TIKVAH-ETHIOPIA
#USA አምባሳደር ማይክ ሐመር ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ወደ ኬንያ ፣ ደቡብ አፍሪካ እና #ኢትዮጵያ ጉዞ ያደርጋሉ። የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ከጥቅምት 3 እስከ ጥቅምት 18 ቀን 2022 ወደ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ እንዘሚጓዙ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ዛሬ አሳውቋል። ሐመር ወደ ቀጠናው የሚመለሱት በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአፋጣኝ እንዲቆምና…
#USA #KENYA

ትላንት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በስልክ ከጎረቤታችን ኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር በተለያዩ የሁለትዮሽ ጉዳዮቻቸውና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን " ሲትዝን ቲቪ ኬንያ " ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ ፤ ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ሲሆን የተወያዩባቸው #ዝርዝር_ጉዳዮች በይፋ አልተገለፀም።

አሜሪካ ከሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ጋር በተያያዘ በአፋጣኝ ግጭት እንዲቆምና በአፍሪካ ህብረት የሚመራ የሰላም ድርድር እንዲጀመር ለመደገፍ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋን አምባሳደር ማይክ ሀመርን ወደ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ እና ኢትዮጵያ (ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 18 /2022 ድረስ) ልካለች።

https://www.citizen.digital/news/president-ruto-blinken-discuss-fertilizer-crisis-ethiopia-and-russia-ukraine-conflict-n306753

@tikvahethiopia