TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba #ባጃጅ

በአዲስ አበባ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ አይቀሬ እንደሆነ ተሰምቷል።

በአዲስ አበባ ከተማ የባለሶስት እና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች  የአሰራር ፣ የአጀረጃጀት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የዲሲፒሊን ቁጥጥር አፈጻጸም መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጎ ነበር።
                              
በውይይቱ ላይ ፦
- የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ
- የትራፊክ ማናጅመንት ፣
- የትራንስፖርት ቢሮ
- የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የማዕከልና የክ/ከተሞች ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

በአፈፃፀም መመሪያው የባለ ሶስትና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ካሁን ቀደም ሲያጋጥሙ የነበሩ የሕግ ጥሰቶችንና የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል ሲባል አገልግሎት ሰጪዎቹ ፦

የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ ፣

የአዲስ አበባ የሠሌዳ ቁጥር

በማህበር መደራጀት እንደሚኖርባቸው ተገልጿል።

" በአዲስ አበባ፣ የከተማ አስተዳደሩን ታርጋ ለጥፈውና የአዲስ አበባ መታወቂያ ይዘው ከሚሰሩት ይልቅ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አሽከርካሪዎች መበራከት የፀጥታ ችግር ሆነው ቆይተዋል " ተብሏል።

ይህ ደግሞ በተለይ በወንጀል ድርጊት ላይ ተሳትፈው በሚገኙ አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ አዳጋች እንደነበር ተገልጿል።

በዚሁ መድረክ ላይ " የባጃጅ ትራንስፖርት የከተማዋን ዘመናዊ እሳቤ የሚመጥን ስላልሆነ በሂደት ሙሉ በሙሉ አገልግሎቱ የሚቋረጥ ይሆናል " ተብሏል።

" እስከዚያ ጊዜ ድረስ የባለሶስት እግር አሽከርካሪዎች የአዲስ አበባ መታወቂያ፣ ታርጋ እና በማህበር መደራጀት ይኖርባቸዋል " ነው የተባለው።

አሁን ላይ በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ሰፊ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ፍላጎት በመኖሩ በነዚህ አካባቢ ያለው ፍላጎት በሌላ አማራጮች እስኪተካ ድረስ አገልግሎቱ እንደሚቀጥል ተመላክቷል።

በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባሉባቸው እንዲሁም በውስጥ ለውስጥ ሰፈሮች ዜጎች ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎችን / ባጃጅ ለትራንስፖርት ይጠቀማሉ።

እጅግ በርካታ ዜጎችም በተለይ በተለይ ወጣቶች በዚሁ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ ገቢ ያገኛሉ ቤተሰባቸውንም ያስተዳድራሉ።

ከዚህ ቀደም ባጃጆች በተለይ በከተማው ዳርዳር ከዋና ዋና የሚባሉ መንገዶች ወጥተው ውስጥ ለውስጥ ብቻ እንዲሰሩ መደረጉ የሚዘነጋ አይደለም።

#AddisAbaba
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ 1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን…
#AddisAbaba

“ የጫት መቃሚያ ፣ የሺሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው ” - ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ወንጀሎች እንደሚደርሱባቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡

አንዳንዶቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ የጸጥታ አካላት ልብስ ለብሰው ጸጥታ አስከባሪ በመምሰል ወንጀል የሚፈጽሙ አሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦

°  ተመሳስለው ወንጀል የሚሰሩ አካላት ላይ ምን አይነት ክትትል እየተደረገ ነው ?

°  ወንጀል በከተማዋ በምን ደረጃ ይገኛል ?

° ሕዝቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?

“ ሌባ የተለያዬ የወንጀል አፈጻጸም ስልት አለው፡፡ አንዱ የጸጥታ አካል መስሎ፣ ልብሱን በተለያዬ አይነት መንገድ ለማግኘት ሙከራ አድርጎና ለብሶ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፡፡

ይሄ በጣም ከበ ሁለት ጥፋት ነው፡፡

አንደኛው ህብረተሰቡ ፖሊስ ሊመስለው ከቻለ በፖሊስ ላይ ያለው አመኔታ ምንም ጥያቄ የለውም ይወርዳል፡፡ ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ወንጀሉ በፖሊስ ላይ ጫና/ሥራ ይፈጥራል፡፡

ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግና መረጃዎች በሚኖሩ ሰዓት ቶሎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡

በተለይ በእንደዚህ አይነት ሁኔታዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ በጣም በጣም፡፡ ትልቅ ዋጋም የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡

ወንጀል ፈጻሚውን በመያዛችን የጸጥታ አካላትን ልብስ ከየት አመጣህ ? ብሎ ለመጠየቅና ተባባሪ የሆነ አካል ካለ ተገቢ እርምጃ ለመውሰድ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡

ወንጀሉ ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድና ለህዝብ ግልጽ በማድረግ በእንደዚህ አይነት ወንጀል የተሰማሩ ሰዎች ሁለት፣ ሦስቴ እንዲያስቡ እናደርጋለን፡፡

ግን ሰው መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን መቻል አለበት፡፡

መረጃ ማድረስ ብቻ ሳይሆን ፈጣን ማድረስ ነው መሆን ያለበት፡፡ አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ሰው መክሯቸው ' መረጃ ስጡ ' ተብለው ነው የሚናገሩት፡፡ ፈጣን ነው መሆን ያለባቸው፤ እንደዚያ ከሆነ ወዲያው በቁጥጥር ሥር እናውላቸዋልን፡፡

ወንጀሎች ከመፈጸማቸው አስቀድሞ ለመፈጸሙ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስቀድሞ በማወቅ የማስወገድ ሥራ መሰራት አለበት፡፡

ለምሳሌ ፦ የወንጀል መንስኤ ብለን እኛ የምናያቸው የጫት መቃሚያ፣ የሽሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው፡፡

በዚህ በኩል ፖሊስ የሚወስደው በጣም ጠንካራ የሆነ እርምጃ አለ፡፡ ግን መረጃ ከመስጠት በኩል አሁንም ክፍተቶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም ለፖሊስ መረጃ ከመስጠት ይልቅ የመደበቅ ሁኔታ አለ፡፡

ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነን ነው የወንጀል መከላከልን ሥራ የምንሰራው፡፡ ግን ግለሰቦቹ ወንጀል ከተፈጸመባቸው ወደ ሚዲያ ሳይሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው መሄድ የሚጠበቅባቸው፡፡ በትክክል የከተማውን የጸጥታ ሁኔታ ቼክ የምናደርግበትም አግባብ ያ ነው፡፡

ስለዚህ ወንጀል ሰዎች ላይ ሊፈጸም ይችላል፡፡ በተቻለ አቅም በከተማው ላይ የወንጀል ስጋት እንዳይኖር ነው እየተሰራ ያለው፡፡ በ2016 ዓ/ም አጠቃላይ የተቋማችን አፈጻጸም 31 ፐርሰንት ወንጀልን ቀንሰናል፡፡

አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ በመሆኗ ለተለያዩ ወንጀል መፈጸሞች ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ከክልል ከተሞችም በብዛት ሰዎች ይመጣሉ፡፡ ሰው ሥራ፣ ቋሚ አድራሽ ከሌለው ያለው አማራጭ አንድም መለመን ካልሆነም ወደ ዘረፋ የሚገባበት ሁኔታ ይኖራል፡፡

አጠቃላይ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁመው ከግምት ውስጥ በማስገባት የወንጀል መከላከልን ሥራ በመስራት ከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንድትሆን ማድረግ እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡

ከመደበኛ ሥራችን ጎን በጎን ኦፕሬሽናል የሆኑ ሥራዎችንም በመስራት በሌቦች ላይ ብቻ አይደለም በተቀባዮችም ጭምር ትልቅ ሥራ እየተሰራ ነው፤ በተለይ የመኪና እቃ ስርቆት በሚፈጽሙት፣ እቃውን በሚሸጡ፣ በሚደልሉ ላይ፡፡

በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ እንኳ በተሰራው ሥራ ወደ 71 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የመኪና እቃም ይዘናል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ' ወንጀል ተፈጸመብኝ ' የሚል ሰው ሊያጋጥም ይችላል፡፡ እሱን ለመከላከል ደግሞ የምንሰራቸው ሥራዎች አሉ፡፡

ወንጀል የሚፈጽማባቸው አካላት ወደ ፖሊስ መጥተው ያመልክቱ፡፡ በርካታው ሰው ከዚያ ይልቅ ወደ ሚዲያ ይሄዳል፡፡ ወደ ሚዲያ አይሂድ ማለት አይደለም ግን ወደ ፖሊስ ቢመጣ ያለንበት የመከላከል አቅም የቱ ጋ ድርሷል ለማለት ይረዳናል።
"

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" ሰራተኞቹ ከሥራ ፈቃድ ወስደው ቤተሰብ ለመጠየቅ ሃና ማሪያም ተብሎ ወደ ሚጠራው ሰፈር ሲጓዙ ነበር " - የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ዛሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 3 የሆቴል መስተንግዶ ሠራተኞች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው " ቀይ አፈር " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቀን 8፡20 ላይ ነው እንደደረሰ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

አንድ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ መንገድ ሲጠቀሙ የነበሩ እግረኞችን ገጭቶ ባደረሰው አደጋ ነው የ3ቱ ሰራተኞች ህይወት ያለፈው።

ሟቾቹ ሶስቱም ሴቶች ሲሆኑ ዕድሜያቸው ከ25-30 ይገመታል።

ሰራተኞቹ ከሥራ ፈቃድ ወስደው ቤተሰብ ለመጠየቅ " ሃና ማሪያም " ተብሎ ወደ ሚጠራው ሰፈር ሲጓዙ ነበር።

ከሟቾቹ ጋር አብራ ስትጓዝ የነበረች አንዲት ሴት እራሷን ስታ ሕክምና እየተከታተለች ትገኛለች።

በበዓል ወቅት መሰል አደጋ እንዳይከሰት አሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እና በእርጋታ እንዲያሽከረክሩ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በጎርፍ ሊወሰዱ የነበሩ እናትና ልጅ በአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ህይወታቸዉን መታደግ ተቻለ።

ዛሬ መስከረም 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ገደማ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ጀርመን ድልድይ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በጎርፍ ሊወሰዱ የነበሩ እናትና ልጅ በአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጥረት ህይወታቸዉን ማትረፍ እንደተቻለ የእሳትና አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።

እናትና ልጇ በወንዝ ዳርቻ ካለዉ የጎመን ማሳቸዉ ዉስጥ ጎመን በመሰብሰብ ላይ ሳሉ በድንገት ደራሽ ጎርፍ ሊወስዳቸዉ የነበረ ቢሆንም በወንዝ መሀል ባለ ድንጋይ ጫፍ ላይ ሆነዉ ህይወታቸወን ማቆየት ችለዋል።

ይሁንና የጎርፉ መጠን እየጨመረ በመምጣቱ እናትና ልጁ በጎርፉ ሊወሰዱ በተቃረቡበት ሰዓት የኮሚሽኑ ጠላቂ ዋናተኞች ደርሰዉ ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸዉ የእናትና ለጇን ህይወት መታደግ እንደተቻለ ተገልጿል።

በአካባቢዉ ቀደም ሲል በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በዚህ አካባቢ ከወንዙ የሚገኘዉን ዉሀ በመጠቀም የጎመንና ሌሎች ተክሎች ማሳ የሚገኝበት ነዉ።

በአሁኑ ሰዓት የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ባለመጠናቀቁ ባለማሳዎች ተክሎቹን ለመሰብሰብ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ የጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም የሚችል በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #ባጃጅ በአዲስ አበባ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ አይቀሬ እንደሆነ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ከተማ የባለሶስት እና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች  የአሰራር ፣ የአጀረጃጀት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የዲሲፒሊን ቁጥጥር አፈጻጸም መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጎ ነበር።                               …
#AddisAbaba

“ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ ” - የኡ/ ትራንስፖርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ውጪ መጥተው የሚሰሩ ባለሦስትና አራት እግር አሽከርካሪዎች የአዲስ አበባ መታወቂያ፣ የአዲስ አበባ ሰሌዳ እስከሚያሟሉና በማኅበር እንስከሚደራጁ ድረስ በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።

ቢሮው ይህን ያለው በእነዚህ የተሽከርካሪ አይነቶች ወንጀል እየተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ነው፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ጉዳዩን በተመለከተ ከወጣው መግለጫ በተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጥ ከከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡

Q. በታገዱት የትራንስፖርት አይነቶች ሥራ ተሰማርተው ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለምን ሰፋ ያለ ጊዜ አልተሰጣቸውም ? ቀድሞ ማሳወቅ አይቻልም ነበር ?

አቶ ዳኛቸው ፦

“ አዲስ አበባ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርት ነው፡፡ ከማስ ትራንስፖርት አንጻር አዲስ አበባ አውቶብስ ድርጅት አለ፡፡ ድጋፍ ሰጪ የምንላቸው ሦስት ቁጥር ታክሲዎች አሉ፡፡ ከዚያ ውጪ ቁጥር አንድ የምንላቸው ታክሲዎች አሉ፡፡

ከእነዚህም የበለጠ የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርቱ ነው፡፡ ከባጃጅ ትራንስፖርት ጋር ባለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደራጅቶ ስምሪት መስጠት የሚችለው በአዋጁ መሠረት ራሱ የሰጠውን ታርጋ ብቻ ነው፡፡

ይሄ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ክልሎችና ከተሞች በራሳቸው ታርጋ የሰጡት፣ የመዘገቡት ብቻ ነው አደራጅተው ማሰማራት የሚችሉት፡፡

ከባጃጂ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ ውስጥ ወደ 5,000 አካባቢ የሚጠጉ ባጃጆች በ93 ማኅበራት፣ እንዲሁም በ73 መስመሮች አካባቢ ላይ ታፔላ ወስደው እየተሰማሩ ነው ያሉት፡፡

አዲስ አበባ በዚህ ደረጃ አጣዳፊ ሥራውን ማሰማራት ተገቢነት የለውም፡፡

ከአዋጅ ውጪ ነው የሚል ቅሬታዎች በተደጋጋሚ ሲነሳ ነው የቆየው፡፡ ቅሬታውም ተገቢ ነው፡፡  ስለዚህ በዚህ ሰዓት ባጃጅን ማበረታታት፣ ማሰማራት አይደገፍም፡፡

በአንድ በኩል የአዲስ አበባ ታርጋ የላቸውም ኦልሞስት 99 ፐርሰንት፡፡ 243 ብቻ ናቸው የአዲስ አበባ ታርጋ ያላቸው ከ5 ሺዎቹ፡፡

አንደኛ ሕጉ መከበር አለበት፡፡ ስህተት በስህተት ላይ መደገም የለበትም፡፡ ሁለተኛ እነዚህ ባጃጆች አካባቢ ሌብነት ይካሄዳሉ፡፡

ህዝቡም እሮሮ ያቀርበል፡፡ ብዙ ቅሬታዎች ናቸው የሚቀርቡት፡፡ የጽንፈኛ ኃይልም አጋዢ ሆነው የሚሰሩ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ለከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ፡፡

ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ስለዚህ እንዚህ ባጃጆች እንዲቆሙ ሳይሆን ወደ ሕግ እንዲመለሱ ነው፡፡ ወደ ሕግ እንዲመለሱ ሲደረግ ደግሞ አንደኛ መደረግ ያለበት አንደኛ ታርጋ ማውጣት ነው፡፡

ታርጋ ለማውጣት ደግሞ እዘዚህ ባጃጆች ታርጋ ያወጡበት ሂደው ክሊራንስ፣ ሊብሬ አምጥተው የአዲስ አበባ ታርጋ ወስደው እንዲደራጁና ወደ ስምሪት እንዲገቡ ማድረግ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ታርጋ ይወስዳሉ፣ ይዘጋጃሉ፣ ወደነበሩበት ይመለሳሉ”።


Q. ቢሮው አጣድፎ ውሳኔውን የወሰነበት ምክንያት ምንድን ነው? አጭር ጊዜ አልሆነም ወይ? ለሚለው ጥያቄ ቀጥታ ምላሽ እንዲሰጡ በድጋሚ ጠይቀናቸዋል፡፡

አቶ ዳኛቸው፦

“ ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ትራንስፖርት ሰላምን መሆንን፣ ምቹ መሆንን፣ ተደራሽ መሆንን ይፈልጋል። ስለዚህ በባጃጆች አካባቢ ያለው ሌብነት፣ ዝርፊያ፣ ያለው የከተማውን ሰላም የማናጋት መጠቀሚያነት ከህዝብ በተደጋጋሚ እሮሮ የመጣበት ነው።

ሁለተኛ ታርጋ የሰጥዋቸው ክልሎች፣ ‘አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እኛ የሰጠነውን ካርታና ሊብሬ አደራጅቶ የማሰማራት ስልጣን የለውም ሕገ ወጥ ሥራ ነው እየሠራ ያለው’ የሚል ቅሬታ፣ ስሞታ፣ ክስ አለ፡፡

እውነት ነው በሰላማዊ መንገድ ሥራ የሚሰሩ ልጆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እነርሱንና ጤናማ ያልሆኑትን ለመለየት ወደ ሕጋዊ መስመር መመለስ ግድ ስለሆነ፡፡

ሰፊ ጊዜ የሚፈልግ ጉዳይ አይደለም፤ ምርምር አይደለም፡፡ ታርጋ ያወጡበት፣ መረጃቸው ያለበት ሂደው ማምጣት ነው፡፡ አብዛኛው ደግሞ መረጃ የሚያሳየው ሸገር ዙሪያ ነው፡፡

ምክንያቱም አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባጃጂ ታርጋ ሲሰጥ ስላልነበረ አብዛኛው ያወጡት እዚህ አካባቢ ናቸው። አማራ ክልልም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡ ሌሎች አካባቢዎችም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡

ዞሮ ዞሮ ግን ለምን ተጣደፋችሁ? ለሚለው ነገር የከተማውን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ ማንኛውም ተሽከርካሪ ሕግ አክብሮ እንዲሰራ ለማድረግ ነው”፡፡


Q. አሽከርካሪዎቹ በከተማዋ ለመስራት እንደያሟሉ ከተጠየቁት መስፈርት አንዱ የአዲስ አበባ የነዋሪነት መታወቂያ መሟላት ነው፡፡ ይህን አገልግሎት ደግሞ ኤጀንሲው እየሰጠ አይደለም፡፡ መታወቂያውን የት አምጥው ያሟላሉ ተብሎ ነው እንዲህ የተደረገው ? ቢሮው ጉዳዩን አጢኖት ነበር ?

አቶ ዳኛቸው፦

“ ይሄ ጥያቄ ለምን Issue ሆኖ ይነሳል? የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መታወቂያ እየሰጠ አይደለም የሚለው መረጃ ስህተት ነው፡፡

ወሳኝ ኩነት ከከተማ ጀምሮ እስከ ወረዳ አደራጅቶ በቴክኖሎጅ ታግዞ ነዋሪው ግልጽ በሆነ መንገድ መታወቂያ እንዲያገኝ አመቻቾቶ መስራት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። "


Q. ከክልል ከተሞች በመሸኛ ለሚመጡት እየሰጠ እንዳልሆነ መረጃው እንዳለን ገልጸንላቸው፣ በድጋሚ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀናቸዋል፡፡
አቶ ዳኛቸው፦


“ አሁን እኛ እያወራን ያለነው ከክልል ሰው አዲስ አበባ ውስጥ መታወቂያ አውጥቶ ሥራ ይስራ እያልን አይደለም ያለነው፡፡ ግልጽ ነው አቅጣጫው ለምንድን ነው የአዲስ አበባ ነዋሪ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈለገው ?

ዝርፊያዎች፣ ሌብነት፣ ተለያዩ ጽንፈኛ ኃይሎች መጠቀሚያ መሆን ማስቀረት ከተፈለገ የነዋሪነት ወታወቂያ የግድ ያስፈልጋል። ”
ብለዋል፡፡

ሌላ ጥያቄ እያቀረብንላቸው በነበረበት ወቅትም ማብራሪያቸውን መቅዳት እንድናቆም አስገድደው፣ ለጥያቄው ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምላሽ ላልሰጠባቸው ሌሎች በርከት ያሉ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በሀሰተኛ የብር ኖት ግብይት የፈፀሙ 2 ተጠርጣሪዎች እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ ገብርኤል አካባቢ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12፡ 30 ሰዓት ላይ ነው።

ግለሰቦቹ ከአንድ ሸቀጣ ሸቀጥ መሸጫ እና ዘይት አከፋፋይ ከሆነ ሱቅ ውስጥ በርከት ያለ ባለ 20 ሊትር ዘይት ለመግዛት ተስማምተው ያስጭናሉ።

በኋላም ሒሳብ ሲከፍሉ ገንዘቡ ከባንክ እንደወጣና ህጋዊ ለማስመሰል አሽገው 42 ሺህ 350 ብር ለነጋዴው ይከፍሉታል፡፡

ሆኖም የግል ተበዳይ ገንዘቡ ሀሰተኛ መሆኑን ተጠራጥሮ በአካባቢ ነዋሪዎች ትብብር እንዲያዙ አድርጓል።

ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይ መጠራጠሩን ሲረዱ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 30791 ተሽከርካሪ በመጠቀም ለማምለጥ ቢሞክሩም በአካባቢው በነበሩ ሰዎች ሊያዙ ችለዋል።

ግብይት ሊፈፅሙበት ከነበረ 42 ሺህ 3 መቶ 50 ብር ውስጥ 39 ሺህ 4 መቶ ሃሰተኛ ብር እጅ ከፍንጅ ተይዘው ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ጉቦ በመቀበል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ሰራተኞቹ የግብር መጠንን በመቀነስ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ጉቦ በመቀበል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የአዲስ አበባ ፖሊስ መርማሪ ያቀረበውን የጥርጣሬ መነሻንና የተጠርጣሪ ጠበቃ መከራከሪያ ነጥቦችን ተመልክቷል።

ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው የታዩት ተጠርጣሪዎች ፦

የአ/አ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ ሃብታሙ ግዲሳ፣

የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ስምረት ገ/እግዚአብሔር፣

የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ዮሴፍ ባቡ፣

የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር አቤኔዘር ቶሎሳ፣

ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ለሚ ሲሌ

ገንዘብ ተቀባይ ባለሙያ ወ/ሮ መቅደስ አረጋዊ ናቸው።

ተጠርጣሪዎቹ የተሰጣቸውን የስራ ኃላፊነትን ወደ ጎን በመተው ከግብር ከፋይ ግለሰቦች ጋር በጥቅም በመመሳጠር ከግብር ከፋይ ድርጅቶች " ግብር እንቀንስላችኋለን " በማለት በመደራደር ከ100 ሚሊየን ብር የግብር መጠንን ወደ 13 ሚሊየን ብር ዝቅ በማድረግ ግብርን በመቀነስ ከተለያዩ ድርጅቶች በተለያዩ መጠኖች ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ጉቦ ተቀብለዋል በማለት መርማሪ ፖሊስ የጥርጣሬ መነሻውን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አቅርቧል።

መርማሪ ፖሊስ በባንክ ሂሳባቸው የጉቦ ገንዘብ ገቢ የተደረገላቸው ተጠርጣሪዎች መኖራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ መሰብሰቡን በማመላከት ተጨማሪ ግብረ አበር ለመያዝና ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ማስረጃዎች አሰባስቦ ለመቅረብ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ በበኩሏ ደንበኞቿ በመርማሪ ፖሊስ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት " አልፈጸሙም " በማለት በመከራከር የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቃለች።

መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢወጡ ማስረጃ ሊያሸሹ ይችላሉ በማለት በጠበቃቸው የቀረበውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ እንዲደረግ በመጠየቅ ተከራክሯል።

የፖሊስ የጥርጣሬ መነሻን እና ግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የምርመራ መዝገቡ ጅምር በመሆኑ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ለፖሊስ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን በማመን የተጠርጣሪ የዋስትና ጥያቄን በማለፍ ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።

መረጃው የኤፍ ቢ ሲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

ከፖሊስ የተገኘ መረጃ  ፦

በአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ እና ባለሙያዎች የሆኑት ፦
- አቶ ሃብታሙ ግዲሳ
- ስምረት ገ/እግዚአብሔር (የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- አቶ ዮሴፍ ባቡ (የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- አቶ አቤኔዘር ቶሎሳ (የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- አቶ ለሚ ሲሌ (ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- ወ/ሮ መቅደስ አረጋዊ (ገንዘብ ተቀባይ)

ጳጉሜ 05/2016 ዓ.ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ውስጥ ግብር ከፋይ የሆኑ ግለሰብ የ2011 ዓ.ም እና 2012 ዓ.ም የአንድ አመት ግብር ኦዲት እንዲደረግላቸዉ የሚጠበቅበትን ሰነድ ያቀረበላቸዋል።

መክፈል ያለብህ 100,000,000 ብር ነዉ ይሉታል።

ይህን ያህል " አልከፍልም ካልክ ግማሹን አስይዘህ ነዉ ይግባኝ የምታቀርበዉ " በማለት ይገልጹለታል።

ለጊዜዉ በቁጥጥር ስር ያልዋለ ግለሰብ ሂሳብ አስጨራሽ በሚል የቀረ ደላላ ጉዳዩን አስተካክላለሁ በሚል በማግባባት ለራሱ 3,000,000 ብር እና ለሰራተኞቹ ስምንት 8,000,000 ብር ለመንግስት ከመቶ ሚሊየን በመቀነስ " 13,000,000 ብር ትከፍላለህ " በማለት ያስማማሉ።

በዚህም 8,000,000 ብር #በቤተሰቦቻቸዉ አማካኝነት በመቀበል 13,000,000 ብር የመንግስት የሚከፈለዉን እንዲከፍል መተማመኛ ሲሰጡት በተደረገ ክትትል እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

ግለሰቦቹ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቤንዚን ? በአዲስ አበባ ቤንዚን ረጅም ሰዓት ሰልፍ ሳይሰለፉ ማግኘት ዘበት ከሆነ ሰነባብቷል። ባለፉት ሳምንታት በትንሽ በትንሹ የጀመረው የቤንዚን ሰልፍ ከሰሞኑን እጅግ ብሶበታል። በአንዳንድ ማደያዎች " ቤንዚን የለም " እየተባለ ሲለጠፍ ቤንዚን ያለባቸው ማደያዎች እጅግ በጣም ረጅም ሰልፍ ነው ያለው። በዚህም ምክንያት የመኪና አሽከርካሪዎች ቀናቸውን በቤንዚን ሰልፍ ለማሳለፍ እየተገደዱ ይገኛሉ።…
#ቤንዚን

° " ቤንዚን ማግኘት ፈተና ሆኖብልናል " - አሽከርካሪዎች

° " የቤንዚን አቅርቦት ችግር የለም " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን

አሁን ላይ በአዲስ አበባ ቤንዚን ማግኘት አስቸጋሪ እንደሆነባቸው አሽከርካሪዎች እየገለጹ ናቸው።

የተለያዩ ማደያዎች ላይ " ቤንዚን የለም " የሚል የተለጠፈ ሲሆን ቤንዚን አለባቸው የሚባሉና የሚቀዳባቸው ማደያዎች ላይ እጅግ በጣም ረጅም ሰልፎች ነው ያሉት።

አሽከርካሪዎች ቤንዚን ለመቅዳት ሰዓታትን ለመሰለፍ እየተገደዱ ነው። በዚህም ቀናቸውን በሰልፍ እያሳለፉ በመሆኑ ስራቸው እየተበደለ ነው።

ምንም እንኳን ከሰሞኑን ችግሩ ብሶ ቢታይም ባለፉት ሣምንታት አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰልፎች ይታዩ ነበር።

ለመሆን ምንድነው የተፈጠረው ?

በዚህ ጉዳይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን መ/ቤትን ማብራሪያ ጠይቋል።

የተፈጠረው ነገር ምንድን ነው ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የባለስልጣኑ አንድ አካል በሰጡን አጭር ማብራሪያ፣ " የቤንዚን እጥረቱ የለም " ብለዋል፡፡

በከተማዋ ያለውን ችግር በተመለከተ ፤ " የእኛ ልጆች ኢስፔክሽን ሲወጡ ያዩት ነገር አሁን የቴሌ ብር አጠቃቀም ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ ነው፡፡ ምክንያቱም በካሽ ግብይት መፈጸም አይቻልም ፤ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ስለሆነ አብዛኛው ሰው ያንን ሲስተም ሳይጠቀም ቆይቶ በካሽ ትራንሰፈር እያደረገ ነበር፡፡ በዚያ ምክንያት አንዱ ከማደያ ላይ ነዳጅ ቀድቶ ለመውጣት ረጅም ሰዓት ይወስዳል " ብለዋል፡፡

" እናም ረጃጅም ሰልፍ የሚፈጠረው በዛ ነው እንጅ በእጥረት አይደለም " ብለው ለተጨማሪ መረጃ ወደ ሌላ የሚመለከተውን የተቋሙ አካልን የመሩን ሲሆን ሌላኛው አካል ማብራሪያ ለመስጠት ለዛሬ ቀጠሮ ቢሰጡም በቀጠሮ ሰዓት በተደጋጋሚ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

በሌላ በኩል ፥ ባለስልጣን መ/ቤቱ ለካፒታል ጋዜጣ በሰጠው ቃል ፥ በአዲስ አበባ ከተማ በአማካይ እስከ 1.4 ሚሊየን ሊትር ቤንዚን እያቀረበ መሆኑን አመልክቷል።

" በአዲስ አበባ ከሰሞኑ በነዳጅ ማደያዎች ላይ የተስተዋለው ያልተለመደ ሰልፎች ባለፈው ሣምንት በነበሩት ሁለት ቀናት ከበዓላት ጋር በተያያዘ የአቅርቦት መቀነስ በመኖሩ ነዉ " ብሏል።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ፥ " በከተማዋ በቀን በአማካይ እስከ 1.4 ሚሊየን ሊትር ቤንዚን የሚቀርብ ቢሆንም የማደያዎቹ አገልግሎት አሰጣጥ ዝግታ መኖሩ እና የቤኒዚን ምርት ላይ ከፍተኛ የጥቁር ገበያ ፍላጎት መኖር ሠልፎችን ምክኒያት በማድረግ የአቅርቦት ዕጥረት ያለ በማስመሰል አጋጣሚውን ለትይዩ ገበያዉ ለመጠቀም መሞከር ይታያል " ሲል አስረድቷል።

" ከነዳጅ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ያለው ሁኔታ በአፋጣኝ እንዲስተካከል የተደረገበት እርምጃ እንዲወሰድ ተደርጓል " ያለዉ መ/ቤቱ " በዚህም በመዲናዋ ከመደበኛ ኮታ ተጨማሪ ቤንዚን እንዲቀርብ ሆኗል " ሲል አስታዉቋል።

" የየቤኒዚን ተጠቃሚ አሽከርካሪዎች አቅርቦት በበቂ ሁኔታ መኖሩን ተረድተው በተለያዩ አከባቢዎች የሚገኙ ማደያዎችን በመጠቀም መገልገል ይችላሉ " ሲል አሳስቧል።

#AddisAbaba #Benzine

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

ነገ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ተደርገዋል።

መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5:00 ሰአት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የሚከተሉት ናቸው።

- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ

- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)

- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ

- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ

- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ

- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ

- ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ

- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከመስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋል።

በተጨማሪም በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ነው።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ። #ኦርቶዶክስተዋሕዶ @tikvahethiopia
#Ethiopia

" በ2,575 የተለያዩ ደብሮችና ቦታዎች በሰላም ተከብሮ ተጠናቋል " - የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

በመላው ሀገሪቱ በተለይም #በአዲስ_አበባ መስቀል አደባባይ የተከበረው የ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።

የፌዴራል ፖሊስ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረገው ህዝብ ፣ ለሀይማኖት አባቶች ፣ ለበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ፣ ለወጣቶችና በተለይ ደግሞ  የተሰጣቸውን ግዳጅ በሚገባ ለተወጡት የፀጥታ እና ደኅንነት ኃይሎች ምስጋና አቅርቧል።

በሌላ በኩል ፤ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ ጨምሮ በ2,575 የተለያዩ ደብሮችና ቦታዎች በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቀዋል።

ከንቲባዋ ፥ " በዓሉ በድምቀት እንዲከበር አስተዋፅዖ ላደረጉ የሀይማኖት አባቶች ፣ የከተማው ወጣቶች ፣ ሲያስተባብሩ ለነበሩ በየደረጃው ያሉ አመራሮች እንዲሁም ዶፍ ዝናብ ሳይበግራቸው በዓሉ ደማቅ በሆነ መንገድ እንዲከበር ላደረጉ የጸጥታ ሃይሎችና የከተማው ነዋሪዎች ሁሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋና እናቀርበላ " ብለዋል።

#የኢትዮጵያኦርቶዶክስተዋሕዶቤተክርስቲያን
#Ethiopia #AddisAbaba

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የዋጋ ጭማሪ የተደረገባቸው አገልግሎቶች ምን ምን ናቸው ?

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ ጭማሪ አድርጓል።

ተቋሙ በአንዳንድ አገልግሎቶች ላይ ያደረገው የዋጋ ጭማሪ ከፍ ያለ ነው።

ለአብነት ፦

° የተሽከርካሪ የዋጋ ግምት ማሳወቅ አገልግሎት 500 ብር የነበረው 1,000 ብር ገብቷል።

° የተሽከርካሪ የዋጋ ግምት ለሽያጭ አገልግሎት 2,310 ብር የነበረው 4,000 ብር ገብቷል።

° የተሽከርካሪ የባለቤትነት ስም ዝውውር አገልግሎት 3,000 ብር የነበረው 5,000 ብር ገብቷል።

° ለዓመታዊ ምርመራ ተለጣፊ ምልክት (ቦሎ) ግልባጭ ለመጀመሪያ ጊዜ 1,010 ብር የነበረው 2,500 ብር ተደርጓል።

° የተሽከርካሪ ባለቤት ማረጋገጫ ሊብሬ 300 ብር የነበረው 1200 ብር ተደርጓል።

° ሊብሬ ሲበላሽ ወይም ሲጠፋ ምትክ ፣ የማደሻ ቦታው ሲያልቅ መስጠት 3,000 ብር የነበረው 3,500 ብር ሆኗል።

° መረጃ መስጠት 300 ብር የነበረው 700 ብር ተደርጓል።

° አዲስ መንጃ ፍቃድ መስጠት 680 ብር የነበረው 1500 ብር ተደርጓል።

° ለጠፋ መንጃ ፍቃድ ማፈላለጊያ ለፖሊስ ወይም ለፕሬስ የሚሰጥ መረጃ 100 ብር የነበረው 700 ብር ተደርጓል።

° ከ3 ጊዜ በላይ የፅሁፍ ፈተና ለወደቁ በየወሩ ለመፈተን የሚሰጥ አገልግሎት 100 ብር የነበረው 300 ተደርጓል።

° ከ3 ጊዜ በላይ የተግባር ፈተና ለወደቁ በየወሩ ለመፈተን የሚሰጥ አገልግሎት ከ300 ብር ወደ 600 ብር ጨምሯል።

° የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ እድሳት ከ620 ብር ወደ 1000 ብር ገብቷል።

° ለጠፋ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ምትክ መስጠት 620 ብር የነበረው 5,000 ብር ገብቷል።

(ተጨማሪ በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ የተደረገውን የታሪፍ ጭማሪ ዝርዝር ከላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
" ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥምቅት 30/2017 ወደ ቤታችሁ ግቡ ፤ ይህ ካልሆነ የሽያጭ ውሉ እንዲቋረጥ ተደርጎ ቤቱን ለሌላ ዕድለኛ እናስተላልፋለን " - የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየገነባ ለቤት ተጠቃሚዎች በዕጣና በጨረታ የሚያስተላልፈው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን " በሽያጭ ከተላለፉና ውል ከተፈጸመባቸው ቤቶች መካከል የቤት ባለቤቶች ወደ ቤታቸው ገብተው እየኖሩ አለመሆኑን አረጋግጫለሁ " ብሏል።

" በህጋዊ መንገድ ውል የተያዘባቸው ቤቶች ለህገወጥ ተግባር እየዋሉ ነው " ያለው ኮርፖሬሽኑ ፥ የቤት ባለቤቶች ከኮርፖሬሽኑ ጋር በያዙት የሽያጭ ውል ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቤታቸው እንዲገቡ አስጠንቅቋል።

" በተባለው ጊዜ ውስጥ ወደ ቤቱ የማይገባ የቤት ባለቤት የሽያጭ ውሉ በህግ አግባብ እንዲቋረጥ ተደርጎ ቤቱን ለሌላ ዕድለኛ እናስተላልፋለን " ሲልም ገልጿል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia