TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#HappeningNow ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር መላ፤ ቴሌብር እንደኪሴ እንዲሁም ቴሌብር ቁጠባ የተሰኙ የፋይናንሻል አገልግሎቶችን ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል። ቴሌ ብር መላ፦ የቴሌብር ደንበኞቹን ባንቀሳቀሱት የገንዘብ ዝውውር መሰረት ታይቶ እስከ በቀን እስከ 2,000 በወር ደግሞ እስከ 10,000 ብር የሚደርስ ብድር የሚያመቻች አገልግሎት ነው። ቴሌ ብር እንደኪሴ ፦ በቴሌብር አማካኝነት…
#ዝርዝር_ማብራሪያ

ኢትዮ ቴሌኮም ፦

• ቴሌብር መላ ፤
• ቴሌብር እንደኪሴ
• ቴሌብር ሳንዱቅ የተሰኙ የፋይናንሻል አገልግሎቶችን አስተዋውቋል።

ይህንን በሚመለከት ዝርዝር መረጃ አጠናቅረናል።

- " ቴሌብር መላ " አነስተኛ የብድር አገልግሎት ሲሆን ግለሰቦች እንዲሁም ነጋዴዎች እና ወኪሎች ያለየብድር ማስያዥያ ( Collateral ) ገንዘብ መበደር ያስችላቸዋል።

ምን ያህል መበደር እችላለሁ የአገልግሎት ክፍያውስ?

- " ቴሌብር እንደኪሴ " የክሬዲት ክፍያ/ኦቨርድራፍት ብድር አገልግሎት ሲሆን ገንዘብ በጎደሎት ጊዜ ሞልቶ ይከፍላል።

እንዴት መጠቀም እችላለሁ?

- " ቴሌብር ሳንዱቅ " የቁጠባ አገልግሎትን የሚሰጥ ሲሆን ከአንስተኛ ብር ጀምረው መቆጠብ ይችላሉ።

ወለዱ እንዴት ይሰላል ?

ያንብቡ : https://telegra.ph/telebirr-08-05
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA አምባሳደር ማይክ ሐመር ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ወደ ኬንያ ፣ ደቡብ አፍሪካ እና #ኢትዮጵያ ጉዞ ያደርጋሉ። የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ከጥቅምት 3 እስከ ጥቅምት 18 ቀን 2022 ወደ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ እንዘሚጓዙ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ዛሬ አሳውቋል። ሐመር ወደ ቀጠናው የሚመለሱት በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአፋጣኝ እንዲቆምና…
#USA #KENYA

ትላንት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በስልክ ከጎረቤታችን ኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር በተለያዩ የሁለትዮሽ ጉዳዮቻቸውና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን " ሲትዝን ቲቪ ኬንያ " ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ ፤ ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ሲሆን የተወያዩባቸው #ዝርዝር_ጉዳዮች በይፋ አልተገለፀም።

አሜሪካ ከሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ጋር በተያያዘ በአፋጣኝ ግጭት እንዲቆምና በአፍሪካ ህብረት የሚመራ የሰላም ድርድር እንዲጀመር ለመደገፍ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋን አምባሳደር ማይክ ሀመርን ወደ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ እና ኢትዮጵያ (ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 18 /2022 ድረስ) ልካለች።

https://www.citizen.digital/news/president-ruto-blinken-discuss-fertilizer-crisis-ethiopia-and-russia-ukraine-conflict-n306753

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ዶ/ር ጫላ ዋታ ያለመከሰስ መብታቸው ተነሳ። የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት የነበሩት ዶ/ር ጫላ ዋታ የመንግስት ግዥ ህግ ከሚፈቅደው አሰራር ውጭ በሰሩት ስራ ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቷል። ምክር ቤቱ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ነው ያለመከሰስ መብታቸው የማንሳት ውሳኔን ያፀደቀው። አንድ ድምፀ ተአቅቦ ያደረጉት እራሳቸው ዶ/ር ጫላ ዋታ ናቸው። (ዝርዝር ይኖረናል) …
#ዝርዝር

የቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት የነበሩት ዶ/ር ጫላ ዋታ  ዛሬ ያለመከሰስ መብታቸው ተገፏል።

የምክር ቤቱ የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስለ ዶ/ር ጫላ ዋታ ምን አለ ?

#የመንግስት_ግዥ_ህግ ከሚፈቅደው አሰራር ውጭ በመሄድ የውስጥ ገቢ ማስገኛ በሚል " ቢኤችዩ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነሪንግ ጄነራል ሌቭል 1 ፒኤልሲ " የተባለ አማካሪ ድርጅት በማቋቋም በስማቸው ንግድ ፍቃድ በማውጣት ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ጋር የተለያዩ የግንባታ ስራዎችን የማማከር አገልግሎት ለመስጠት በቀጥታ ግዥ በመፈፀም መዋዋሉን ፣ ለአማካሪ ድርጅቱና ለአማካሪ ድርጅቱ ላፀደቃቸው ተቋራጮች ክፍያ በመፈፀም በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል በሚል ጥቆማ ደርሶ ዝርዝር ምርመራ ተደርጓል።

በዚህም በተደረገ የወንጀል ማጣራት ፦

- 195 ሚሊዮን 52 ሺህ 812 ብር ከ81 ሳንቲም የሚያወጡ የተገለያዩ የግንባታ ስራዎች ለዘጠኝ ተቋራጮች ከመንግስት የግዥ አዋጆች እና አፈፃፀም መመሪያ ውጭ በቀጥታ እንዲፈፀም አድርገዋል።

- ዩኒቨርሲቲው ለመሰረተ ልማት ግንባታ የተፈቀደለትን የካፒታል በጀት አላግባብ በመጠቀም የግዥ ህግ እና ደንብ ባልተከተለ መልኩ ዋጋቸው 116 ሚሊዮን ብር የሆኑ 14 ተሽከርካሪዎች እና ማሽነሪዎች በግል ተቋራጭ ድርጅት ስም ግዥ ተፈፅሟል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎቹ እና ማሽነሪዎቹ በዩኒቨርሲቲው ገንዘብ የተገዙ ቢሆንም በግል ተቋራጮች ድርጅቶች  ስም እንዲሆኑ ተደርጋል።

ተሽከርካሪዎቹ እንዲሁም ማሽነሪዎቹ  የተገዙበት ዋጋ እጅግ የተጋነነ ሲሆን ለምሳሌ አንድ ደብል ጋቢና ፒካፕ ለተሽከርካሪ ተቋራጭ ድርጅቱ ከአስመጪ በብር 3 ሚሊዮን 300 ሺህ ግዥ የተፈፀመ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው በብር 6 ሚሊዮን 173 ሺህ 396 ብር ከ83 ሳንቲም እንደተገዛ ተቆጥሮ ክፍያ በመፈፀም ብር 2 ሚሊዮን 873 ሺህ 396 ብር እላፊ ተከፍሏል።

አንድ ሌላ ተሽከርካሪ ግዥ የተፈፀመው በብር 6.1 ሚሊዮን ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው በብር 6 ሚሊዮን 415 ሺህ 687 ብር ከ05 ሳንቲም በመግዛት ክፍያ የተፈፀመ በመሆኑ 315 ሺህ 687 ብር ከ05 ሳንቲም እላፊ እንዲከፈል ተደርጓል።

አጠቃላይ የ14ቱ ተሽከርካሪዎች እና ማሽነሪዎች ባለቤት የዩኒቨርሲቲው ሳይሆን የስራ ተቋራጭ ድርጅቶቹ እንዲሆኑ በማድረግ የተሰጣቸውን የመንግስት ኃላፊነትን ወደ ጎን በመተው ለራሳቸው የማይገባ ጥቅም በማግኘት እንዲሁም አማካሪ ድርጅት በሌለበት የተቋሙ የግንባታ ፅህፈት ቤት በፀደቁ የክፍያ የምስክር ወረቀት 11 ሚሊዮን 532 ሺህ 83 ብር ከ53 ሳንቲም ለተቋራጮች ክፍያ እንዲፈፀም በማድረግ የመንግሥት ሃብት እና ንብረት እንዲባክን አድርገዋል።

- በዶ/ር ጫላ እና ቢኤችዩ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነሪንግ ጄነራል ሌቭል 1 ፒኤልሲ በተባለው ድርጅት ላይ በተካሄደው የሃብት ምርመራ ስራ በተገኘው ውጤት ድርጅቱን የሚያንቀሳቅሱት ስራ አስኪያጅ እና የቦርድ ዳይሬክተር ዶ/ር ጫላ ዋታ መሆናቸው በዚህም ድርጅቱ ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ጋር በገባው ውል መሰረት በድምሩ 23 ሚሊዮን 135 ሺህ 433 ብር ከ27 ሳንቲም ያለአግባብ ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ የባንክ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ ወደ ድርጅቱ ሂሳብ ቁጥር ገቢ መደረጉና ከዚህ በመቀጠል ከድርጅቱ ቢኤችዩ ኃ/የተ/የግል ማህበር የባንክ ሂሳን ተቀንሶ በ6 የተለያዩ ጊዜያት በድምሩ 2 ሚሊዮን 116 ሺህ 16 ብር ከ65 ሳንቲም ወደ ዶ/ር ጫላ ዋታ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተ የሂሳብ አካውንት ገቢ ተደርጓል።

- በዶ/ር ጫላ ዋታ ባለቤት ስም ወ/ሮ ፀሃይ ኃይሉ ተፈራ ስም 72 ካሬ ላይ ያረፈ በብር 10 ሚሊዮን የተገዛ ባለ 3 ወለል ህንፃ የተገኘ መሆኑና ህንፃው የተገዛበት ገንዘብ በተመለከተ የተደረገው የፋይናንስ ምርመራ ክፍያው የተፈፀመው " ቢዳሩ ኮንስትራክሽን " ከተባለ ድርጅት ብር 4 ሚሊዮን እንዲሁም ደግሞ አቶ ተስፋሁን ሌንጄቦ ሌካ ብር 3 ሚሊዮን 500 ሺህ በተጨማሪ በዚህ ተመሳሳይ ቀን ቦኩይ ኢታንሳ የተባሉ ብር 2 ሚሊዮን 500 ሺህ በዶ/ር ጫላ ዋታ ባለቤት ወ/ሮ ፃሃይ ኃይሉ ስም ወደ ተከፈተ የሂሳብ ቁጥር ገቢ ተደርጎ ይኸው ገንዘብ በቀጥታ ለህንፃው ግዥ መዋሉ ታውቋል።

ገንዘቡ ለባለቤታቸው ለወ/ሮ ፀሃይ ኃይሉ ተፈራ ገቢ አድራጊዎች ማንነት ለማጣራት በተደረገው ምርመራ መሰረት በ " ቢዳሩ ኮንስትራክሽን " በቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ገንዘብ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 አአ 05069 የሆነ በብር 7 ሚሊዮን 785 ሺህ 157 ከ30 ሳንቲም የተገዛለት መሆኑና ተስፋሁን ሌንጄቦ የተባለው ደግሞ ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ለሚያሰራቸው ግንባታ መሰረተ ልማት እና ኢንፍራስትራክቸር ዝርጋታ ስራ በቀጥታ በደብዳቤ ትዕዛዝ 55 ሚሊዮን 133 ሺህ 893 ብር ስራ የተሠጠው ነው።

- በዶክተር ጫላ ዋታ ስማቸው የተመዘገበ አ/አ በን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ አንድ ሙሉ ክፍያው የተፈፀመ ኮንዶሚኒየም ቤት በልጃቸው ስም 200 ሺህ ብር በራሳቸው ስም የተገዛ የ1 ሚሊዮን ብር ሼር የተገኘ መሆኑ ተረጋግጧል።

ዶ/ር ጫላ ዋታ ምን አሉ ? ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-04-04
አቶ ግርማ የሺጥላ ተገደሉ።

የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ዛሬ በሰሜን ሸዋ " መሀል ሜዳ " ላይ በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል።

የአቶ ግርማን ግድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት የወንድማችንን የግርማ የሺጥላን ነፍስ ነጥቀዋል። " ብለዋል።

ዶ/ር ዐቢይ የግድያውን ሁኔታ በተመለከተ #ዝርዝር_መረጃ ባይሰጡም " ልዩነትን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ባህል በሆነበት ክፍለ ዘመን፣ በሐሳብ የተለየንን ሁሉ በጠመንጃ ለማሳመን መነሣት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው " ሲሉ ገልጸውታል።

" ተወልዶ ባደገበት አካባቢ ፣ ከእኛ የተለየ ሐሳብ ማሰብ አልነበረበትም ብለው የሚያምኑ ነውጠኛ ጽንፈኞች የፈጸሙት አስነዋሪና አሰቃቂ ተግባር፣ ጽንፈኝነትን በጊዜ ታግለን ካላስወገድነው ወደ መጨራረስ እንደሚወስደን ጉልሕ ማሳያ ነው። " ሲሉ አክለዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
#Update

የተሻሻለው የ " ንግድ ሕግ ማስፈጸሚያ መመርያ " ሊወጣ ነው !

ከስልሣ ዓመታት በኋላ ተሻሽሎ የወጣውን አዲሱን የንግድ ሕግ ማስፈጸሚያ መመርያዎች ውስጥ እና የመጀመርያው የሆነው በዚህ ዓመት ፀድቆ ሥራ ላይ እንደሚውል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የንግድ ሕጉ ማስፈጸሚያ ይሆናል የተባለው ይህ የመጀመርያው መመርያ የ " አክሲዮን ማኅበራት " ን የሚመለከት ነው፡፡

በዚሁ መሠረት ፤ " የአክሲዮን ማኅበራት ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር መመሪያ " በሚል የተዘጋጀው ረቂቅ መመርያ ተዘጋጅቶ በመጠናቀቁ በዚህ በጀት ዓመት ይፀድጋል ተብሎ ይጠበቃል።

መመርያው ምን ይዟል ?

- በንግድ ሕጉ ላይ " የመተዳደሪያ ደንብ ያስፈልጋል ? አያስፈልግም ? " የሚለውን ጉዳይ ለማብራራትና በቀላሉ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎችና በሁሉም ፈጻሚ ተቋማት ወጥ በሆነ መንገድ እየተተረጎመ እንዲፈጸም ለማስቻል በሚረዳ መልኩ በመመርያው እንዲቀመጥ ተደርጓል፡፡

- መመርያው አክሲዮን ማኅበራት ሲደራጁ ገንዘብ ከሕዝብ የሚሰበሰብበት መንገድ ላይ ምን መሆን እንዳለበት በግልፅ ያመላክታል። ኅብረተሰቡ እንዳይበዘበዝ እንዴት መተዳደር እንዳለበት በዝርዝር የተቀመጡ አንቀጾችን አካቷል፡፡

አደራጆች የምሥረታ ሒደት ለማካሄድ የሚያስከፍሉት አስተዳደራዊ ወጪ የሚዋጣው ገንዘብ ከአምስት በመቶ መብለጥ እንደሌለት በረቂቅ መመርያው ተመላክቷል፡፡

በምሥረታ ሒደት ከፈራሚዎች አስተዳደራዊ ወጪን ለመሸፈን ገንዘብ የተሰበሰበ እንደሆነ፣ ማኅበሩ ሲመሠረት የምሥረታ ወጪን ለማኅበሩ ማስተላለፍ የሚቻለው የተሰበሰበው አስተዳደራዊ ክፍያ የምሥረታ ወጪውን ለመሸፈን ያልበቃ መሆኑን የምሥረታ ኦዲተር ካረጋገጠ ብቻ ነው።

በምሥረታ ኦዲተር ሪፖርት መሠረት ለአስተዳደራዊ ወጪ ከተሰበሰበው ገንዘብ ላይ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቀሪ ገንዘብ ያለ እንደሆነ ማኅበሩ ሲመሠረት ፣ ለማኅበሩ ገቢ መደረግ ይኖርበታል። ይህም ቀድሞ ለአገልግሎት ተብሎ የተሰበሰበን ገንዘብ ከብክነት ያድናል።

- አደራጆች በአክሲዮን ምሥረታ ወቅት ከፈራሚዎች ሚሰበሰበውን መዋጮ በባንክ በዝግ ሒሳብ ሲያስቀምጡ በገበያው ላይ ካለው የወለድ ምጣኔ አንፃር ተመጣጣኝ የሆነ ወለድ እንዲያፈራ የማድረግ ኃላፊነት አለባቸው።

- የማኅበሩ ምሥረታ በስኬት የተጠናቀቀ እንደሆነ ዋና ገንዘቡና ያስገኘው ወለድ ለማኅበሩ ገቢ መደረግ አለበት።

- የግል አክሲዮን ማኅበር ሚመሠረተው በመሥራቾች እንደሚሆን ይደነግጋል። መሥራቾች በባለአክሲዮንነት ከሚያገኙት መብት ውጪ በመሥራችነታቸው ምክንያት የሚከፈላቸው የአገልግሎት ክፍያ አይኖርም።

- በአክሲዮኖች ላይ #ከአንድ_መቶ_ብር (100) ያነሰ ዋጋ የተጻፈባቸው አክሲዮኖች ያላቸው ማኅበራት፣ ይህ መመርያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሁለት ዓመት ውስጥ ቢያንስ ወደ አንድ መቶ ብር በማሳደግ መመሥረቻ ጽሑፋቸውን አሻሽለው ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።

- የአክሲዮን ኩባንያዎች የሚያደራጁ ሰዎች ያለባቸው ኃላፊነት ምንድነው የሚለውም በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን በአዲሱ የንግድ ሕግ የአክሲዮን ኩባንያዎች የኤሌክትሮኒክስ ስብሰባ ማድረግ የሚችሉ በመሆኑ፣ ይህንን ለማስፈጸም ዝርዝር ጉዳዩ በዚህ መመርያ ተገልጿል።

" የቦርድ ስብሰባ " የሚደረግበት የኤሌትሮኒክ ዘዴ የተሰብሳቢዎችን ማንነት ለመለየት የሚያስችል ፤ የውይይቱን የድምጽ ቅጂ በትክክል መያዝ የሚችል መተግበሪያ ያለውና ፤ ሚስጢራዊነትንም መጠበቅ የሚችል መሆን አለበት።

በመመስረቻ ጽሑፍ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር እያንዳንዱ የቦርድ አባል በዳይሬክተሮች ቦርድ ስብሰባ ላይ በአካል የመገኘት መብት ያለው ሲሆን፣ የቦርድ ስብሰባን በኤሌትሮኒክ ዘዴ ለመሳተፍ ዳይሬክተሩ ጥያቄ ካላቀረበ በቀር፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊያስገድድ ወይም በአካል የመሳተፍ መብቱን ሊገድብ እንደማይችች ተቀምጧል፡፡

- ከመመርያው መውጣት በኋላ ብዙ አክሲዮን ያላቸው ኩባንያዎች በቀላሉ ስብሰባቸውን እንዲያካሂዱ ዕድል ይሰጣቸዋል።

- የአክሲዮን ዝውውሮችን በተመለከተ በዚህ መመርያ ግልጽ ድንጋጌ ያስቀመጠ ሲሆን፣ በተለይ የግለሰብ አክሲዮንን ለማስተላለፍ #የትዳር_አጋር_ስምምነት ቅድመ ሁኔታ መሆኑን ያስቀምጣል፡፡

"በግል የአክሲዮን ማኅበር" ውስጥ በግለሰብ የተያዘ አክሲዮንን ፦
- በሽያጭ ፣
- በስጦታ ፣
- በመያዣ
- በሌላ በማንኛውም መንግድ ለማስተላለፍ በሕግ ወይም ደግሞ በመመሥረቻ ጽሑፍ ከተገለጹት ቅድመ ሁኔታዎች በተጨማሪ አስተላላፊው በአስገዳጅነት ያገባ ከሆነ የትዳር አጋሩ ውል ለማዋዋል እና ሰነድን ለመመዝገብ ' ሥልጣን ባለው አካል ፊት ቀርቦ ' ስምምነቱን መግለጽ አለበት።

ያላገባ ከሆነ / ከሆነች አግባብ ካለው የአስተዳደር መሥሪያ ቤት ተገቢውን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል በሚል መመርያው ይደነግጋል፡፡

- ሁሉም የአክሲዮን ማኅበራት ይህ መመርያ ተፈጻሚ ከሆነበት ቀን ጀምሮ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ድረገጽ ማበልጸግና በድረገጹ ላይ በሕጉ መሠረት ተገቢነት ያላቸውን መረጃዎች ማስቀመጥ አለባቸው። ይህንን ድንጋጌ የማይፈጽም የአክሲዮን ማኅበር የንግድ ፈቃዱ ሊታገድ እንደሚችልም ተደንግጓል፡፡

- አክሲዮን ለመሸጥ ስለሚወጡ #ማስታወቂያዎች በመመርያው ላይ ተቀምጧል።

ይህም ፤ " በማንኛውም በሕዝብ ማኅበር በምሥረታ ሒደት አክሲዮን ለመሸጥ በሚተላለፍ ማስታወቂያ ስለ ታሳበው የንግድ ሥራ አዋጭነት በጠቅላላው ከመግለጽ በስተቀር ስለሚያስገኘው የትርፍ መጠን በምን ያህል ጊዜ ለኢንቨስትምንት የተከፈለው ገንዘብ እንደሚመለስ ወይም ሌሎች በተጨባጭ ሊረጋገጡ የማይችሉ መረጃዎችን መስጠት አይቻልም " በሚል ተጠቅሷል፡፡

በማንኛውም #ዋና_ገንዘብ በማሳደግ ሒደት በግል ማኅበር ወይም በሕዝብ ማኅበር፣ ለሕዝብ አክሲዮን ለመሸጥ የሚደረግ ማስታወቂያ ማኅበሩ አስቀድሞ ያገኘውን ትርፍ የሚገልጽ ከሆነ፣ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ ዓመታት የትርፍ ውጤት መግለጽ ግዴታ አለበት፡፡

ነገር ግን ማኅበሩ #ለወደፊት የሚኖረውን አትራፊነት በቁጥር ወይ በመጠን መግለጽ አይቻልም።

ሚኒስቴሩ (ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር) ወይም አግባብ ያለው ሌላ የመንግሥት መሥሪያ ቤት አሳሳች ናቸው ብሎ ከወሰነ፣ አክሲዮን ለመሸጥ ለሕዝብ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎች እንዲቋረጡ ለማዘዝ ይችላል።

.
.
.

መመርያው በአጠቃላይ ከአክሲዮን ምሥረታ ጀምሮ እስከሚፈርስበት ጊዜ ድረስ #ዝርዝር የአሠራር ጉዳዮችን በመተንተን የቀረበ ነው።

በአዲሱ የንግድ ሕግ መመርያ የማውጣት ሥልጣን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነው፡፡

መመርያን ያዘጋጀው በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን በተለይ #የሕዝብን_ገንዘብ ተቀብለው የሚያስተዳድሩ የአክሲዮን ማኅበራት ላይ መጠነኛና ቁጥጥር ለመዘርጋት የሚያስችል ነው፡፡

(ሪፖርተር ጋዜጣ የረቂቅ መመርያው ዝግጅት ተሳታፊ የሕግ ባለሙያ አቶ ፈቃዱ ጴጥሮስን ዋቢ በማድረግ ያወጣው)

@tikvahethiopia
በሻኪሶ ከተማ ሞቶ በሦስተኛው ቀን አስክሬኑ የተገኘው ወጣት ጉዳይ !

#ዋና_ነጥብ

- በሻኪሶ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ተወዳጅ ታምራት (ጆኒ) ከሞተ በሦስተኛው ቀን አስክሬኑ ተገኝቷል።

- በሟች ግድያ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት ጓደኞቹ ፍርድ ቤት የዋስ መብት ፈቅዶላቸዋል።

- ወደ ስምንት የሚሆኑ የሟች ቤተሰቦች " ሁከት ፈጥራችኋል " ተብለው ከታሰሩ 10 ቀን ሞልቷቸዋል። ፍርድ ቤት ግን አልቀረቡም።

#ዝርዝር_ጉዳይ

በጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የባጃጅ ሹፌር የሆነው ወጣት ተወዳጅ ታምራት (ጆኒ) ሚያዚያ 29 በአንድ ሰርግ ላይ ተገኝቶ ምሽት ላይ ከታየ በኋላ ሊገኝ አልቻለም።

ጓደኞቹ ጋር ይሆናል ተብሎ ቢታሰብም በ2ኛው ቀን ግን ከጓደኞቹ " ጆኒን አይታችሁታል " የሚል ጥያቄ ለወንድሞቹ ቀረበ።

በዚህ ጊዜ ታናሽ ወንድሙ ወደሚያድርበት ቤት ሄዶ የጆኒ ክፍል የተባለውን ቤት ከአንድ ጓደኛው ጋር ሰብሮ ይገባሉ። ጠፋ የተባለው ወንድሙም በአልጋው ላይ ህይወቱ አልፎ ያገኘዋል። በወቅቱ ፖሊስ ደርሶ አስክሬኑን ለምርመራ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይልካል።

ፖሊስ ለሆስፒታሉ በጻፈው ደብዳቤ ሟች በሰው እጅ በመደብደቡ ከሞተ በኋላ ቤት ውስጥ በማስገባት ከተደበቀ በጥቆማ አስክሬኑ ተገኝቷል ሲል ድብደባ መፈጸሙን ይገልጻል።

የዓይን እማኞችም አስክሬኑ ላይ የምት እንዲሁም በቤቱ የደም ምልክት መመልከታቸውን ጉዳዩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ቤተሰባችን ጠቁመዋል።

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ለፖሊስ በጻፈው የውጤት ሪፖርት አስክሬኑ ለምርመራ የቀረበው በከፍተኛ ደረጃ በመስበስ ላይ እንዳለ መሆኑን ይጠቅሳል። በአስክሬኑ ላይ ተለይቶ የሚታይ ጉዳት የለም ያለው ሪፖርቱ " የደረሰ ውስጣዊ ጉዳትም የለም " ሲልም አካቷል።

አክሎም የልብ የደም መጋቢ ቧንቧ ወደ ወስጣዊ የልብ ክፍል ሰርገው መግባታቸው የሞት መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ጠቁሞ፤  " ከአስክሬን የምርመራ ውጤት በመነሳት የሞቱን መንስኤ መወሰን አልቻልንም፤ ስለሆነም መርማሪ ፖሊስ አደጋ የተከሰተበት የምርመራ ውጤት ከሁኔታው ጋር ተያያዥነት ያላቸው ማስረጃዎችን እና ሌሎች ደጋፊ ማስረጃዎችን በመጠቀም ድምዳሜ ላይ እንዲደርስ ምክራዊ ሀሳባችንን እንገልጸለን " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

በግድያ ወንጀል የተጠረጠሩት ሁለት ጓደኞቹ እና የአንደኛው ተጠርጣሪ ልጅ እናት እና አባት በጊዜው በቁጥጥር ሥር ቢውሉም የዋስ መብታቸው በፍርድ ቤት መፈቀዱን የሰሙት የሟች ቤተሰብ " ይህ እንዴት ይሆናል " ብለው ለመጠየቅ በሄዱበት ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ሁኔታውን ካስረዱን ቤተሰባችን እንዲሁም ከተላኩልን የምስል ማስረጃዎች መመልከት ችለናል።

የሟች ወላጅ እናት እና አባት፤ 2 ታላላቅ ወንድሞቹ እንዲሁም የሟች አጎት ጨምሮ ወደ 8 ሰዎች " ሁከት በመፍጠር እና እስረኛ ለማስመለጥ " ተጠርጥራችኋል ተብለው ከታሰሩ ዛሬ 10ኛ ቀናቸው መሆኑን ሰምተናል። የሟች ቤተሰቦች እስካሁን ድረስ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡም ሰምተናል።

በሟች ግድያ የተጠረጠሩት ጓደኞቹና የአንደኛው ተጠርጣሪ ልጅ እናት እና አባት በእስር ላይ ይገኛሉ።

ጉዳዩን በሚመለከት ከአከባቢው ፖሊስ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

በጉዳዩ ላይ ፖሊስ የሚሰጠው ማብራሪያ ካለ የምናቀርብ ይሆናል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba “ በእኛ የህግ አማካሪ በኩል ጥፋት ነበረ ” - ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የሚገኘው፣ 90 ዓመት ያስቆጠረ፣  በታሪካዊ ቅርስነት መመዝገብ አለበት በሚል በፍርድ ቤት በኩል ጉዳዩ ተይዞ ነበር የተባለለት ሎሞባርዲያ ሬስቶራንት ሳይፈርስ እንዲቆይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም ሰሞኑን በግብረ ኃይሎች እንዲፈርስ መደረጉ…
#ዝርዝር

" ሕንጻው የፈረሰው በቅርስነት መመዘኛ መስፈርቶች መሠረት ከ100 ቢያንስ 50ና ከዚያ በላይ ውጤት ባለማምጣቱ  ነው " - ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው

የቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፤ ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌውን ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ሎምባርዲያ ይገኝበት የነበረው ሕንጻ የፈረሰው በቅርስነት መመዘኛ መስፈርቶች መሠረት ከ100 ቢያንስ 50ና ከዚያ በላይ ውጤት ባለማምጣቱ ነው ብለዋል።

ሕንፃው ከ100/38 ነጥብ ያገኘ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦

- የዚህ ነጥብ መመዘኛ መስፈርቶች ምን ምን ናቸው ?

- በእያንዳንዱ መመዘኛ የተሰጡት ውጤቶችስ ስንት ናቸው ? ሲል ጠይቋል።

ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ፦

* ሦስት ደረጃዎች ናቸው የሚኖሩት። ደረጃ ሀ፣ ደረጃ ለ እና ደረጃ ሐ። 

1ኛ) ደረጃ ሀ ማለት ከ100 እስከ 65 ያመጣ ነው። ከ100 እስከ 65 ውጤት ከመጣ ምንም አይነት አልትሬሽን አይደረግበትም። ለሙዚየም፣ ለባህል ማዕከል ሊደረግ ይችላል። ነገር ግን ውጫዊውንም ፣ ውስጣዊውንም ገጽታ መቀየር አይቻልም።

2ኛ) ደረጃ ለ ማለት ከ64 እስከ 50 ነው። ይሄ ደግሞ የሚይዘው ውስጥ ላይ Reinnovataion ሊሰራ ይችላል። ግን ቅርስ አይፈርስም የሚል ነው።

3ኛ) 49ና ከ49 በታች ደረጃ ሐ ነው። ይሄን ምዘና ያገኘ ደግሞ ቅርስ አይሆንም፣ መስፈርት አያሟላም የሚል ነው የሚይዘው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በእነዚህ ደረጃዎች መሠረት ሎሞባርዲያ ይገኝበት የነበረው ህንፃ የተሰጠው ነጥብ ከስንት ስንት እንደሆነ በዝርዝር ይግለጹ ? ብሎ ጠይቋል።

* “ስታይል 7 ነጥብ ነው የሚይዘው። 3 ነጥብ ነው ያገኘው። ኮንስትራክሽን ማተሪያልን ጨምሮ 6 ነጥብ ነው የሚይዘው። 2 ነጥብ ነው ያገኘው። ዕድሜ 5 ነጥብ ነው የሚይዘው። 3 ተሰጥቶታል።

* አርክቴክት 3 ነጥብ ነው የሚይዘው። ከ3 ዜሮ ነው ያገኘው። ኢንተርየር ከ3/1 (ከሦስት አንድ) ነው ያገኘው። ታሪኩ ሲወሰድ ኢርሌር ትሬደር ነው በሚል 10 ነጥብ ነው የሚይዘው። 7 አግኝቷል።

* ኢቨንት 10 ነጥብ ነው የሚይዘው። 3 ነው ያገኘው። ኮንቴክስት ከ10/3 (ከአሥር ሦስት) አግኝቷል። አካባቢውን ጨምሮ ኮንቲኒዩቲ የሚለው 0/3 (ዜሮ ከሦስት ነው) ያገኘው። Land mark ነው የሚለው፣ ከ4/1 (ከአራት አንድ) ነው ያገኘው። 

* Usabilityን በተመለከተ Comparability አለ፣ 5 ነጥብ ነው ያለው። ዜሮ ነው ያገኘው። አዳፕታቢሊቲ ከአምስት አንድ ነው ያገኘው። ቦታው ፐብሊክ ነው ወይ? በሚለው አይደለም። ከአራት አንድ ነው ያገኘው። 

* Service (አገልግሎት) የሚሰጥበት መኝታ ቤቶችና ሌሎች ናቸው። ታችም ሱቆች ናቸው። ከሦስት ዜሮ ነው ያገኘው። ቢቆይ፣ አዲስ ቢሰራ በሚል ሦስት ሦስት (3/3) ነጥብ ነው ያገኘው። ኢንተግሪቲ (ያለበት ሁኔታ) አልትሬሽን ብዙ አልተደረገም። ከአምስት ሦስት ነው። ያገኘው።

* “Condition, in good condition ነው አምስት ነው ያገኘው ከሰባት፤ እንደዚህ ሆኖ 38 ነጥብ ይመጣል በአጠቃላይ። በዚያ መሠረት ኢቫሉየት ከተደረገ በኋላ ነው የሰረዝነው።

ያንብቡ👇 https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-12

@tikvahethiopia