አጫጭር መረጃዎች ፦
- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 55 ሰዎች በኮቪድ-19 ተይዘዋል፤ ከነዚህ መካከል 18 ሰዎች ከለገጣፎ፣ 14 ሰዎች ከምስራቅ ሸዋ ይገኙበታል።
- በትግራይ ባለፉት 24 ሰዓት 37 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፤ 18ቱ የውጭ ጉዞ ታሪክ ያላቸው፣ 12 ሰዎች ንክኪ ያላቸውና 7 ሰዎች የውጭ የጉዞ ታሪክና ንክኪ የሌላቸው ናቸው።
- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 115 ምርመራ ተደርጎ 2 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
- በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1 ሰው በቫይረሱ ተይዟል ፤ አጠቃላይ በክልሉ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 292 ደርሰዋል።
- በደቡብ ክልል ከተደረገው 578 የላብራቶሪ ምርመራ 24 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጣል ፤ ከነዚህ መካከል 13 ሰዎች ከወላይታ ዞን ናቸው።
- በሱማሌ ክልል ከተደረገው 42 የላብራቶሪ ምርመራ 19 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል ፤ 10 ከጅግጅጋ እንዲሁም 9 ከጎዴ ናቸው።
- በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ሃያ (20) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ ከነዚህ መካከል 9 ሰዎች ከኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ናቸው።
#CARD #TIKVAH
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia