TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia #Sudan

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ እና ሱዳንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ በአረብኛ ቋንቋ ባሰራጩት መልዕክት የሱዳንና የኢትዮጵያ ህዝቦች ወንድማማቾች መሆናቸውን ገልፀው በሁለቱ ሀገራት መካከል ችግር መኖሩ ግልፅ ነው ብለዋል።

ነገር ግን ሁለቱ ሀገራት እነዚያን ችግሮች ለመፍታት ሊጥሩ እና ሊተባበሩ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ እና ሱዳንን ለማጋጨት የሚፈልጉ መንግስታት ወይም #ሌሎች_ወገኖች ቢኖሩም እነዚህ አካላት ከሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ግጭት የሚያተርፉት አይኖርም ሲሉ አስረድተዋል።

#በውጭ_ሀይል_ግፊት በሁለቱ ሀገራት መካከል ውዝግብ ሊኖር እንደማይግባ ገልፀው ራሳችንን ልንቆጣጠር እና ከግጭት ልንቆጠብ ይግባል ብለዋል።

" በመካከላችን የጠላትነት መንፈስ ሊኖር አይግባም ፤ ይልቁንም በልማት ልንተባበር እና አብረን ልናድግ ይገባናል " ሲሉ ገልፀዋል።

ለሱዳን ህዝብ ክብር አለን ያሉት ዶ/ር ዐቢይ የሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ያጋጠማቸውን ችግር በወንድማማችነትና በመልካም ጉርብትና መንፈስ የመፍታት አቅም አላቸው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ ትላንት የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ም/ቤት ሊቀ መንበር አብዱል ፋታህ ከአውሮፓ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አኔቴ ዌበር ጋር ካርቱም ውስጥ ተወያይተው ነበር ፤ በዚህም ወቅት ቡርሃን " ከኢትዮጶያ ጋር ጤናማ ግንኙነት እንዲኖረን እንፈልጋለን " ማለታቸውን ሱና ዘግቧል።

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለውን አለመግባባት ለማርገብ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Sudan የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ እና ሱዳንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ በአረብኛ ቋንቋ ባሰራጩት መልዕክት የሱዳንና የኢትዮጵያ ህዝቦች ወንድማማቾች መሆናቸውን ገልፀው በሁለቱ ሀገራት መካከል ችግር መኖሩ ግልፅ ነው ብለዋል። ነገር ግን ሁለቱ ሀገራት እነዚያን ችግሮች ለመፍታት ሊጥሩ እና ሊተባበሩ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ እና ሱዳንን ለማጋጨት የሚፈልጉ…
#Update #Ethiopia #Sudan

" መረጃው ውሸት ነው " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

" በእግረኛ የሚመጡ ከሆነ የአካባቢው ታጣቂ በተጠንቀቅ ቆሟል " - አቶ አብራራው ተስፋ

" ሱዳን ትሪቡን " የተባለው የሱዳን ሚዲያ የሱዳን ጦር ሰራዊት ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ኃይሎች ተወሰደብኝ ያለውን እርምጃ ለመበቀል የይገባኛል ጥያቄ በሚናሳበት የአልፋሽጋ አካባቢ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ስር የነበሩ " ካላ ላባን " እና " በረከት " የተባሉ አካባቢዎችን ተቆጣጥሯል ሲል ዘግቧል።

በዘገባውም ላይ የሱዳን ጦር በርካታ የኢትዮጵያ የጦር ተሸከርካሪዎች ላይ ጉዳት እንዳደረሰ  / እንዳቃጠለ ፣ ወታደሮችንም እንደማረከ ገልጿል።

ዛሬ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ቃላቸውን የሰጡት የኢፌድሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስተር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መረጃው #ውሸት እንደሆነ አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል በም/ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ የሱዳን ጦር አካባቢው እንዳይለማ አልሞ አሁንም ድረስ ከእርቀት መድፍ እየተኮሰ እንደሆነ የወረዳው የሰላምና ደህንነት ኃላፊ አቶ አብራራው ተስፋ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልፀዋል።

አንድ የአካባቢው ነዋሪም የሱዳን ጦር ትንኮሳውን በአካባቢው ትናንት ማምሻውን ቀጥሎ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ 

መድፍ ከእርቀት ከመተኮስ ያለፈ ነገር እንደሌለ የሚናገሩት የወረዳው የሰላምና ደህንነት ኃላፊ ፥ " በእግረኛ የሚመጡ ከሆነ የአካባቢው ታጣቂ #በተጠንቀቅ_ቆሟል ነው " ያሉት፡፡ 

ህብረተሰቡ በሚተኮሱት ከባባድ መሳሪያዎች ከመደናገጥ ይልቅ ተደራጅቶ ዘልቀው የሚመጡ ከሆነ እየጠበቀ እንደሆነ ነው ለሬድዮ ጣቢያው ያስረዱት፡፡

@tikvahethiopia
#Sudan #June30March

ዛሬ በሱዳን ከፍተኛ ተቃውሞ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

ዛሬ #June30 በጎረቤት ሱዳን በሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን የሚመራውን ወታደራዊ ጁንታን በመቃወም ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

በተቃውሞ ሰልፉ ወታደራዊው ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት የያዘውን ስልጣን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ እና የሲቪል መንግስት እንዲቋቋም ይጠየቅበታል ነው የተባለው።

ተቃውሞውን ተከትሎ የፀጥታ ኃይሎች የተለያዩ መንገዶችን ዘግተዋል። በተጨማሪ የፀጥታ ኃይሎች ሰልፍ የሚያስተባብሩትን አክቲቪስቶች እያደኑ እያሰሩ ነው ተብሏል።

የሱዳን ወታደራዊ ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረ በኃላ በሱዳን ዜጎች የሚደርስበት ተቃውሞ እስካሁን የቀጠለ ሲሆን ስልጣኑን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ ግፊት እየተደረገበት ይገኛል።

እስከዛሬ ድረስ በነበሩት ተቃውሞዎች የመንግስት ፀጥታ ኃይሎች በወሰዷቸው እርምጃዎች ብዙ ሰዎች ሞተዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል።

@tikvahethiopia
#Sudan

ሱዳን በጋረጠችው የፀጥታ ችግር ሳቢያ በምዕራብ አርማጭሆ አንድ ጋሻ የሚጠጋ የእርሻ መሬት ለ1 ዓመት ያህል ሳይታረስ መቆየቱ ተገልጿል።

የሱዳን ኃይሎች የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግረው መግባት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ ነው መሬቱ ያልታረሰው።

የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ም/ል ኃላፊ ደሴ ዘውዓለ ለአሐዱ በሰጡት ቃል፤ በምዕራብ አርማጭሆ ኢንቨስትመንት ቀጠና በስፋት ጥጥ፣ አኩሪ አተር፣ ማሽላና ሰሊጥ ይመረታል ብለዋን።

በ2013/14 የምርት ዘመን በአካባቢው የእርሻ ስራ ማከናወን ባለመቻሉ በርካታ ገንዘብ ስለመታጣቱን አንስተዋል፡፡

በተመሳሳይ በዞኑ መተማ ወረዳ በሱዳን ኃይሎች ሳቢያ በ2013 ዓ.ም ከእርሻ ስራ የወጡ 76 ባለሃብቶች መኖራቸውን የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ ምህረቱፍቃድ ገላው ተናግረዋል፡፡

የሰሞኑን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ ግን ከእርሻ ስራቸው የተፈናቀሉ ባለሃብቶች አለመኖራቸውን አስረድተዋል፡፡

በወረዳው ደለሎ በሚባለው የኢንቨስትመንት ቦታ ከሱዳን የሚተኮሰው መሳሪያ በእርሻ ስራ ላይ #ከስጋት ባለፈ ያስከተለው ጉዳት እንደሌለ ገልፀዋል።

የሚተኮሰው መሳሪያ የሚያርፈው ከኢንቨስትመንት ስፍረው በ500 ሜትር ርቀት ላይ መሆኑን ነው የጠቀሱት፡፡

በመተማ ወረዳ በ3 የኢንቨስትመንት ቀጣና 256 ባለሃበቶች ተሰማርተው የቆዩ ቢሆንም ሱዳን ገፍታ በመምጣቷ ሳቢያ በአሁኑ ወቅት 76ቱ ከስራ ውጭ ናቸው፡፡

የሱዳን ኃይሎች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ከገቡበት ዕለት አንስቶ እስካሁን በምዕራብ ጎንደር ዞን 276 የሚደርሱ ባለሃብቶች ከስራቸው ተፈናቅለዋል።

መንግስት የጉዳዩን አሳሳቢነት በመመልከት የተለያዩ ዲፕሎማሲያዊ ስራዎችን በመስራት የተስተጓጎሉ የእርሻ ስራዎች እንዲቀጥሉ ማድረግ እንደሚገባው የወረዳው ባለስልጣናት ጥሪ ማቀረባቸውን አሐዱ ቲቪ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#SUDAN #DrWorknehGebeyhu

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በሱዳን የአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አድርገዋል።

ዋና ፀሀፊው በስራ ጉብኝታቸው ከሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን አሳውቀዋል።

በውይይቱ ኢጋድ ማክሰኞ ዕለት በኬንያ፣ ናይሮቢ ስለሚያካሂደው ስብሰባ የተነሳ ሲሆን ዶ/ር ወርቅነህ ከውይይቱ በኃላ በሰጡት መግለጫ በኢጋድ ስብሰባ ላይ የሁሉም አባል ሀገራት መሪዎች እንደሚገኙ ማረጋገጠናቸውን ገልፀዋል።

ስብሰባው እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት የሚደረግ ስብሰባ ነው ተብሏል።

ስብሰባውን በተመለከት ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ፤ " እጅግ በጣም ወሳኝ ስብሰባ ነው " ያሉ ሲሆን " የሁሉም አባል ሀገራት መሪዎች እንደሚመጡ አረጋግጠውልናል ፤ የቀጣናው ጉዳይ በመሪዎችችን አማካኝነት ይመከርበታል ይህ እጅግ በጣም ትልቅ ዜና ነው " ብለዋል።

" መሪዎቻችን ቀጠናውን በሚያሳስቡ ጉዳዮች ላይ ፣ ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት ስለሆኑ ጉዳዮች ፣ በድርቁ ሁኔታ ላይ " ይመክራሉ ሲሉም ገልፀዋል።

ሱዳን የወቅቱ የኢጋድ ሊቅመንበር መሆኗ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#SUDAN

ሲቪል አስተዳደሩን ገልብጠው ሙሉ በሙሉ ስልጣን ከተቆጣጠሩ ጊዜ አንስቶ በሱዳናውያን ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ እያስተናገዱ ያሉት ሌ/ጄነራል አብዳልፈታህ አልቡርሃን ጦሩ ቦታውን እንደሚለቅ ተናግረዋል።

ትላንት ሰኞ ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን በቴሌቫዥን ቀርበው የሱዳን ጦር ኃይል አገሪቱ ወደ ሲቪል አስተዳደር እንድትመለስ ለማድረግ ቦታውን ይለቃል ብለዋል።

የአገሪቱ ጦር ኃይል ሱዳን ወደ ዴሞክራሲ ለምታደርገው ሽግግር እንቅፋት እንደማይሆንና ምርጫ እንዲደረግ ወስኖ እየሰራ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ጨምረውም በአገሪቱ ያለውን ፖለቲካዊ ቀውስ ለማብቃት ከሲቪል ቡድኖች ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ ጦር ሠራዊቱ የሚያደርገውን ተሳትፎ እንደሚያቋርጥ አሳውቀዋል።

ነገር ግን አገሪቱ ውስጥ ምርጫ ስለሚደረግበት እንዲሁም ጦር ኃይሉ ሥልጣን ስለሚያስረክብበት ሂደት የጊዜ ሰሌዳ ምንም አላሉም።

በሱዳን ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲመሰረት የሚጠይቁት ተቃዋሚ ሰልፈኞች ሠራዊቱ ከፖለቲካው እንዲወጣ በመጠየቅ ለወራት የዘለቀ ተቃውሞ ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወሳል ሲል ቢቢሲ ፅፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት ይደረጋል ያተባለው የኢጋድ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል። በዚሁ ስብሰባ ላይ የአባል ሀገራት መሪዎች ናይሮቢ እየገቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። ናይሮቢ ከደረሱ መሪዎች መካከል የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የሱዳኑ ወታደራዊ አስተዳደር መሪ እና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ይጠቀሳሉ። ከኢጋድ ስብሰባ ጎን ለጎን ጠ/ሚ ዶ/ር…
#SUDAN #ETHIOPIA

የኢትዮጵያ እና የሱዳን ጉዳይ !

ኢትዮጵያ እና ሱዳን በመካከላቸው ያሉ ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸው ገለፁ።

ኬንያ ፤ ናይሮቢ የሚገኙት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከጄኔራል አብዱል ፈታሕ አል-ቡርሃን ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " ሁለቱ ሀገራት በሰላማዊ መንገድ ሊሠሩባቸው የሚችሉ በርካታ የትብብር መሠረቶች እንዳሏቸው አረጋግጠናል " ብለዋል።

" ያለን ትሥሥር ከየትኛውም መከፋፈል የሚበልጥ ነው " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " ሁለታችንም ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮችን #በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታችንን ገልጸናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
#Sudan

በጎረቤት ሀገር ሱዳን ፤ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በሚቀርበው ብሉናይል ግዛት ውስጥ በተቀሰቀሰ ግጭት በትንሹ 31 ሰዎች ሲገደሉ 39 ሰዎች ለጉዳት መዳረጋቸው በርካቶችም ሰላም ፍለጋ መሸሻቸው ተሰምቷል።

ግጭቱ የጎሳ ግጭት እንደሆነ ተገልጿል።

በበርቲ እና ሃውሳ ጎሳዎች መካከል በተነሳ የመሬት ውዝግብ ምክንያት በሮሰሪስ ከተማ ውስጥ ከትናንት በስቲያ በተፈጠረው ግጭት ቢያንስ 31 ሰዎች ሲገደሉ፣ 39 ሰዎች ቆስለዋል በርካታ ሱቆች ተቃጥለዋል።

በሁለት ግለሰቦች መካከል የተነሳ አለመግባባት ሳቢያ አንድ ሰው (በግብርና ስራ የሚተዳደር) ከተገደለ በኃላ ግጭቱ ወደ ጎሳ ግጭት ተቀይሮ ነው የበርካቶችን ህይወት የቀጠፈው ተብሏል።

ምንም እንኳን ሱዳን በአካባቢው ተጨማሪ ወታደሮችን ብታሰማራም ግጭቱ እስከ ትላንት ከሰአት በኋላ ቀጥሎ መዋሉ ታውቋል።

መንግስት ደም አፋሳሹን ግጭት ለማስቆም ችግር ባለባቸው ቦታዎች ላይ የምሽት ሰዓት እላፊ አውጇል።

#CGTNAFRICA #AlJazeera #AP

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sudan በጎረቤት ሀገር ሱዳን ፤ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በሚቀርበው ብሉናይል ግዛት ውስጥ በተቀሰቀሰ ግጭት በትንሹ 31 ሰዎች ሲገደሉ 39 ሰዎች ለጉዳት መዳረጋቸው በርካቶችም ሰላም ፍለጋ መሸሻቸው ተሰምቷል። ግጭቱ የጎሳ ግጭት እንደሆነ ተገልጿል። በበርቲ እና ሃውሳ ጎሳዎች መካከል በተነሳ የመሬት ውዝግብ ምክንያት በሮሰሪስ ከተማ ውስጥ ከትናንት በስቲያ በተፈጠረው ግጭት ቢያንስ 31 ሰዎች ሲገደሉ፣…
#Update #SUDAN

ለኢትዮጵያ ድንበር በሚቀርበው የሱዳን ብሉናይል ግዛት ውስጥ በተቀሰቀሰው ደም አፋሳሽ የጎሳ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 70 መደረሱ ሪፖርት ተደርጓል።

በበርቲ እና ሃውሳ ጎሳዎች መካከል በተነሳው የመሬት ውዝግብ ምክንያት በተፈጠረው ግጭት ቢያንስ 70 ሰዎች ሲገደሉ ከ200 በላይ ሰዎች ቆስለዋል (አብዛኞቹ በጥይት እና በስለት የቆሰሉ ናቸው) በርካታ ሱቆች ተቃጥለዋል ፤ 150 ሰዎች ተፈናቅለዋል።

በሁለት ግለሰቦች መካከል የተነሳ አለመግባባት ሳቢያ አንድ ሰው (በግብርና ስራ የሚተዳደር) ከተገደለ በኃላ ግጭቱ ወደ ጎሳ ግጭት ተቀይሮ ነው የበርካቶችን ህይወት የቀጠፈው ተብሏል።

Photo Credit : Darfur Monitors

@tikvahethiopia
#SUDAN

በትግራይ ክልል ጦርነት ሲቀሰቀስ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ ሱዳን መግባታቸው ይታወሳል።

እነዚህ ኢትዮጵያውያን ተፈናቃዮች በነበሩባቸው የሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ውስጥ #የግዳጅ የውትድርና ምልመላ ይካሄድ እንደነበረ መረጃ እንዳለው የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ለቢቢሲ በሰጠው ቃል አሳውቋል።

ተቋሙ ከወራት በፊት ከስደተኞቹ መካከል አንዳንድ ጊዜ በኃይል ጭምር ተዋጊዎችን ለመመልመል የሚደረጉ ጥረቶች እንደነበሩ " ተአማኒ ሪፖርቶች "  ደርሶኛል ብሏል ለቢቢሲ በሰጠው ቃል።

ተቋሙ ይህን ካወቀ በኃላ ምን አደረገ ?

የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን " ወታደራዊ ምልመላ መኖሩን እንደተገነዘብኩኝ ጉዳዩን ለሱዳን ማዕከላዊ መንግሥትና ለአካባቢ ባለሥልጣናት ስጋቴን ገልጫለሁ " ብሏል።  ይህንም ተከትሎ ሁኔታዎች የተሻሻሉ ይመስሉ ነበር ሲል መልሷል።

ምልመላውን ማነው የሚያደርገው ?

ይኸው የተመድ ተቋም " ወታደራዊ ምልመላውን ለማካሄድ #ከኢትዮጵያ የሚመጡ ሰዎች እንደነበሩ እና ይህንንም ከስደተኞች መረዳቱን ይገልጻል። ነገር ግን የትኛው ወገን ምልመላውን እንዳካሄድ " ማረጋገጥ አልቻልኩም"  ብሏል።

NB : ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግሥት ሰደተኛ ነን ብለው ወደ ሱዳን የገቡ ሰዎች ድንበር ተሻግረው ከህወሓት ጋር በመሆን ሲዋጉ እንደነበር መግለፁ ይታወሳል።

ያንብቡ : telegra.ph/BBC-09-07

@tikvahethiopia
#SUDAN

በሱዳን ያሉ ኢትዮጵያዊያን ከግጭት አከባቢዎች እንዲርቁና ከእንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ማሳሰቢያ ተለለፈ።

ካርቱምን ጨምሮ በተለያዩ የሱዳን ግዛቶች ግጭት ተፈጥሯል።

ከተፈጠረው ግጭት ጋር በተያያዘ ሊያጋጥም ከሚችል አደጋ እራስን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ከግጭት አካባቢዎች በመራቅና ከእንቅስቃሴ በመቆጠብ እራሳቸውን ከአደጋ እንዲጠብቁ በካርቱም የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#SUDAN

ሱዳን ውስጥ እየተደረገ ያለው ግጭት መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል።

በተለይም በዋናነት በካርቱም ሰሜናዊ አቅጣጫ ግጭት እየተካሄደ እንደሆነ ተሰምቷል።

ከትላንት አንስቶ በነበረው ግጭት የሟቾች እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ይገኛል። እስካሁን ባለው 56 ሰላማዊ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።

የፈጣን ድጋፍ ሰጭ ኃይሎች በፖርት ሱዳን ጦራቸው #ከውጭ_አውሮፕላኖች ጥቃት እንደረሰበት ገልጸዋል። እነዚህ የውጭ ኃይሎች እነማን እንደሆኑ በግልፅ አልተነገረም።

የውጭ ኃይሎች ከጣልቃ ገብነት እራሳቸውን እንዲያርቁ እና እጃቸውን እንዲሰበስቡ RSF አስጠንቅቋል።

የሱዳን ጦር በRSF ይዞታዎች ላይ የአየር ላይ የቦንብ ጥቃቶችን ስለማድረሱ ለመስማት ተችሏል። ዋና ዋና የሚባሉትን የጦር ሰፈሮችንም መቆጣጠሩ እየተነገረ ነው።

የRSF አዛዥ ጀነራል መሐመድ ሀምዳን ደጋሎ ለሚዲያ በሰጡት ቃል ፤ እስካሁን ከ "አል-ቡርሃን" ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌላቸው ገልጸዋል። " አል-ቡርሃን ተከቧል " ያሉት ዳጋሎ " ያለው አማራጭ እጅ መስጠት ብቻ ነው " ብለዋል።

ሱዳን ውስጥ የምትገኙ ቤተሰቦቻችን ነገሮች እስኪረጋጉ እራሳችሁን እንድትጠብቁ የሚወጡ ትዕዛዞችንም እንድትፈፅሙ አደራ እንላችኃለን።

ቪድዮ ፦ በሱዳን ከተማ ውስጥ ሲቪል ሰዎች በሚኖሩባቸው አካባቢዎች የሚደረጉ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ያሳያሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በጎረቤት ሱዳን ያለው ውጊያ ዛሬ ለሶስተኛ ቀን መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል። ከካርቱም ጨምሮ ከሌሎች ከተሞች በወጡ መረጃዎች ዛሬም በከባባድ መሳሪያ የታገዘ የከተማ ውስጥ ውጊያ እየተካሄደ ነው። በተለይም በካርቱም ሰሜናዊ እና ደቡባዊ ክፍል የከባድ መሳሪያ ውጊያ እንዳለ ተነግሯል። የሠራዊቱ ጠቅላይ ዋና መሥሪያ ቤት በር ፊት ለፊት ውጊያ እየተካሄደ ሲሆን አርኤስኤፍ (RSF) ከቅዳሜ ጀምሮ…
#Sudan

በሱዳን የአሜሪካ ኤምባሲ ተሽከርካሪ በጥይት ተደበደበ።

በሱዳን ፣ ካርቱም የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ብረት ለበስ ተሽከርካሪው " ሆን ተብሎ " በጥይት መደብደቡን አስታወቀ።

ድርጊቱን የፈፀመው ሄሜቲ የሚመሩት RSF ቡድን መሆኑን ኤምባሲው ለአል አረቢያ ገልጿል።

ኤምባሲው ተሽከርካሪው በ100 ጥይት መደብደቡን ገልጾ ድብደባው ያደረሰው ምንም ጉዳት የለም ብሏል።

በሌላ በኩል ፤ የአሜሪካ መንግሥት ጦርነት ውስጥ ካለችው ሱዳን ዜጎቹን የማስወጣት እቅድ እንደሌለው ዋይትሃውስ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#SUDAN

በሱዳን የEU አምባሳደር ጥቃት ተፈፀመባቸው።

በሱዳን ካርቱም ሚገኙት የአውሮፓ ህብረት (EU) አምባሳደር በመኖሪያ ቤታቸው ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ተሰማ።

አምባሳደሩ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ያሳወቁት የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ዲፕሎማት ጆሴፕ ቦሬል ናቸው (በትዊተር ገፃቸው)።

ቦሬል ስለ ጥቃቱ ምንም አይነት ዝርዝር ነገር ባይገልጹም አምባሳደሩ ግን " ደህና ናቸው " ብለዋል።

የዲፕሎማቲክ ቦታዎችን እና ሰራተኞችን ደህንነት ማስጠበቅ የሱዳን ባለስልጣናት ቀዳሚ ኃላፊነት ነውም ሲሉ ገልጸዋል።

ምንም እንኳን ቦሬል ፤ በሱዳን የአውሮፓ ህብረት አምባሳደርን ስም ባይፅፉም ስማቸው አይዳን ኦሃራ የሚባሉ ሲሆን የ #አየርላንድ ዲፕሎማት ናቸው።

ቦሬል ካርቱም ውስጥ የተፈፀመው ጥቃት ፤ በሌሎች ሀገራት የሚሰሩ ዲፕሎማቶች ጥበቃን የሚደነግገውን የተመድ ስምምነት የ " ቪይና ኮንቬንሽን " በእጅጉ የጣሰ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ የአውሮፓ ህብረት ቃል አቀባይ ናቢላ ማስራሊ ለAFP በሰጡት ቃል " የሰራተኞች ደህንነት ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው " ብለዋል፤ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡድን ከካርቱም እንዲወጣ እንዳልተደረገ ተናግረዋል።

ቃል አቀባይዋ ፤ በሱዳን ያለው የፀጥታ እና ደህንነት ሁኔታ እየተገመገመ ነው ብለዋል።

@tikvahethiopia