TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሀዋሳ-ወቅታዊ ጉዳይ⬇️

ያልተጣራ ወሬ በህዝቦች መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ያደርጋል።

ከተማችን ሀዋሳ በርካታ ብሄሮችና ብሄረሰቦች #ተቻችለው እና #ተከባብረው የሚኖሩባት እንደሆነ ማንም የሚያውቀው ሀቅ ነው።

ይሁንና በቅርቡ በከተማው የተከሰተውን የፀጥታ ችግር መነሻ በማድረግ በከተማው ነዋሪዎቾ መካከል #ጥርጣሬ እና #አለመደማመጥ እንድፈጠር እንዲሁም ለዘመናት የከተማችን እሴቶች የሆኑት መከባበርና መቻቻል እንድሸረሸሩ እኩይ አላማ ያላቸው ግለሰቦች የተለያዪ የውሸት መረጃዎችን በማህበራዊ ገፅ ላይ እየለቀቁ እንዳሉ መረጃዎች ያሳያሉ።

ለአብነትም በ13/12/2010 በሀዋሳ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን የጫነ ተሽከሪካሪ ተይዟል ተብሎ የተለቀቀው #የሀሰት ወሬ እንደሆነ #ከፓሊስ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

#እውነታው የተያዘው ተሽከሪካሪ 15 ቦንዳ በህገ ወጥ መልኩ /ኮንትሮባንድ/ የገባ እቃ የጫነ እንደሆነ የተረጋገጠ ሲሆን ሌላው በህገ ወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶችን ለማፍረስ የተንቀሳቀሱ ፖሊሶች ተገደሉ ተብሎ የተለቀቀው ፎቶግራፍ የጥፋት ሀይሎች አቀነባብረው የለቀቊት
#የሀሰት_መረጃ እንደሆነ ለመጠቆም እንወዳለን።

በመጨረሻም የከተማችን #ፀጥታ እና #ሰላም እንዳይደፈርስ እንዲሁም በከተማው ህዝብ መካከል ጥርጣሬና አለመተማመን እንዳይፈጠር በዚህ በውሸት መረጃ ህብረተሰቡን በስጋት ላይ የሚትጥሉ አካላት #ከእኩይ ዲርጊታችሁ እንድትታቀቡ እያለ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር #ያሳስባል

የከተማችን ህዝብ በማህበራዊ ገፅ የፌክ አካውንት የከፈቱ አካላት በየጊዜው በሚያሰራጬት #የአሉባልታ ወሬ #እንዳይሸበር እናስታውቃለን።

©አቶ ደስታ ዶጊሶ #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia