TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#CARD

በመብቶች ዴሞክራሲ ብልፅግና ማዕከል (CARD) አማካኝነት ሶሻል ሚዲያ ላይ ንቁ ተሳታፊ ከሆኑና መረጃዎችን እንዲሁም ኃሳቦችን በማቅረብ ከሚሳተፉ ሚዲያዎችና ግለሰቦች ጋር በምርጫ ህጉ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዛሬ ተካሂዷል፡፡

የCARD ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ አጥናፉ ብርሃኔ እንደገለጹት ሌሎች ሚዲያዎች የራሳቸውን ሰው የማሰልጠን አቅሙ ይኖራቸዋል ነገር ግን ሶሻል ሚዲያው ላይ ላሉ አዘጋጆች ታስቦ የሚዘጋጅ ባለመኖሩ ማዕከሉ ይህንን መሰረት አድርጎ ዝግጅቱን እንዳዘጋጀ ገልጸዋል፡፡

ለተሳታፊዎቹ ስለአጠቃላይ ህጉ መግለጫ የሰጡትና ለተነሱ ጥያቄዎችም መልስ የሰጡት የምርጫ ቦርድ የኮሚውኒኬሽን አማካሪ ወይዘሪት ሶልያና ሽመልስ ሲሆኑ ከዚህ በፊት የነበረውን አዋጅ ጨምሮ በአዲሱ የተቀየሩ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ከተሳታፊዎችም ወቅታዊ እና በምርጫ ጊዜ ሊከሰቱ ይችላሉ የተባሉ አንኳር ነጥቦች ከሕጉ አንጻር ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ በቀጣይም ተመሳሳይ ውይይቶች እንደሚካሄዱ ማዕከሉ ገልጿል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#CARD

የመብቶችና ዲሞክራሲ ብልጽግና ማዕከል ባለፉት ስድስት ወራት ባደረገው የማህበራዊ ሚዲያዎች ቅኝት አስተውሏል፡፡ በዚህም የተዛቡ መረጃዎችን የሚሰራጩ ሰዎች የመጀመሪያ ምክንያታቸው በተመልካች ብዛት የገቢ ምንጭ ቢሆንም ለፓለቲካዊ ዓላማ፣ ለተራ ዝናና ግላዊ ብሽሽቅ እንዲሁም ባለማወቅ እና እንደመዝናኛነት በመቁጠርም ጭምር እንደሆነ ቅኝቱ አመላክቷል ተብሏል፡፡

በቅኝቱ መሰረት የጥላቻ ንግግሮች የሚበራከቱባቸው የተለያዩ ጊዜያት መኖራቸው ተጠቁሟል፡፡ እነዚህም የተቃውሞ ሰልፎችና ግጭቶች በሚከሰሰቱባቸው ወቅቶች፣ ሃይማኖታዊ በዓላትና ፌስቲቫሎች በሚኖሩበት ሰዓት፣ በዩኒቨርሲቲዎች በሚነሱ ግጭቶች፣ የፓለቲካ መሪዎች የገቢ ማሰባሰቢያ ሲያደርጉና ምርጫዎችና ህዝበ ውሳኔዎች ሲካሄዱ ይጨምራል፡፡

ይህ ደግሞ ምርጫው እየተቃረበ ሲመጣ የሚጨምር ይሆናል፡፡ ከወዲሁም በቅኝቱ በተደራጀ መልኩ የስም ማጥፋትና የማጥላላት ዘመቻዎች እየተካሄዱ መሆኑን ማየት ተችሏል፡፡ ይህም ዜጎችን በተሳሳተ መረጃ ለማይፈልጉት አካል ድምጻቸውን እንዲሰጡ ሊያደርግ ይችላል ሲል ፍራቻውን ይገልጻል፡፡

በመጨረሻም ማዕከሉ የህዝብን አረዳድ በመጨመር ግንዛቤ መፍጠር ላይ አተኩሮ የሚሰራ እንደሆነና በቀጣይ በሚኖሩ መግለጫዎች አጥፊዎችን በግልጽ በመለየት የሚያሳውቅ ይሆናል ተብሏል፡፡ ከዚህ ባሻገር ጋዜጠኞች የሐቅ ማረጋገጥ ሥራ በመስራትና ዜጎችም የጥላቻ ንግግር ባለማጋራት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተጠቁሟል፡፡

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaabot
CARD FoE and Legitimate Restrictions.pdf
1.2 MB
7ቱ የተዛቡ መረጃ ዓይነቶች!

1ኛ - ስላቅ ወይም ቀልድ (Satire or Parody) - እነዚህኞቹ አንባቢውን ለመጉዳት ወይም ለማሳሳት የተፈጠሩ ሳይሆን ለማስገረም፣ ለማዝናናት ወይም ባለታሪኩ ላይ ለማላገጥ የተዘጋጁ መረጃዎች ናቸው፤ ነገር ግን በተደራሲዎቹ እንደ እውነት ሊቆጠሩ ይችላሉ።

2ኛ - አሳሳች ይዘት (misleading content) - እነዚህኞቹ መረጃዎቹ ስህተት ባይሆኑም የቀረቡበት መንገድ ግን ተደራሲያኑን በማሳሳት ሌላ ነገር እንዲገምቱ ወይም እንዲያምኑ የሚያደርግ ነው።

3ኛ - የተፈበረከ ይዘት (fabricated content) - ጉዳት ለማስከተል በማሰብ ሙሉ ለሙሉ የተፈጠረ የሐሰት መረጃ።
4ኛ - ለምድ ለባሽ ይዘት (Imposter content) - መረጃው ከታማኝ ምንጭ ወይም ቢሮ የተገኘ ለማስመሰል የተደረገ ነገር ግን የተፈበረከ የሐሰት መረጃ።

5ኛ - የውሸት ግንኙነት (False connection) - ሁለት የማይገናኙ ነገሮችን (ፎቶ እና ታሪኩ፣ ርዕሱና ዝርዝሩ…) እንደሚገናኙ አስመስሎ ማቅረብ።

6ኛ - የውሸት ዐውድ (False context) - እውነተኛ ታሪኮችን እና ምስሎችን እየተጠቀሙ ነገር ግን ከአገባቡ ውጪ በመጥቀስ መረጃ ማዛባት።

7ኛ - አላግባብ የተተረጎመ ይዘት (manipulated content) - መረጃው ብዙ ተመልካች እንዲያገኝ ሲባል ብቻ አዛብቶ ማቅረብ።

[ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትና ቅቡልነት ያላቸው ገደቦች]

#CARD
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#CARD

የጥላቻ ቃላትን እና ዓረፍተ ነገሮችን ለመለየት እና ለመረዳት የሚደረግ ሰርቬይ ነው። ሰርቬዩ የጥላቻ ቃላትን ዝርዝር በተጠና መንገድ በማዘጋጀት የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እንዲያስወግዷቸው ይረዳል። 

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSe2vnd9oVr9iL1TA_Q8T6q9AXpUKNklWrPOkvH5yB_uxLH-SA/viewform?usp=send_form

Qorannoo sarara irraa Itiyophiyaa kessatti tamsaasa jechoota jibbaa fi balaa uumuu dandaa'an ilaalchise godhame.

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdh2N-lwmZBNlKV2jcAB1tEz_9LEIU4krsUzxJKL0ZaN5xg7w/viewform?usp=send_form

This survey intends to identify and understand hate and inflammatory words and terms in Ethiopian local languages. The result will help us develop a lexicon of hate speech terms and phrases to help social media users to avoid the use of them and the social media platform moderate them effectively. 

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScRCF9rDhOQYTf6m7mizLBjUQsjJCYycRjWcUBsHlqp9Tbr0Q/viewform?usp=send_form
ዛሬ ዓርብ (ግንቦት 28/2012 ዓ/ም) በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ያለውን አጠቃላይ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወቅታዊ መረጃ - #CARD #TIKVAH

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እራሳችንን እና ቤተሰቦቻችንን ከኮቪድ-19 እንጠብቅ!

አስከፊውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመግታት አካላዊ ርቀትን መጠበቅ #ዋነኛው የመከላከያ መንገድ ነው።

የበሽታው ስርጭት ፦

- ሠዎች እርስ በእርስ ባላቸው ቅርበት
- አብረው በሚያሳልፋበት ጊዜ
- በሚያደርጉት የሰው ንክኪ ቁጥር ይወሰናል።

#CARD #TIKVAH

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ፦

- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 55 ሰዎች በኮቪድ-19 ተይዘዋል፤ ከነዚህ መካከል 18 ሰዎች ከለገጣፎ፣ 14 ሰዎች ከምስራቅ ሸዋ ይገኙበታል።

- በትግራይ ባለፉት 24 ሰዓት 37 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፤ 18ቱ የውጭ ጉዞ ታሪክ ያላቸው፣ 12 ሰዎች ንክኪ ያላቸውና 7 ሰዎች የውጭ የጉዞ ታሪክና ንክኪ የሌላቸው ናቸው።

- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 115 ምርመራ ተደርጎ 2 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1 ሰው በቫይረሱ ተይዟል ፤ አጠቃላይ በክልሉ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 292 ደርሰዋል።

- በደቡብ ክልል ከተደረገው 578 የላብራቶሪ ምርመራ 24 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጣል ፤ ከነዚህ መካከል 13 ሰዎች ከወላይታ ዞን ናቸው።

- በሱማሌ ክልል ከተደረገው 42 የላብራቶሪ ምርመራ 19 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል ፤ 10 ከጅግጅጋ እንዲሁም 9 ከጎዴ ናቸው።

- በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ሃያ (20) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ ከነዚህ መካከል 9 ሰዎች ከኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ናቸው።

#CARD #TIKVAH
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ፦

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 216 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- 1 ከመተከል ዞን ጉባ ወረዳ
- 2 ከአሶሳ ዞን አሶሳ ወረዳ

#Harari

በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 670 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 15 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የሁለት ሰዎችም ህይወት አልፏል።

አጠቃላይ በሀረሪ ፦
- 366 በቫይረሱ የተያዙ
- 14 ሞት
- 78 ያገገሙ

#Tigray

በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 586 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 66 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ ትላንት 39 ሰዎች አገግመዋል።

አጠቃላይ በትግራይ ፦
- 1,252 በቫይረሱ የተያዙ
- 10 ሞት
- 697 ያገገሙ

#DireDawa

በድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 250 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 36 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 10 ከጅቡቲ ተመላሾች በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ፤ 26 ከማህበረሰቡ በተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 4,086 የላብራቶሪ ምርመራ 70 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

ከነዚህ መካከል

- 25 ከባህር ዳር
- 13 ከምዕራብ ጎንደር ዞን
- 12 ከሰሜን ሸዋ ዞን
- 7 ከደ/ጎንዳር ዞን
- 6 ከሰ/ወሎ ዞን
- 3 ከምስ/ጎጃም ዞን
- 3 ከደሴ ከተማ
- 1 ከማዕ/ጎንድር

#Sidama

በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 252 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 14 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል፤ የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 6 ሰዎች ከሀዋሳ ይገኙበታል።

#CARD #TIKVAH
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በሀገር አቀፍ ደረጃ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ 943 ሰዎች መካከል 612 ሰዎች ከአዲስ አበባ ከተማ ናቸው።

ከፍተኛ ኬዝ ከተመዘገበባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተማዎች መካከል አራዳ (124)፣ ቦሌ (84)፣ ጉለሌ (80) በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

በተጨማሪ በ24 ሰዓት በሀገሪቱ ከተመዘገበው ሃያ ሶስት የሟቾች ቁጥር 18 ከአዲስ አበባ ከተማ ናቸው ፤ 13 ሰዎች ከአስክሬን ምርመራና 5 ሰዎች ከጤና ተቋም መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ መረጃ ያሳያል።

#CARD #TIKVAH
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ታማሚዎች ብዛት ሁሉንም ጎረቤት ሀገራት በልጣ #በመጀመሪያው ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

ግንቦት 24/2012 ዓ/ም

• ሱዳን - 5,026
• ጅቡቲ - 3,569
• ሱማሊያ - 2,023
• ኬንያ - 2,021
• ኢትዮጵያ - 1,257
• ደ/ሱዳን - 994
• ኤርትራ - 39

ዛሬ ነሃሴ 11/2012 ዓ/ም

• ኢትዮጵያ - 31,336
• ኬንያ - 30,365
• ሱዳን - 12,410
• ጅቡቲ - 5,369
• ሱማሊያ - 3,257
• ደ/ሱዳን - 2,489
• ኤርትራ - 285

በነገራችን ላይ በ24 ሰዓት ውስጥ በኢትዮጵያ የሚደረገው የላብራቶሪ ምርመራ ከሌሎቹ ሀገራት በእጅጉ ይልቃል።

#CARD #TIKVAH
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ATTENTION

በአዲስ አበባ ያለው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ይገኛል። ትላንት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተመዘገበው 1,778 ኬዞች 836ቱ ከአዲስ አበባ ከተማ ነው።

በተጨማሪ ትላንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው 20 ሞት ሁሉም ከአዲስ አበባ ከተማ ነው። ከአ/አ ጤና ቢሮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው 15 ከአስክሬን ምርመራ 5 ደግሞ ከጤና ተቋም ናቸው።

ወረርሽኙ እጅግ ከበረታባቸው የአ/አ ክፍለ ከተሞች መካከል ቦሌ (3,410) ፣ ጉለሌ (2,570) ፣ የካ (2,327) ፣ አዲስ ከተማ (2,227) ፣ ኮልፌ ቀራንዮ (2,172) ፣ አራዳ (2,030) ይገኙበታል።

ዛሬ በከተማይቱ ቅኝት አድርገናል ብዙ ቦታዎች ላይ ፍፁም ወረርሽኙ የሌለ እስኪመስል ድረስ መዘናጋት ይታያል። ምንም እንኳን ማስክ የማድረጉ ልምድ እየጨመረ ቢመጣም አካላዊ ርቀትን የመጠበቅ ሁኔታ አሁንም ብዙ ስራ የሚጠይቅ ነው።

ሁላችንም ከአስከፊው ወረርሽኝ እራሳችንን እንጠብቅ!

#CARD #TIKVAHETHIOPIA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በመራጭነት ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል? መምረጥ የማይችሉ ዜጎች አሉ ?

ለመራጭነት ለመመዝገብ ፦

- ኢትዮጵያዊ ዜግነት

- እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ

- 6 ወራት ነዋሪነት

- ነዋሪነት ማረጋገጫ መታወቂያ ወይም ሌላ ሰነድ ወይም ነዋሪነት የሚያውቁ ምስክሮች

በመራጭነት መመዝገብ የማይችሉ ፦

- በአዕምሮ ሕመም ሳቢያ የመወሰን አቅም ውስንነት ያለባቸው

- የእስር ፍርደኞች

- የመምረጥ መብታቸው በሕግ የተገደበባቸው

#CARD

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#MoSHE

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት የምርምር፤ አፕላይድ ሳይንስ፣ ኮምፕሬሄንሲቭ፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ቴክኒካል በሚል ከለያቸው ውስጥ የትኞቹ የቅድመ ምዘና ፈተና ይሰጣሉ ?

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በመባል ከተለዩት ፦
- ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርስቲ ውጪ ምንም አይነት የቅድመ ምዘና ፈተና እንደማይሰጥ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ለ @tikvahuniversity ገልጿል።

ሚኒስቴሩ አሁን ላይ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ በቀጥታ እንደሚገቡ ነው የገለፀው፤ ሆኖም የመጀመሪያ ዓመት (freshman) ትምህርታቸውን አጠናቀው የትምህርት ክፍል ምርጫ ሲያደርጉ የምዘና ፈተና ሊወስዱ እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።

በተጨማሪ መረጃ ፦ የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርስቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ መኩሪያ ንጋቱ ዩኒቨርሲቲው አዲስ ለሚገቡ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና እንደሚሰጥ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጠዋል።

"የምንሰጠው ስልጠና 50 በመቶው የተግባር ስልጠና በመሆኑ ብዙ ተማሪዎችን መቀበል አንችልም" ያሉት ኃላፊው፤ ስልጠናው ብዙ ሰርቶ ማሳያ ማዕከላና ከፍተኛ ሃብት እንደሚጠይቅ ነው የገለፁት።

#CARD #TikvahUniversity

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 22 ተማሪዎቹን ያስመርቃል።

የደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ ለ @tikvahuniversity እንዳሳወቀው በተለያዩ ትምህርት መስኮች ያሰለጠኛቸውን ተማሪዎቹን ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ/ም ያስመርቃል።

ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ 3ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና የማታ መርሀ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አህመድ መሀመድ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ትምህርት በመጠናቀቁ ነባር ተማሪዎች (ከተመራቂዎች በስተቀር) ሰኔ 11 እና 12/2013 ዓ.ም እረፍት እንደሚወጡ ኃላፊው ገልፀዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከሰኔ 25 እስከ 30/2013 ዓ.ም ጥሪ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ : https://publielectoral.lat/joinchat/RYD_4tbNBwRoKR2h

#CARD #TIKVAH

@tikvahuniversity
የአሠልጣኞች ሥልጠና ጥሪ - #CARD

ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት መምህራን መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ፅንሰ-ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና !

የመብቶች ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD) በአዲስ አበባ፣ ቢሾፍቱ ፣ አዳማ፣ ደብረብርሀን፣ ድሬዳዋ፣ ሀዋሳና ሀረሪ ክልሎች ውስጥ ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የስነዜጋና ስነምግባር ትምህርት መምህራን የሰብዓዊ መብቶች ፅንሰ-ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት አቅዷል።

ሥልጠናው “የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች አዲስ ትውልድ’’ የተባለውና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሠራው ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው መሆኑን ገልጿል።

ከስልጠናው በኋላ ተቋሙ በተጠቀሱት አካባቢዎች በቀጣይነት ለሚኖረው የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች መሰረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ስልጠና ሂደቶችን በማስተባበር ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ለማድረግ አቅዷል።

ለመመዝገብ https://bit.ly/3vu4rZK

@tikvahethiopia
#CARD

የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንደ አዲስ ማገርሸቱ ለጥቂት ወራት ታይቶ የነበረውን የሰላም ጭላንጭል ተስፋ እንዳደበዘዘው ገልጿል።

ካርድ ፤ የግጭቱን እና የጦርነት ፕሮፖጋንዳውን ማባባስ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልጾ ሁሉም ወገኖች ጦርነቱንና ግጭቱን ከሚያባብሱ ትርክቶና ድርጊቶች እንዲታቀበ ጥሪ አቅርቧል።

በተጨማሪም የዓለም ዐቀፍ ሰብዓዊነት ህግጋት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በተለያዩ የማኅበረ-ፖለቲካዊ ዘርፎች የሠለጠኑ ባለሙያዎች ተሳትፎ የክልሎች አስተዳደር ከዴሞክራሲያዊ መርሖዎች አንፃር የሚመዘንበትን ሒደት አመቻችቷል።

የምዘናው ዋነኛ አካል ባለሙያዎች የሚሳተፉበት ወርክሾፕ ሲሆን፣ በወርክሾፑ የሚሳተፉት ባለሙያዎች በሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ላይ እየተወያዩ ምዘናቸውን ይሰጣሉ።

በእነዚህ ወርክሾፖች የሚሳተፉ ባለሙያዎች የዕለት ወጪ አበል ይታሰብላቸዋል። 

የምዘና ሒደቱ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች የሚከተሉት ሙያዊ ብቃቶች ሊኖሯቸው ይገባል ፦

▪️በአንድ ክልል ወይም ክልሎች ውስጥ ያለውን አስተዳደራዊ ሁኔታ በቅርብ የሚያውቁ እና የሚከታተሉ፣ 

▪️በሲቪል ነጻነት፣ በምርጫ እና ፖለቲካዊ ብዝኃነት፣ በማኅበረ-ፖለቲካዊ መብቶች፣ በመንግሥት አገልግሎት ቀልጣፋነት፣ በአናሳ ቁጥር ያላቸው ሕዝቦች ጥበቃ፣ ወይም በሥልጣን ቁጥጥር እና ሚዛን ርዕሰ ጉዳዮች የተለየ ትኩረት እና ዕውቀት ያላቸው፣

▪️ለጉዳዩ ረብነት ባለው የማኅበራዊ ሳይንስ ጥናት ሁለተኛ ዲግሪ ወይም ከዚያ በላይ ያለቸው፣ 

የተመረጡ አመልካቾች 30 ጥያቄዎች ላይ በመወያየት መጠይቅ የሚሞሉበት ወርክሾፕ ላይ ለአንድ ቀን ይሳተፋሉ።

ተሳታፊዎች በቀን 3,000 ብር (ሶስት ሺህ ብር) አበል ይታሰብላቸዋል።

አንዳንድ ባለሙያዎች በትምህርት እና ልምዳቸው መሠረት በበርካታ ወርክሾፖች ላይ እንዲሳተፉ ሊመረጡ ይችላሉ። 

በእነዚህ ወርክሾፕ ላይ ለመሳተፍ ይህንን ሊንክ ክሊክ በማድረግ ፎርሙን ይሙሉ።

የማመልከቻው ጊዜ መጠናቀቂያ ሐምሌ 29፣ 2015 ነው።

#CARD
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#CARD: ይህን የ4 ደቂቃ መረጃ ዳሰሳ ጥናት በመሙላት የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመግታት የምንሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ መመርያ ያግዙ።
👉 https://09u34jhg43098.typeform.com/to/nToapX9c

(የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል)
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#CARD: ይህን የ4 ደቂቃ መረጃ ዳሰሳ ጥናት በመሙላት የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመግታት የምንሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ መመርያ ያግዙ።
👉 https://09u34jhg43098.typeform.com/to/nToapX9c

(የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል)
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#CARD: ይህን የ4 ደቂቃ መረጃ ዳሰሳ ጥናት በመሙላት የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመግታት የምንሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ መመርያ ያግዙ።
👉 https://09u34jhg43098.typeform.com/to/nToapX9c

(የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል)