TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የኤርትራ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ልዑክ በኢትዮጵያ የሚያደርገውን ጉብኝት ለመጀመር በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ የሚገባ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የጉብኝቱ አላማ የሀገራቱን ታሪካዊ ግንኙነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማጠናከር ነው ተብሏል። የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ልዑኩ በኢትዮጵያ በሚኖረው ቆያታ በተለያዩ ዝግጅትቶች ተሳታፊ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህም ልዑኩ የፊታችን የካቲት 9 ቀን ባህርዳር፣ የካቲት 10 በአዳማ፣ የካቲት 12 በሀዋሳ እና የካቲት 14 ደግሞ በአዲስ አበባ ከተሞች በሚካሄዱ ባህላዊ #የሙዚቃ_ኮንሰርቶች ተሳታፊ ይሆናል ተብሏል። ለዚህ ባህላዊ የሙዚቃ ኮንሰርትም #ሁሉም ኢትዮጵያዊና ኤርትራዊያን ተሳታፊ እንዲሆኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል። በሚቀጥለው ወርም የሁለቱ ሀገራትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ይበልጥ  ለማጠናከር የኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ልዑክ  ወደ ኤርትራ የሚያቀና መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሰበር_ዜና በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ በሚገኙ #ሁሉም ዞኖች፣ ከተማ አስተዳደሮች እና ልዩ ወረዳዎች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ #ታውጇል#ETHIOPIA

#State_of_emergency

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ካምቦዲያ ከኮቪድ-19 ታማሚዎች #ነፃ ሆነች!

በካምቦዲያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 122 ሰዎች መካከል #ሁሉም በተደረገላቸው ህክምና ከበሽታው ማገገማቸው ተገልጿል።

በትላንትናው ዕለት የመጨረሻዋ የኮሮና ቫይረስ ታማሚ (የ36 ዓመት ሴት) ከሆስፒታል ወጥታለች።

ካምቦዲያ ከሚያዚያ 4/2012 ዓ/ም በኃላ አዲስ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ኬዝ ሪፖርት አላደረገችም።

የሀገሪቱ መንግስት አሁንም የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል የጣላቸውን ገደቦች አላነሳም። ትምህርት ቤቶች አሁንም እንደተዘጉ ናቸው ፤ በድንበር አካባቢ የሚደረገው ቁጥጥር እንደተጠናከረ ነው፤ ኳረንታይንም ቀጥሏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#SouthSudan

የደቡብ ሱዳን የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ሚካኤል ማኩዪ ከጤና ሚኒስትሯ ውጭ #ሁሉም የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብረ ኃይል አባላት በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ለቢቢሲ #አረጋግጠዋል

በኮቪድ-19 የተያዙት ሁሉም ሚኒስትሮች በለይቶ ማቆያ የሚገኙ ሲሆን በሙሉ ጤንነትም ላይ ይገኛሉ ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ የባለስልጣናቱ ጠባቂዎች እንዲሁም ሠራተኞች በኮሮና ቫይረስ ተይዘው በለይቶ ማቆያ ውስጥም ይገኛሉ።

በሌላ በኩል የኢንፎርሜሽን ሚኒስትሩ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በኮቪድ-19 ተይዘዋል የሚለውን ሪፖርት #አጣጥለውታል

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#HAWASSA

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ዛሬ በሰጠው መግለጫ #ሁሉም አሽከርካሪዎች እና ተሳፋሪዎች ከመጪው ሰኞ ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የፊትና የአፍ መሸፈኛ ማስክ የማድረግ ግዴታ እንደሚኖርባቸው አሳውቋል።

ይህን መመሪያ በሚተላለፉ አሽከርካሪዎች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ መምሪያው በጥብቅ አስታውቋል፡፡

መመሪያው በመላው ሀገሪቱ #እየጨመረ የሚገኘውን ፤ እንዲሁም ወደ ከተማው የመግባት አዝማሚያ እያሳየ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል ይረዳል ተብሎ የተዘጋጀ ነው ተብሏል።

የባለ 2 እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎችን እንዲሁም የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች ረዳቶችና ተሳፋሪዎችን ፤ እንዲሁም የግልና የመንግስት መኪና አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎችን፤ ባጃጅና የመሳሰሉትን አነስተኛ የትራንስፖት ዘርፎች የሚያካትት ነው።

አሽከርካሪዎች ይህንን አውቀው በቀጣይ ሁለት (2) ቀናት ውስጥ ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የፊት ማስኮችን አድርገው መንቀሳቀስ እንደሚኖርባቸው ተገልጿል፡፡

#SRTA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ትምህርት ሚኒስቴር በጦርነት እና ግጭት ውስጥ ሆነው ተፈትነዋል ተብለው የተለዩ እና የ12ኛ ክፍል " የማለፊያ ውጤት ያላመጡ " ተማሪዎች በዚህ ዓመት በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እንደ መደበኛ ተማሪ ሆነው መፈተን እንደሚችሉ አስታወቀ፡፡ ከዩኒቨርስቲዎች ጋር ውይይት በማድረግ ተጨማሪ የቅበላ አቅም እንዲኖር ከስምምነት ላይ መደረሱን እና ተጨማሪ የቅበላ አቅም በፍትሀዊነት በጦርነቱ…
#ውሳኔ

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2013 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን አስመልክቶ ውሳኔ መተላለፉን አሳውቋል።

ከውሳኔዎቹ አንደኛው ከዚህ በፊት በተላለፈው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት ወደ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች መግባት ከቻሉት የክልሉ ተማሪዎች በተጨማሪ 4339 ተማሪዎች በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ቅበላ እንዲያገኙ ተወስኗል ብሏል።

እነዚህ 4339 ተማሪዎች እንዴት እና በምን አግባብ ቅበላ ሊያገኙ እንደቻሉ (የተበላሸ ውጤታቸው ተስተካክሎ ወይስ ሌላ ስለሚለው) ቢሮው ዝርዝር ማብራሪያ አልስጠም።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሌላ ተላልፏል ያለው ውስኔ ፥ በ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ወደ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመግቢያ ነጥብ ያላሟሉ የክልሉ #ሁሉም_ዞኖች ተማሪዎች በ2014 ዓ.ም በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በመደበኛ ተማሪነት (as regular students) መፈተን እንደሚችሉ ነው።

ቢሮው ፤ ትምህርት ሚኒስቴር የውጤት መቁረጫ ነጥብ ተወስኖ እና ያለፉት ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምርጫ ፎርም የሚሞላበት የመጨረሻው ቀን ከተወሰነ በኋላ ከአማራ ክልል በተነሳ ቅሬታ መነሻነት ቅሬታውን አዳምጦ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ጊዜው እንዲራዘም ማድረጉ ትልቅ መደማመጥ የተስተዋለበት ነበር ሲል ገልጿል።

" ይህም ለቀጣይ በመደማመጥ ላይ የተመሰረተ የሀገር ግንባታ ጉዟችን አንድ ማሳያ ነው ብለን እናስባለን " ሲል አክሏል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከተፈጠረው ችግር አኳያ ውሳኔው ያላረካቸው አካላት ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገመታል ያለ ሲሆን የክልሉ ተማሪዎች በመደበኛ ተማሪነት የመፈተን እድሉን በድጋሜ ማግኘታቸውን እንደ ትልቅ አጋጣሚ አድርገው ለውጤታማነት እንዲጠቀሙበት አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ሀገራዊ_ምክክር 🇪🇹

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰብሳቢ ፕ/ር መስፍን አርአያ ለኤፍ ቢ ሲ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦

" በሀገራዊ ምክክሩ #ሁሉም ኢትዮጵያዊ አጀንዳ የሚያስይዝበት አሰራር ይዘረጋል።

የውይይት ሃሳቦች ከታች ወደ ላይ ነው የሚሰበሰቡት።

በውይይቱ ይህ ይነሳ ያ አይነሳ የሚባል ነገር የለም ። ኮሚሽኑ በአጀንዳዎች ላይ ጣልቃ አይገባም።

ምክክሩ ልሂቁ ላይ ብቻ የተንጠለጠለ ባለመሆኑ ሁሉም ዜጋ ሐሳቡ በጥቂቶች እንዳይጨናገፍ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ እናቀርባለን።

በቀጣይ በየክልሉ እንደ አመቺነቱ ጽሕፈት ቤቶች ይቋቋማሉ ፤ የኮሚሽኑ ምክር ቤት መርሃ ግብር ያዘጋጀ ሲሆን ስትራቴጂክ ዕቅዱን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ግብዓት ይሰበሰባል።

አጀንዳ የመሰብሰብ ሥራ በገጽ ለገጽ ማህበረሰቡ በሚረዳው ቋንቋ ስለ ኮሚሽኑ በማስረዳት ሃሳቡን እንዲገልጽ ይደረጋል። በሌሎች አማራጮችም በስልክ፣ ኢሜይል እና ፖስታ በመሳሰሉት ማቅረብም ይቻላል።

ማሕበረሰቡ ሃሳቡን ከማቅረብ በተጨማሪ በማዕከል ደረጃ ለሚደረገው ምክክር ወኪሎቹን እንዲመርጥ ይደረጋል።

የአጀንዳ ሃሳቦች መሰብሰብ የሚጀመርበት ጊዜ #በቅርቡ_ይፋ ይደረጋል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA🇪🇹 #በኢትዮጵያ_መንግስት እና #በህወሓት መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ይዘት የሚገልፅ 12 ነጥብ ያለው #የጋራ_መግለጫ ከላይ ተያይዟል። ነገ ሁለት ዓመት የሚደፍነውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲበጅለትና ህዝቡም እረፍት እንዲያገኝ ፤ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ፣ አርሶ አደሮችም ወደ እርሻቸው ፣ ሰራተኞችም ወደ ስራቸው፣ ነጋዴዎችም ወደንግዳቸው እንዲመለሱ አጠቃላይ…
ስለ " ሰላም ስምምነቱ " ምን ተባለ ?

🕊 የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦

ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ኢትዮጵያ ለሰላም ያላት ቁርጠኝነት አሁንም የፀና መሆኑን ገልፀው " ስምምነቱ #ወደተግባር እንዲለወጥ አስፈላጊውን ትብብር ለማድረግ ጠንካራ አቋም / ቁርጠኝነት አለን " ብለዋል።

🕊 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (አንቶኒዮ ጉተሬዝ) ፦

በደቡብ አፍሪካ የተደረሰው የ " ሰላም ስምምነት " የበርካታ ኢትዮጵያውያንን ህይወት የቀጠፈውና ሁለት ዓመት ያስቆጠረውን አስከፊ ጦርነት ለማስቆም ወሳኝ የሆነ የመጀመሪያ እርምጃ ነው ብለዋል።

#ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ክልል አመራሮች ለሰላም የወሰዱትን እርምጃ እንዲደግፉ አሳስበዋል።

የጦርነት ማቆም የሚሰጠውን እድል በመጠቀም ለተቸገሩ ሰላማዊ ዜጎች ሁሉ ሰብአዊ እርዳታን ከፍ ለማድረግ እና በጣም አስፈላጊ የህዝብ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።

🕊 አሜሪካ ፦

ከአፍሪካ ኅብረት፣ ተመድ፣ ኢጋድ እና ከሌሎችም ጋር በመሆን የተደረሰው ስምምነት #ተግባራዊ እንዲሆን በሚደረገው ጥረት ውስጥ ድጋፏን እንደታደርግ ገልጻለች። የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር በሰሜን ኢትዮጵያ በጦርነቱ የደረሰውን ውድመት መልሶ ለመገንባት እና ለልማት ያላቸውን ፍላጎት እንደምትደረግፍም አሳውቃለች።

🕊 የአውሮፓ ህብረት (ጆሴፕ ቦሬል) ፦

የሰላም ስምምነቱ ባስቸኳይ ሊተገበር ይገባል ያሉ ሲሆን በግጭቱ ጉዳት ለደረሰባቸው አካባቢዎች ሰብዓዊ ዕርዳታ ማቅረብ ፤ በትግራይ ክልል የተቋረጡ መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንደገና መጀመር #ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/ETHIOPIA-11-03

@tikvahethiopia
#Update

" ማንኛውም የሰብዓዊ ድጋፍ አቅራቢ ተቋም በአየር እና በየብስ የሰብዓዊ እርዳታ ማቅረብ ይችላል " - የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን

ዛሬ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ፤ ወደ ትግራይ ክልል የሚወስዱ #ሁሉም ኮሪደሮች ለሰብአዊ ደጋፍ አቅርቦት ክፍት መደረጋቸውን አስታውቋል።

የሰብአዊ ድጋፍ ተቋማት በአየርና በየብስ የሰብዓዊ እርዳታ ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጿል።

ይህ የተገለፀው የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምሳደር ሽፈራው ተክለማርያም ለተለያዩ #ዓለም_አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅራቢ ድርጅቶች የሰሜን ኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታን በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።

አምባሳደር ሽፈራው ፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተደረገውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ሰብአዊ ድጋፍ ለሚያቀርቡ ተቋማት የየብስም ሆነ የአየር ትራንስፖርት ክፍት ተደርጓል ሲሉ ገልጸዋል።

በአፋር ክልል ከአብዓላ መቐለ ፣ በሁመራ በኩል ሽራሮ ፣ ሽሬ አክሱም አድዋ፤ በጎንደር አዲ አርቃይ ማይጸምሪ ሽሬ እንዲሁም የወልዲያ አላማጣ መስመሮች ሁሉም ለሰብዓዊ እርዳታ ክፍት እንደሆኑ ተናግረዋል።

በአፋር ክልል ከአብዓላ መቐለ መስመር የሙከራ አገልግሎት የሰጠ ሲሆን፤ በሁመራ በኩል ሽራሮ፣ ሽሬ አክሱም አድዋ በኩል ከገቡ 16 ከባድ መኪናዎች መካከል 3ቱ የሕክምና ቁሳቁስ ይዘው መግባታቸውን አመልክተዋል።

" ማንኛውም የሰብዓዊ ድጋፍ አቅራቢ ተቋም በአየር እና በየብስ የሰብዓዊ እርዳታ ማቅረብ ይችላል " ብለዋል ኮሚሽነሩ።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" አንዳንድ የተፈጠረውን ሰላማዊ ሁኔታ የማይቀበሉ አሉ "

የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፤ የተፈጠረውን ሰላማዊ ሁኔታ (ከህወሓት ጋር ማለታቸው ነው) የማይቀበሉ እንዳሉ በመጠቆም ፤ እነዚህ ሰላማዊ ሁኔታውን አይቀበሉም ያሏቸው አካላት " በዛም በዚህም " ያሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ትላንት ከናይሮቢ ሲመለሱ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ፤ " አንዳንድ የተፈጠረውን ይሄን ሰላማዊ ሁኔታ የማይቀበሉ አሉ። በዛም በዚህም አሉ፤ ይሄ ትግል ይፈልጋል፤ ሰላም አልፈልግም የሚል እና ሰላም የሚፈልግ ትግል ከገጠመ ሰላም የማይፈልግ ሰው አሸንፎ አያውቅም ብለን እናስባለን " ሲሉ ተደምጠዋል።

ኢታማዦር ሹሙ እነዚህ " በዛም በዚህም " አሉ ሲሉ የገለጿቸው ሰላም አይፈልጉም ያሏቸው አካላትን በግልፅ ከመናገር ተቆጥበዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ በኢትዮጵያ መንግስት / በመከላከያ በኩል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ለመፈፀም " በመሉ ልብ ዝግጁ ነን " ሲሉ አሳውቀዋል።

" ዝግጁ የሚያደርገን (ለስምምነቱ ተፈፃሚነት) ለኢትዮጵያ ህዝብ ብለን ነው። " ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ " የትግራይ ህዝብ ህዝባችን ነው። እዛ የደረሰውን ችግር፣ ውድመት አይተናል፣ ይበቃዋል፤ ከዚህ በላይ በእሱ ላይ መፍረድ ህሊናቢስነት ነው። ሀገራችንም ይበቃታል፤ ወደ ተጀመረው ልማት ፣ ብልፅግና ብትሸጋገር ይሻላል የሚል ሀሳብ ይዘን ነው በዚህ ድርድር የተደራደርነው የተፈራረምነው አፈፃፀሙንም የተግባባነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የመጣው የሰላም ዕድል ጥሩ ዕድል መሆኑን የገለፁት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፤ " የተቻለንን ያህል ተግባራዊ እንዲሆንና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ እና #ሁሉም ወደነበረበት ወደሰከነበት እንዲመለስ እንመኛለን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ዛሬ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ይዘጋሉ።

የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል መንገዶች የሚዘጉት ለ " ፀጥታ ስራ ሲባል " መሆኑን ገልጾ ለተሽከርካሪም ሆነ ለእግረኞች ዝግ እንደሚደረጉ ነው ያመለከተው።

የጋራ ግብረ ሃይሉ ከቀናት በኋላ በአ/አ በሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሚከናወነው #የአጀብ እና #የፀጥታ ስራዎች ምክንያት በማድረግ #ሁሉም_የፀጥታ_አካላት_የሚሳተፉበት ወታደራዊ የተግባር ልምምድ እንደሚከናወን አሳውቋል።

ለዚሁ ሲባል የሚከተሉት መንገዶች ለተሽከርካሪ እና ለእግረኞች ዝግ ይደረጋሉ ፦

🚘 ከጎተራ መሳለጫ ወይም ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ጎተራ መሳለጫ ጋር፤

🚖 ከቂርቆስ ታቦት ማደሪያ ወደ ለገሀር የሚወስደው ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ መስቀለኛ  ላይ ፤

🚘 ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ ለሚመጡ ቡልጋሪያ ማዞሪያ፤

🚖 ከሳር ቤት በአፍሪካ ህብረት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚመጡ ሳር ቤት አደባባይ፤

🚘 ከካርል አደባባይ በልደታ ፀበል ወደ ከፍተኛ ፍ/ቤት  ለሚመጡ ካርል አደባባይ፤

🚖 ከጦር ሃይሎች ወደ ሜክሲኮ አደባባይ አዋሽ ወይን ጠጅ ፋብሪካ፤

🚘 ከአብነት ወደ ጌጃ ሰፈር አብነት አደባባይ፤

🚖 ከሞላ ማሩ ወደ አብነት ፖሊስ ጣቢያ ለሚመጡ ሞላማሩ መስቀለኛ ፤

🚘 ከበርበሬ በረንዳ ወደ ቀድሞ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ  ለሚመጡ በርበሬ በረንዳ፤

🚖 ከተ/ሃይማኖት ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ፤

🚘 ከቴዎድሮስ አደባባይ በቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ የሚሄደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ዝግ የተደረገ ሲሆን ከየትኛውም አቅጣጫ ወደ አራት ኪሎ መሄድ የተከለከለ ነው፡፡ 

🚖 ከሽሮ ሜዳ ወደ 6 ኪሎ እና ወደ 4ኪሎ የሚያስኬደው መንገድ  ሽሮ ሜዳ ጋር የሚዘጋ ሲሆን ከ4 ኪሎ ወደ ቤተ መንግስት የሚወስደው መንገድ ዝግ ተደርጓል፡፡ 

🚘 ከቀበና ወደ 4ኪሎ ቀበና አደባባይ ፤

🚖 ከጀርመን አደባባይ እና ከሲግናል አካባቢ ወደ 4 ኪሎ ጥይት ቤት ለሚመጡ ጀርመን አደባባይ ፤

🚘 ከካዛንቺስ መናህሪያ ወደ 4ኪሎ እና ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሴቶች አደባባይ፤

🚖 ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ ወሎ ሰፈር ፤

🚘 ከመገናኛ ወደ መስቀል አደበባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል መስቀለኛ ፤

🚖 ከቅዱስ መርቆሪዮስ አደባባይ ወደ መስቀል ፍላወር ቅዱስ መርቆሪዮስ አደባባይ፤

🚘 ከአፍንጮ በር ወደ 6 ኪሎ አፍንጮ በር፤

🚖 ከፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ወደ 6 ኪሎ የሚያመጣው 6 ኪሎ ዝግ ይሆናል፤

🚘 ከሚኒሊክ ሆስፒታል ወደ 6 ኪሎ የሚያመጣው መንገድ 6 ኪሎ ቶታል ጋር ዝግ የሚደረግ ሲሆን በተጨማሪም ወደ 4 ኪሎ እና በቅርበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚያመጡ አቋራጭ መንገዶች ዝግ የሚደረጉ ይሆናል ተብሏል።

በተጨማሪም #ለእግረኛ ተጠቃሚዎች፦

🚶መስቀል አደባባይ 4ተኛ ክፍለ ጦር ወይም ጥላሁን አደባባይ ዙርያ፣
🚶‍♂ኦሎምፒያ ዙርያ፣
🚶‍♂ከኡራኤል ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ ከቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከሀራምቤ ወደ መሰቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከለገሀር ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከባምቢስ ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከትምህርት ሚኒስቴር በአራት ኪሎ ብሔራዊ ቤተ መንግስትና ወደ ቦሌ እንዲሁም ከቀበና ወደ አራት ኪሎ የሚወስደው መንገድ ዝግ መሆኑ ተነግሯል።

ዝግ ሆኖ የሚቆየው ከለሊቱ 11፡ 00 እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ሲሆን ህብረተሰቡ #አማራጭ_መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ተላልፏል።

(የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቤት ማፍረስ ዘመቻው ... በአዲስ አበባ ዙርያ " ሸገር ከተማ " እየተካሄደ ያለውን የቤት ማፍረስ ዘመቻን በተመለከተ ኢሰመኮ የደረሰበትን የክትትል ውጤት በላከልን መግለጫ አሳውቋል። በመግለጫው፤ በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ እየተካሄደ ያለው ቤቶችን የማፍረስ እና በግዳጅ ማስነሳት እርምጃ የመኖሪያ ቤት አልባነትን አባብሷል ብሏል። ሕገ ወጥ የሆነ ግንባታን የማፍረስ እርምጃ ሕጋዊ ሂደትን መከተልና…
ከኢሰመኮ መግለጫ...

በሸገር ከተማ እየተካሄደ ካለው የቤት ማፍረስ እና በግዳጅ ማስነሳት ዘመቻ ጋር በተያያዘ ኢሰመኮ እርምጃው ተገቢ ልየታ ያልተደረገበት መሆኑን ገልጿል።

የቤት ፈረሳውና በግዳጅ ማንሳቱ የሚመለከተው የከተማውን መሪ ዕቅድ በሚጥሱ እና የመንግሥት ይዞታን በመውረርና ከአርሶ አደሩ ጋር በተደረገ ሕገወጥ የመሬት ግብይት የተገኙ ይዞታዎች ላይ የተደረጉ ግንባታዎችን ነው ቢባልም #ሁሉም ቤቶች ግን በተመሳሳይ ሥሪት ላይ የተመሠረቱ ባለመሆናቸው የሚገዛቸውም ሕጎች እና አሠራሮች በዚያው ልክ የተለያዩ ሊሆኑ ይገባ ነበር ብሏል።

ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትልና ምርመራ እየፈረሱ ያሉ ቤቶች በተለያየ አይነት ክፍል የሚመደቡ መሆኑን ገልጿል

👉 የመጀመሪያው ክፍል ፦

ከ2005 ዓ.ም. በፊት የተገነቡ ቤቶች ሲሆኑ እነዚህን ቤቶች በተመለከተ በሀገሪቱ የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 6(4) እና (5) እንደተደነገገው አዋጁ ከመውጣቱ በፊት በኢመደበኛ መልኩ የተገነቡ ቤቶች የከተሞችን ፕላን እና የሽንሻኖ ስታንዳርድ ሲያሟሉ ወደ መደበኛ ስሪት እንደሚዞሩ ደንግጓል። ነገር ግን ኮሚሽኑ ባደረገው ማጣራት እነዚህን ቤቶች ሕጉ በደነገገው መሠረት በወቅቱ ወደ መደበኛ ሥሪት እንዲዘዋወሩ የሚያስችላቸውን መስፈርቶች ማሟላታቸውን በማረጋገጥ የማዘዋወር ሥራ ሳይሠራ እንዲሁ #እንዲፈርሱ ተደርጓል።

👉 ሁለተኛው ክፍል ፦

በግዢ የተገኙ ቤቶች ሲሆኑ ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ መደበኛ ካርታ፣ የአየር ላይ ካርታ እና አረንጓዴ ደብተር ያላቸው እንዲሁም እንዳይፈርሱ የፍርድ ቤት እግድ ያለባቸው ቤቶች ከከተማ ፕላን ጋር የማይሄዱ ናቸው ከተባለ፤ በሕግ አግባብ በተደነገገው መሠረት ተለዋጭ የቤት መሥሪያ ቦታ እና ተገቢው ካሳ ተከፍሏቸው መነሳት የሚገባቸው ነበሩ። ቤቶቹ በገጠር መሬት ላይ የተሠሩ ናቸው የሚባል ቢሆን እንኳ በኦሮሚያ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 130/1999 አንቀጽ 6(8) መሠረት በቂ ጊዜ ተሰጥቶ ንብረቶቻቸውን እንዲያነሱ ይደረጋል እንጂ በድንገት ማፍረስ አይገባም ነበር።

👉 ሦስተኛው እና አራተኛው ክፍል ፦

ከአርሶ አደሮች ጋር በተደረገ ሕገ ወጥ የመሬት ሽያጭ በተገኘ ቦታ ላይ የተሠሩ ቤቶች እና ከ2005 ዓ.ም. በኋላ ያለሕጋዊ ፈቃድ በመንግሥት ይዞታዎች ላይ የተገነቡ ቤቶች ናቸው።

ስለሆነም እንዲፈርሱ የተደረጉት ቤቶች በተለያየ አይነት ሥሪት ላይ የተመሠረቱ ስለሆነ እንደየነገሩ ሁኔታ ተገቢው መለየት እና ማጣራት እየተደረገ ሊፈጸም ይገባው ነበር፡፡

ሕገወጥ ግንባታ ማፍረስና የመንግሥት ይዞታ የሆነን ቦታ መልሶ መውሰድ ሕጋዊ እርምጃ ቢሆንም እንኳን፣ የመኖሪያ ቤት ማፍረስና በግዳጅ ማስነሳት ዜጎችን መኖሪያ ቤት አልባ በሚያደርግ መልኩ መደረግ እንደሌለበት እና በሕግ የተፈቀደ እና ለቅቡል አላማ የተደረገ መሆኑ ብቻ በቂ ምክንያት ሊሆን እንደማይችል ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕግ ይደነግጋል።

ዜጎች የመኖሪያ ቤት መብት እንዳላቸው ኢትዮጵያ ያጻደቀችው ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ባህላዊ መብቶች ቃልኪዳን በአንቀጽ 11 የደነገገ ሲሆን ኢመደበኛ በሆነ መንገድ እንኳን የተገኙ የመኖሪያ ቤቶችን በሚመለከት መኖሪያ ቤት አልባነትን ለመከላከል ሲባል ሕጋዊ የይዞታ ዋስትና ሊሰጣቸው ወይም አማራጭ መፍትሔ ሊመቻች እንደሚገባ የኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊ እና ባህላዊ መብቶች ኮሚቴ በግዳጅ ማንሳትን በተመለከተ ባወጣው አጠቃላይ አስተያየት ቁጥር 7 ላይ አስቀምጧል፡፡

ሙሉ መግለጫ ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/77467?single

ፎቶ፦ Tikvah Family

@tikvahethiopia
A_HRC_54_55_AdvanceUneditedVersion.docx
79.2 KB
#ETHIOPIA #UN

ኢትዮጵያ ውስጥ ጦርነት እንዲቆም ስምምነት ከተፈረመ አንድ አመት ሊሞላው ቢቃረብም አሁንም ግፍ፣ የጦር ወንጀሎች እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እየተፈፀሙ ነው ሲል በተመድ ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ኤክስፐርቶች ኮሚሽን ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አሳወቀ።

ኮሚሽኑ የሰላሙ ሁኔታ አሁንም ያልተረጋገጠ መሆኑን ጠቁሟል።

ኮሚሽኑ ባወጣው ባለ 21 ገጽ ሪፖርቱ ከህዳር 3 ቀን 2020 ጀምሮ በግጭቱ ውስጥ በተሳተፉ #ሁሉም_አካላት የተፈፀሙ መጠነ ሰፊ አሰቃቂ ድርጊቶችን አስፍሯል።

ከእነዚህም ውስጥ ፦
- የጅምላ ግድያ፣
- አስገድዶ መድፈር፣
- ረሃብ፣
- የትምህርት ቤቶች እና የህክምና ተቋማት ውድመት፣
- የግዳጅ / በኃይል ማፈናቀል እና የዘፈቀደ እስራት ይገኙበታል።

የኮሚሽኑ ሊቀመንበር መሀመድ ቻንዴ ኦትማን ፤ " የሰላም ስምምነቱ መፈረሙ በአብዛኛው የመሳሪያ ድምፅ ጸጥ ያሰኘው ቢሆንም ፤ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በተለይም በትግራይ ያለውን ግጭት አልፈታም ወይም ምንም አይነት አጠቃላይ የተሟላ ሰላም አላመጣም " ብለዋል።

" በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በአማራ ክልል በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርስ የመብት ጥሰት እና በትግራይ እየተፈጸመ ያለ ግፍን የሚገልጹ ሪፖርቶች እንዳሉት ኮሚሽኑ አሳውቋል።

ኮሚሽኑ ያፋ ባደረገው ሪፖርት፤ የኤርትራ ወታደሮች እና የአማራ ሚሊሻ አባላት ትግራይ ውስጥ ከፍተኛ ጥሰቶችን መፈፀም መቀጠላቸውን አመልክቷል። ይህም ስልታዊ የሆኑ አስገድዶ መድፈር፣ በሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ የሚፈፀም ፆታዊ ጥቃቶችን እንደሚያካትት አመልክቷል።

ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በመንግስት ሃይሎች ይፈፀማል ስላለው የሰላማዊ ዜጎች እስራት እና የማሰቃየት ድርጊትን በተመለከተ በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል።

በተጨማሪም ፤ በቅርቡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ በአማራ ተወላጅ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን የሚያሳዩ በርካታ ሪፖርቶችን እንዳገኘ አሳውቋል።

ኮሚሽኑ ፤ የአማራ ክልል የጸጥታ ሁኔታ እያሽቆለቆለ መምጣቱ እና ለጭካኔ ወንጀሎች የሚያጋልጡ ሁኔታዎች መኖራቸው በእጅጉ እንደሚያሳስበው አመልክቷል።

ይህ ሁኔት በኢትዮጵያ እንዲሁም በሰፊው ቀጣና መረጋጋት ላይ እንዲሁም በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሴቶች፣ ወንዶች፣ ህፃናት ላይ እንድምታ እንዳለው ገልጿል።

https://www.ohchr.org/en/press-releases/2023/09/ethiopia-nearly-one-year-after-ceasefire-un-experts-warn-ongoing-atrocities

(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ሩስያ

ሩስያ ላልተወሰነ ጊዜ ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ወደ ውጭ መላክ አቆመች ፤ ይህ ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ይኖራል ተብሎ ተሰግቷል።

ሩስያ ፤ " የሀገር ውስጥ ገበያን ለማረጋጋት እንዲሁም የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎትን ለማሻሻል " በሚል ከአራት የቀድሞ የሶቪየት ሕብረት አባላት ውጭ ወደ #ሁሉም_ሀገራት የነዳጅ ምርቶችን ቤንዚን እና ናፍጣ መላክን ለጊዜው አግዳለች።

እገዳው ፦
- ቤላሩስ ፣
- ካዛኪስታን ፣
- አርሜኒያ እና ኪርጊስታን #አይመለከትም ተብሏል።

እገዳው " ጊዜያዊ ነው " የተባለ ሲሆን እስከመቼ እንደሚቆይ ሩስያ ያለችው ነገር የለም።

ሩሲያ ወደ ውጭ የምትልከው የናፍጣ ነዳጅ በቀን ወደ 900,000 በርሜል እንደሚገመት እና ሀገሪቱ በየቀኑ ከ60,000 እስከ 100,000 በርሜል ቤንዚን ወደ ውጭ እንደምትልክ የመንግስት የዜና ወኪሉ " ታስ " ዘግቧል።

የሩስያ የነዳጅ እገዳን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ሊያሳድር እንደሚችል እየተነገረ ይገኛል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ #ሰላም

#ሰላም_ከሌለ_ሁሉ_ነገር_የለም!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፦

" ... በምድር ላይ ሰላም ካልነገሰ በቀርን መቼም ምንም ነገር ሊሆን አይችልም። ሰላም ዓለምን የሚገዛ ነው ፤ ሰላም ከሌለ ሁሉ ነገር የለም። ሰላም ካለ ሁሉ ነገር አለ።

ለሰላም የሚሆን ዋጋ በዓለም ላይ አይገኝም። ብርም ይሁን ፣ ወርቅም ይሁን አልማዝም ይሁን #አይመጥነውም። ለሰላም የሚሆን ዋጋ አይመጥነውም ይሄ ሁሉ።

ሰላሙን የምናመጣው እኛው ነን ፣ የምናባርረውም እኛው ነን።

ሰላም በምድር መንገስ አለበት። ሰላም በምድር ካለ ሁሉም ነገር አለ ፦
- ሀብት አለ
- ትምህርት አለ
- ስልጣኔ አለ
- ድሃ በጉልበቱ፣ ሃብታም በሀብቱ ፣ የተማረም በእውቀቱ ሀገርን ያቀናል እራሱም ይኖራል።

ሰላም ከሌለ ሁሉም ነገር እንደሌለ የታወቀ ነው።

ስለ ሰላም #መጸለይ ምንጊዜም አስፈላጊ ነው። ሰላም በሶስት ፊደል የተወሰነች ብትሆንም ዓለምን #የምትገዛ ሰላም ናት። ሰላም ዓለምን ይገዛል ምክንያቱም ሁሉም ነገር የሚስተካከለው በሰላም ስለሆነ።

ስለ ሰላም ምንጊዜም ቢሆን #ሁሉም_ኢትዮጵያዊ በያለበት ጸሎት ማድረግ አለበት፤ በጸሎት ሁሉም ነገር ይገኛልና። "

የፎቶ ባለቤት፦ ፎቶግራፈር አቤል ጋሻው + ኢጃት (አዲስ አበባ ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል - ' የአእላፋት ዝማሬ ' - በኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ)

@tikvahethiopia
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

➡️ " በሃገራዊ ምክክሩ #ሁሉም አካላት ካልተሳተፉ ምክክሩ ውጤት ላያመጣ ይችላል " - የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

➡️ " ያኮረፉ እና ጫካ የገቡ #ታጣቂዎች በምክከሩ እንዲሳተፉ ከሲቪል ማህበረስብ  እና ከተለያዩ ሀገራት #ኤምባሲዎች ጋር እየሰራን ነው " - ኮሚሽኑ

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት እየተደረጉ ያሉ ግጭቶች ቆመው ሁሉም አካላት ወደ ንግግር አንዲመጡ ጠይቋል

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጫካ የሚገኙት ታጠቂዎች በምክክሩ ላይ እንዲሳተፉ ከለላ እንዲደረግላቸው መንግስትን የመጠየቅ ፍላጎት እንዳለው ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሳቢ ደስታ ዲንቃ " በሃገራዊ ምክክሩ ሁሉም አካላት ካልተሳተፉ ምክክሩ ውጤት ላያመጣ ይችላል " ብለዋል፡፡

በጫካ ያሉ ታጣቂዎች በምክክሩ አንዲሳተፉ ለዚህ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ  ምክር ቤቱ የጠየቀ ሲሆን ፥ " ይህ ካልሆነ ግን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስራ ውጤት ላያመጣ ይችላል " ሲል የጋራ ም/ቤቱ ስጋቱን ተናግሯል።

#ሌላው_ስጋት ብሎ ያነሳው ደግሞ የምክክር ኮሚሽኑ የተቋቋመበት አዋጅ  ግጭቶችን የማስቆም ሃላፊነት አልተሰጠውም ግጭት ሳይቆም በግጭት ውስጥ የሚደረግ ምክክር ደግሞ ውጤት ላያመጣ ይችላል ብሏል፡፡

የጋራ ም/ቤቱ ከጅምሩ ጀምሮ " በምክክሩ አንሳተፍም " ያሉ ፓርቲዎችን፣ በተለያየ ክልሎች ያሉ ታጣቂዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ እንዲደርግ ኮሚሽኑን ጠይቋል፡፡

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ዶክተር ዮናስ አዳዬ ምክክሩ አሳታፊ እንዲሆን፣ ያኮረፉ እና ጫካ የገቡ ታጣቂዎች በምክከሩ እንዲሳተፉ ከሲቪል ማህበረስብ  እና ከተለያዩ አለም ሀገራት ኤምባሲዎች ጋር እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

" ጫካ የገቡ አካላት በምክክሩ እንዲሳተፉ በመገናኛ ብዙሃን ተደጋጋሚ ጥሪዎችን እያደረግን ነው " ያሉት ዶ/ር ዮናስ " ሕጋዊ የሆነ መስሪያ ቤት ስለሌላቸው ጥሪ ለማድረግ ተቸግረናል፣ እዚህ ነን  አለን የሚሉ ከሆነ የተመካከሩ ጥሪ ወረቀት ይዘን ለመሄድ ዝግጁ ነን " ብለዋል፡፡

Credit - Sheger FM 102.1

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የፌዴራሉ መንግሥት የ2017 ጠቅላላ የወጪ በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። ለክልል መንግሥታት የበጀት ድጋፍ የተመደበው 236.7 ቢሊዮን  ብር ነው። አጠቃላይ የ2017 በጀት (971.2 ቢሊዮን) በ2016 በጀት ዓመት ከጸደቀው የወጪ በጀት አንጻር የ21.1 በመቶ እድገት እንዳለው  ተገልጿል። ዛሬ ከሰዓት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ምክር…
#Ethiopia

የደቡብ ክልል ፈርሶ እንደ አዲስ የተዋቀሩት #ሁሉም አዳዲስ ክልሎች በጀት የሚደለደልላቸው በነበረው የድሮ ቀመር እንደሆነ ተገልጿል።

ገንዘብ ሚኒስቴር #አዲስ_ቀመር የማዘጋጀት ምንም ስልጣን እንደሌለው ይህ ስልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሆነ አመልክቷል።

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የ2017 በጀት ረቂቅን ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባብራሩበት ወቅት ስለ አዳዲሶቹ ክልሎች የበጀት ድልድል ቀመር ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

" ከደቡብ አደረጃጀቶች ጋር በተያያዘ #የትኛው_ቀመር ነው ? የሚለው የምክር ቤቱ ስልጣን እንጂ የገንዘብ ሚኒስቴር ስልጣን አይደላም " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

" አዲስ ቀመር በሀገር አቀፍ ደረጃ ተጠንቶ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ የነበረው ቀመርና በፌዴሬሽን ም/ቤት በፀደቀው መሰረት ነው ገንዘብ ሚኒስቴር ድልድል የሚያደርገው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፥ ሁሌም የፌዴራል መንግሥት #ለክልሎች አጠቃላይ ምን ያህል በጀት ይመደብ ? በሚል ካለው አቅም አንጻር እንደሚያስቀምጥ አስረድተዋል።

አሁን የተበተኑት ክልሎች በደቡብ ክልል ስር አንድ ላይ በነበሩበት ጊዜ የወጣ ቀመር እንዳለ አስታውሰዋል።

አሁን እየተሰራበት ያለው ያ የቀድሞው ቀመር እንደሆነ ጠቁመዋል።

ቀመሩ ምንድነው ?

አሁን እየተገበረ ያለው ቀመር የቀድሞው ደቡብ ክልል የነበረው በጀት ለአራቱ ክልሎች #ይከፋፈላል

መጀመሪያ ሲዳማ ሲወጣ ratio ተሰርቶ በዛ መንገድ ነው የተሰራው።

ደቡብ ምዕራብ ሲወጣም ratio ተሰርቷል።

ሌሎቹ ሁለቱም ሲወጡ ማለትም ደቡብ ኢትዮጵያ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በተመሳሳይ ratio ተሰርቶ በዛ መንገድ ነው ድልድል የሚደረገው።

ይህ ደግሞ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት ነው የተካሄደው።

የነበረው ቀመር ማለት በአጭሩ ደቡብ ክልል በአንድ ላይ በነበረበት ወቅት ይመደብለት የነበረው በጀት በ ratio ለአዳዲሶቹ እንዲከፋፈል ይደረጋል።

አቶ አመህድ ገንዘብ ሚኒስቴር አዲስ ቀመር ተገዛጅቶ ተግባር ላይ እስካልዋለ ይህኑን ተፈጻሚ እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።

" በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ህዝብ ቆጠራ አልቆ ፣ አጠቃላይ የeconomic census እና survey በሚገባ ተጠናቆ ፤ አዲስ ቀመር በሚዘጋጅበት ጊዜ እና የተሟላ ቀመር ሲኖር አዲሱን ቀመር መሰረት በማድረግ ተግባራዊ   ይደረጋል (የበጀት ድልድሉ) " ብለዋል።

አዲስ ቀመር #የማዘጋጀት_ስልጣን ደግሞ የገንዘብ ሚኒስቴር ሳይሆን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣን እንደሆነ ተናግረዋል።

በአዳዲሶቹ ክልሎች ከበጀት ጋር በተያያዘ ፤ " የበጀት እጥረት " የሚሉ ጥያቄዎች እንደሚነሱ ይታወቃል።

የመንግሥት ሰራተኞች ደሞዝ መዘግየትና በአግባቡ አለመክፈልም በስፋትም ከአዳዲሶቹ ክልሎች የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia