉ እንደሚቀጥል ጠንከር በማለት ተናግሯል።

የቀረበውን የእርቅ ጥሪ ተቀብለው ከገቡት የኦነግ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የግንባሩ ጦር የሞራል እና ፖለቲካ መምህር የ57 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ አቶ #ታፈሰ_ኦላና በመሮ በኩል ያሉት ወታደሮች እየተመለሱ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል።

ጨምረውም "መሮ መመለስ አይፈልግም፤ ስልክ እየደወለ #ጸያፍ_ቃል እየተናገረን ነው። 'እጃችሁን ለአባገዳዎች እየሰጣችሁ ሰዎች ከትግላችን ዓላማ ውጪ የሆነ ተግባር እየፈጸማችሁ ነው። ታሪክ ይፋረዳችኋል' እያለ ያስጠነቅቀናል።"

አቶ ታፈሰ እንደሚሉት አሁንም በምዕራብ ኦሮሚያ ትዕዛዝ የሚሰጠው መሮ መሆኑንና "የኦሮሞን ምድር የጦር አውድማ ማድረግ ነው የሚፈልገው። ህዝብ ሰላም እየፈለገ እሱ ግን አሁንም ደም ማፍሰስ የሚፈልግ ከሆነ ተሳስቷል" ብለዋል።

የኦነግ የምዕራብ ኦሮሚያ ጦር አዛዥ መሮ በአባ ገዳዎች የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው ወደተዘጋጀላቸው ስፍራ የሄዱ የጦሩ አባላት ላይ ይሰነዝራል ስለተባለው ማስፈራሪያን በተመለከተ "የምን ማስፈራራት ነው። መሳሪያ ይዘን እያየናቸው እኮ ነው እየሄዱ ያሉት። ምርጫቸው ነው። ማንም ማንንም አላስፈራራም" ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

መሮ ችግሩን ለመፍታትም እንደቅድመ ሁኔታ የሚጠይቀው "በደቡብ ኢትዮጵያ እና በተለያዩ ዞኖች ከሚገኙ አባላቶቻችን ጋር በቅድመ ሁኔታዎች ላይ #ውይይት ማድረግ አለብን" በማለት የሽምግልና ኮሚቴውም እንዲያወያያቸውና "አንድ በአንድ የጦሩን አባላት ማስኮብለል" ያለውን ድርጊት ማስቆም እንዳለባቸው ተናግሯል።

የእርቅ ኮሚቴው ጸኃፊ የሆነውን #ጀዋር_መሐመድ በበኩሉ የኮሚቴው አባላት በተንቀሳቀሱባቸው ስፍራዎች ሁሉ የኦነግ የጦር አመራሮችን ለማግኘት ያደረጉት ጥረት የጦሩ አመራሮች ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው ሳይሳካ እንደቀረ ይናገራል።

ጃዋር ''ወደ ምዕራብ ኦሮሚያ የተጓዙት አቶ በቀለ ገርባ እና አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ያደረጉት ሙከራ #አልተሳካላቸውም። ወደ ደቡብ ኦሮሚያ የሄድኩት ደግሞ እኔ ነበርኩኝ። የኦነግ የምዕራብ ዞን የጦር ኃላፊ ሊያገኘን ፍቃደኛ #አልነበረም።'' ሲል ተናግሯል።

ምንጭ፦ BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia