TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#WFP #Ethiopia የግጭት ማቆም ውሳኔ ይፋ ከተደረገበት ከመጋቢት ወር ጀምሮ ወደ ትግራይ ክልል ከሚገባው እርዳታ #ከፍተኛ መጠን ያለው ቁሳቁስ በዚህ ሳምንት ወደ ክልሉ መግባቱን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል። በዚህ ሣምንት ወደ ትግራይ የገባው 15 ሺህ ቶን ምግብ እና ሌሎች የነፍስ አድን አቅርቦቶች ሲሆን አሁንም ተጨማሪ እርዳታ ወደ ክልሉ እያመራ መሆኑን WFP ገልጿል። ኤድሪያብ ቫን ደር…
#Afar

ሰይድ ሞሃመድ (የዓለም አቀፉ ህፃናት አድን ድርጅት የአፋር ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ዋና ኃላፊ) ለቪኦኤ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦

" ማህበረሰቡ ድብርብርብ ሸክም ነው የገጠመው ፤ የመጀመሪያው በርካታ የውሃ አቅርቦት እና ሌሎችም መሰረታዊ አገልግሎት ተቋማትን ስራ ያስተጓጎለው ፤ ያቋረጠው ግጭት በዚህ ላይ ድርቅ ሌላው ፈተና ነው።

ላለፉት በርካታ አመታት አፋር በተከታታይ በድርቅ ሲጠቃ ነው የቆየው ፤ ስለሆነም ድርቁ ለአፋር ማህበረሰብ ሌላ ፈተና ነው ማለት ይቻላል ። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ከ8 ወር በላይ ወደ ቄያቸው ያልተመለሱት የገደማይቱ ተፈናቃዮች የመፍትሄ ያለ እያሉ ነው። በገደማይቱ ሀምሌ 17 ቀን በነበረው ግጭት ምክንያት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ በርካታ ዜጎች እስካሁን ወደ ቄያቸው መመለስ አልቻሉም። እነዚህ ዜጎች በየመጠለያው ካምፕ እና በየዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው ወራት ማለፋቸውን ገልፀውልናል። " ዞር ብሎ የሚያየን እና የሚጠይቀን አጥተናል " ያሉት…
#Afar #Somali

ዛሬ በአዳማ ከተማ የአፋርና የሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ውይይት ማጠቃለያ መድረክ እየተካሄደ መሆኑን ለመስማት ተችሏል።

መድረኩ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት አላማ ያደረገ ነው ተብሏል።

በውይይቱ የሰላም ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ፣የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባን ጨምሮ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ይህን የሰሙ ከ9 ወር በላይ በግጭት ምክንያት ከገደማይቱ የተፈናቀሉ ወገኖች መፍትሄ እንዲያገኙ አቤት በለዋል። ችግር ተፈቶ ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱም ፣ ፍትህም እንዲያገኙ ጠይቀዋል።

በገደማይቱ ሀምሌ 17 በነበረው ግጭር ከመኖሪያ ቄያቸው የተፈናቀሉ ወገኖች ወደቄያቸው አልተመለሱም።

እነዚህ ዜጎች በየመጠለያ ጣቢያ እና ዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት የተጠለሉ ሲሆን ዞሮ ብሎ የሚያያቸው እና የሚጠይቃቸውን እንዳጡ ለ20 እና 30 ዓመታት ከኖሩበት ቄያቸው ተፈናቅለው ያለፍትህ ሜዳ ላይ መቅረታቸውን ገልፀው እንደነበር አይዘነጋም።

ዛሬም ድረስ ችግር ላይ የሚገኙ ወገኖች መፍትሄ እና ፍትህን ይሻሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somali #Afar #ሰላም #ውይይት

ትላንት የአፋርና የሱማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ኮንፈረንስ በአዳማ ተካሂዶ ነበር።

የሰላም ኮንፈረንሱ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት ዓላማ ያደረገ ነው መሆኑን ሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።

በአካባቢዎቹ የሚታዩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ሰላምን ለማምጣት ወደ ግጭት ለሚያመሩ ጉዳዮችም መፍትሔዎች ተለይተው የተቀመጡበት መድረክ ነው ተብሏል።

የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ፤ በግጭት ምክንያት ከኖሩበት ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው እየኖሩ ችግሮችን እየተጋፈጡ ያሉ ወገኖች ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ሊደረጉ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም በመድረኩ መነሳቱን ከሰላም ሚኒስቴር በኩል የወጣው መረጃ ያሳያል።

ባለፈው ዓመት በተነሳ ግጭት ከዘጠኝ ወር በላይ ቤታቸው ተፈናውለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በየዘመዶቻቸው ቤት የተጠለሉ በርካታ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
#Afar

ከትላንትና በስቲያ ፤ በአፋር ክልል ጭፍራ ወረዳ ከምሽት 1 ሰዓት አንስቶ ለሊቱን ሙሉ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ በተለያዩ የቤት እንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል።

የክልሉ አደጋ መከላከልና ስጋት አመራርና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን ለኢዜአ በሰጠው ቃል ፤ ሀሙስ ከምሽቱ 1 ሰአት ጀምሮ ሌሊቱን ሙሉ በጣለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ምክንያት ፦

👉 13 ሺህ 834 ፍየል እና በግ፣
👉 180 የቀንድ ከብት፣
👉 20 ግመሎች እና 3 አህዮች ሞተዋል።

በክልሉ ባለዉ ድርቅ የቤት እንስሳዎቹ በመኖ እጥረት የተጎዱ በመሆናቸዉ ዝናቡን መቋቋም አለመቻላቸው አደጋውን የከፋ አድርጎታል ተብሏል።

በወረዳው ደርጌራ ፣ አፉማና ወአማ ቀበሌዎች በዝናቡ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።

የቤት እንስሳቶቻቸው ለሞቱባቸው ቤተሰቦች ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ተገልጿል።

የጭፍራ ወረዳ አርብቶ አደር ጽ/ ቤት በበኩሉ ፤ ከወረዳዉ ስፋት ጋር በተያያዘ ገና መረጃ እየተሰበሰበ የሚገኝ በመሆኑ የሞቱ የቤት እንሰሳዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ለኢዜአ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ ከግንቦት 15 እስከ 20/2014 ዓ.ም በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር ተያይዞ " ለደኅንነታቸው ጥበቃ እና በወንጀል ጥርጣሬ የሚፈለጉ ሰዎችን ለመለየት " በሚል ምክንያት ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች ፦ - ከአባላ - ከኮነባ - ከበረሃሌ…
#Afar

በአፋር ክልል በሰመራ ከተማ በሚገኝ የማቆያ ካምፕ ውስጥ #ያለፈቃዳቸው ተይዘው ከነበሩት የትግራይ ተወላጆች መካከል የተወሰኑት በአውቶብሶች እና የደረቅ ጭነት መኪኖች ተሳፍረው ወደ ቀደመ መኖሪያቸው እየተወሰዱ እንደሆነ መግለፃቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።

በሺዎች የሚቆጠሩት የትግራይ ተወላጆች ከአፋሯ አብኣላ ተይዘው ወደ ሰመራ ተዘዋውረው የነበረ ሲሆን  ከ8 ወራት እስር በኋላ ወደ አብኣላ እየተመሰሉ መሆኑን ተናግረዋል።

በሰመራ ተይዘው የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን "በብሔር ማንነት ላይ የተመሰረተ ሕገ ወጥ እና የዘፈቀደ እስር በመሆኑ በአፋጣኝ ሊለቀቁ ይገባል ብሎ ነበር።

https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/71528?single

የትግራይ ተወላጆቹ ቀደሞ ወደሚኖሩበት የመኖሪያ ስፍራቸው እንዲመለሱ እያመቻች የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት (OCHA Ethiopia) መሆኑ የተነገረ ሲሆን ድርጅቱ ሰዎቹን " የአገር ውስጥ ተፈናቃይ (IDP) " ሲል ገልጿቸዋል።

ዜጎችን ወደነበሩበት ቦታ የመመለሱ ስራ በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚቀጥልም ገልጿል።

ነገር ግን ተመድ ባሰራጨው መረጃ ላይ በርካቶች በቃል አጠቃቀሙ ላይ ያለቸውን ተቃውሞ የገለፁ ሲሆን እነዚህ ተይዘው የነበሩት ዜጎች " ያለአንዳች ፍላጎታቸው በመውሰድ ነው " እንጂ የውሥጥ ተፈናቃይ አይደሉም ብለዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩት እዚህ ዜጎች ለወራት ተይዘው በቆዩበት ካምፕ ውስጥ የምግብ እና ሌሎች አገልግሎቶች ችግሮች እንደነበሩባቸው የተናገሩ ሲሆን ለተለያዩ የጤና ችግሮች ተጋልጠው መቆየታቸውን እንደገለፁለት ቢቢሲ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#Oromia #Afar

ዛሬ በኦሮሚያ ክልል እና በአፋር ክልል በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ11 ሰዎች ህይወት አልፏል።

በኦሮሚያ ክልል አደጋው የደረሰው በምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ ሲሆን በአደጋው የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል።

ከ6 ሟቾች በተጨማሪ 15 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።

አደጋው ከአዳባ ከተማ ወደ ላጆ ከተማ ሲጓዝ በነበረ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ አይሱዙ መኪና በመገልበጡ የተከሰተ ነው።

መኪናው የመጫን ልኩ 28 ሰው ብቻ የነበረ ቢሆንም ከመጠን በላይ በመጫን 40 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ አደጋው መድረሱ ተገልጿል፡፡

በአፋር ክልል ደግሞ የትራፊክ አደጋ የደረሰው በሎጊያ ከተማ ሲሆን መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል።

ተሽከርካሪው ጥዋት ከሎጊያ 15 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ አፍዴራ ሲጓዝ ኮሪ ወረዳ ልዩ ቦታው " ጉያህ " ላይ ተገልብጦ ነው አደጋው የደረሰው።  5 ሰዎች ወዲያው ህይወታቸው ሲያልፍ 10 ሰዎች ቀለል እና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው።

አሸክርካሪዎች ይዛችሁ የምትጓዙት ክቡር እና የማይተካውን የሰው ህይወት ነው እና ሁሌም ጥንቃቄ ማድረግ፣ ህግ እና ስርዓትን ማክበር አትዘንጉ።

@tikvahethiopia
#Tigray #Afar

የዓለም ምግብ ፕሮግራም በሎጅስቲክስ ክላስተር ትብብር ወሳኝ የሆኑ ህይወት አድን ድጋፎችን በአየር መቐለ መድረሳቸውን አሳውቋል።

መቐለ በአየር ከደረሰው ህይወት አድን ድጋፍ መካከል የUNICEF ክትባቶች እና በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለተጎዱ እናቶች እና ህፃናት የሚውል የዓለም ምግብ ፕሮግራም ድጋፍ የተካተተበት ነው።

UNICEF ይፋ ባደረገው መረጃ 1.4 ሚሊዮን ዶዝ ክትባቶችን መቐለ ደርሷል። ክትባቶቹ በክልሉ 50,000 ህጻናትን እና እናቶችን ለመከተብ እንደሚውሉ የሚውሉ ናቸው ተብሏል። መቐለ ከደረሱት ክትባቶች አሁን ላይ በክልሉ ላሉ ጤና ጣቢያዎች እየተከፋፈሉ መሆኑ ተገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ በዩናይትድ ኪንግደም ድጋፍ በሰሜን ምዕራብ አፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የምግብ እርዳታ የያዙ ተሽከርካሪዎች ስለመንቀሳቀሳቸው ተሰምቷል።

እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች በዓለም ምግብ ፕሮግራም በኩል እንዲደረስ በዩናይትድ ኪንግደም የተሰጠው ወሳኝ የሆኑ ህይወት አድን ድጋፎችን የያዙ 54 ተሽከርካሪዎች መሆናቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#Afar

የዲጂታል ቴክኖሎጂን ለሰላምና ግንባታ የመጠቀም ልምድ ደካማ በሆነበት ሁኔታ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ሀሰተኛና የጥላቻ ንግግሮች ጉዳታቸው ትልቅ ነው።

በተለይ እነዚህ አደገኛ መረጃዎች በከተማም ሆነ ከተማ ወጣ ባሉ አከባቢዎች የሚፈጥሩት ተጽዕኖ ከፍ ያለ ነው።

ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ከጥር 13 ጀምሮ ለ4 ቀናት በዲጂታል ሰላም ግንባታ እንዲሁም መሰረታዊ የሚዲያ ክህሎት ላይ ትኩረቱን መሰረት ያደረገው የአሰልጣኞች ስልጠና (TOT) በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ተካሂዷል።

በስልጠናው 20 ወጣቶች ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን ከክልሉ 4 ወረዳዎች (አሚባራ፣ አፋንቦ፣ ጭፍራ፣ ገዋኔ) ለተወጣጡ ሰልጣኞች የዲጂታል ሚዲያ ክህሎትን ስለማሳደግ፣ የሰላም ግንባታ ሥራዎችን ስለመስራትና ከሀሰተኛና ጥላቻ ንግግሮችን ራስንና ማኅበረሰብን ስለመከላከል በዚህም ምክንያት የሚደርስን ጉዳት መቀነስ በሚቻልበት አግባብ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል።

በቀጣይም ወጣቶቹ በወሰዱት ሥልጠና መሰረት ወደ ማኅበረሰባቸው ተመልሰው ለሌሎች እኩዮቻቸው ተመሳሳይ ሥልጠናዎችን እንዲሰጡ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በአከባቢያቸው አወንታዊ ተጽዕኖ እንዲፈጥሩ ለማስቻል ታቅዷል።

በተለይ የመረጃ ተደራሽነቱ በተለያዩ ምክንያቶች ለተገደበባቸው አከባቢዎች መሰል የአቻ ሥልጠናዎች ትርጉም ያለው ለውጥ ከማምጣቱም በዘለለ ወጣቱን አሳታፊ ያደረገ የመፍትሔ ሀሳቦች ተግባራዊ እንዲሆኑ እድሉን በሰፊው ያመቻቻል።

ይህንን ስልጠና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ Mercy Corps Ethiopia ጋር በጋራ በመሆን ለሥልጠናው ከሚያስፈልገው የሥርዓተ ትምህርት ቀረጻ ጀምሮ በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።

በቀጣይ በድሬደዋና በጅጅጋ ከተሞች መሰል ሥልጠናዎችን የሚሰጡ ይሆናል።

@tikvahethiopia
#Afar

15ኛው የአፋር ሱልጣን በዓለሲመት ሰኞ ይከናወናል።

የፊታችን ሰኞ መጋቢት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ሱልጣን አህመድ አሊሚራሕ  15ተኛው የአፋር ሱልጣን በመሆን  በዓለሲመታቸው እንደሚከናወን የአፋር ማስ ሚዲያ ኤጀንሲ ዘግቧል።

ለዚሁ በዓለሲመት ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ ዛሬ አዲስ አበባ  ገብተዋል። አዲስ አበባ ሲገቡ ከፍተኛ  አመራሮች ተገኝተው  አቀባበል አድርገውላቸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar 15ኛው የአፋር ሱልጣን በዓለሲመት ሰኞ ይከናወናል። የፊታችን ሰኞ መጋቢት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ሱልጣን አህመድ አሊሚራሕ  15ተኛው የአፋር ሱልጣን በመሆን  በዓለሲመታቸው እንደሚከናወን የአፋር ማስ ሚዲያ ኤጀንሲ ዘግቧል። ለዚሁ በዓለሲመት ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ ዛሬ አዲስ አበባ  ገብተዋል። አዲስ አበባ ሲገቡ ከፍተኛ  አመራሮች ተገኝተው  አቀባበል አድርገውላቸዋል። @tikvahethiopia
#Afar

ቀጣይ የአውሳ ሱልጣኔት አልጋወራሽ እንደሚሆኑ የሚጠበቁት ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ በዓለሲመታቸዉን ለመከወን ዛሬ  የአፋር መዲና፣ ሰመራ መግባታቸውን የአፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል።
   
ሱልጣን አህመድ አልሚራህ ሰመራ ሲደርሱ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመሬሮችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች አቀባባል አድርገዉላቸዋል።

በዓለሲመቱ የሰኞ መጋቢት 4 ቀን 2015 ዓ/ም በአውሳ ሱስለጣኔት መናገሻ በሆነችው አይሳኢታ ከተማ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከናወን ይጠበቃል።

በእለቱ ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከሚገኙ እና በጀቡቲና ኤርትራ የሚገኙ የአፋር ማህበረሰብ ባህላዊ መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸዉ ሰዎች እንዲሁም የፌድራልና የክልሉ መንግስት አካላት አምባሳደሮች እንደሚገኙ ይጠበቃል ተብሏል።

#አፋብመድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar ቀጣይ የአውሳ ሱልጣኔት አልጋወራሽ እንደሚሆኑ የሚጠበቁት ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ በዓለሲመታቸዉን ለመከወን ዛሬ  የአፋር መዲና፣ ሰመራ መግባታቸውን የአፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል።     ሱልጣን አህመድ አልሚራህ ሰመራ ሲደርሱ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመሬሮችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች አቀባባል አድርገዉላቸዋል።…
#AFAR

ሱልጣን አህመድ አሊሚራህ 15ኛው የሀውሳ ሱልጣኔት ሱልጣን ሆነው በዓለ ሲመታቸው ዛሬ ተከናወነ።

በበዐለ ሲመቱ ላይ ፦ በርካታ ነዋሪዎች፣ በጅቡቲ እና ኤርትራ የሚኖሩ የአፋር ህዝብ ተወካዮች፣ የአርጎባ ህዝብ አመራሮች ተገኝተው ነበር።

በተጨማሪ ፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ፣ የአፋር ክልል ርዕሠ መስተዳደር ሀጂ አወል አርባ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ ከፍተኛ የፌደራል መንግሥት የስራ ሀላፊዎች ፣ አምባሳደሮች በበዓለ ሲመቱ ተገኝተው ነበር።

Photo Credit : Argoba Community Radio

@tikvahethiopia
#Afar

" ከጨው ፓለቲካ ጋር በተያያዘ ከ1,700 በላይ ሰዎች ታስረዋል " - የዶቢ ጨው አምራቾች ማኅበር

" ከጨው ፓለቲካ ጋር በተያያዘ ከ1,700 በላይ ሰዎች ታስረዋል" ሲል በአፋር ክልል የሚገኘው የዶቢ ጨው አምራቾች ኃላ/የተ/የግል/ሕብረት ሽርክና ማኅበር ገለጸ።

ሰዎቹ የታሰሩት የት ማረማያ ቤትና ለምን እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበለት ጥያቄ ማኅበሩ፣ " የታሰሩት በሰመራ ማረሚያ ቤት ነው፣ የታሰሩበት ምክንያት ደግሞ ጨው ለማምረት በመከልከላቸው ቅሬታ ሲያቀርቡ ነው " ብሏል።

ማኅበሩ እንዳስረዳው ፤ 409 አባላቱ ጨው እንዳያመርቱ በመንግሥት መታገዳቸውን፣ የታገዱበት ምክንያትም እንዳልተነገራቸው ነው።

የሚኅበሩ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሁሴን አሊ የማኅበሩ አባላት በችግር ላይ መሆናቸውን ገልጸው፣ በክልሉ ብዙ #ሙስና እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ ፤ በጨው ማምረት ሥራ የተሰማሩት በክልሉ የሚገኙ አመራሮች ብቻ ናቸው ብለዋል።

የማኅበሩ አባላት በተናጠልና በጋራ እንደገለጹት ፣ ክልከላው እንዲነሳ  ለሚመለከታቸውን የክልሉ የመንግሥት አካላት ተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም አጥጋቢ ምላሽ አላገኙም።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ በማኅበርና በየፊናቸው በሰጡት ገለጻ፣ በዚህ ሳቢያ በአፋር ክልል ግጭት ከመፈጠሩ በፊት የፌደራል መንግሥት አፋጣኝ መፍትሄ ይስጠን ሲሉ ጠይቀዋል።

ከዚህም ባሻገር ጨው አምራቾች ምርታቸው የሸጡበት የስድስት ወራት ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ፣ የማኅበሩ አባላት በየፊናቸውና በማኅበር በሰጡት ገለጻ አስረድተዋል።

በሌላ በኩል ፤ በክልሉ በተከሰተው ድርቅ " ተርበናል " ብለው የሚጠይቁ ሰዎች በፓሊስ እየታሰሩ መሆኑን ማኅበሩ አስታውቋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ በክልሉ የተለያዩ ቦታዎች ሰዎች በርሃብ እየሞቱ ነው ብለው፣ ለአብነትም በአፍዴራ ሰሞኑን ሁለት ሰዎች ሞተዋል ብለዋል።

ዶቢ የጨው አምራች ማኅበር ኃላ/የተ/የግል/ሕብረት ሽርክና ማኅበር በአፋር ክልል በ1992 ዓ.ም በባህላዊ የምርት አሰራር የተመሰረተና በሂደት ወደ ዘመናዊነት የተሸጋገረ 409 አምራች አባላት ያሉት ማኅበር ነው።

መረጃውን የአዲስ አበባ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው ያዘጋጀው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Afar #Somali🚨

" የግጭቱ ማገርሸት ለሰላማዊ ሰዎች ግድያ እና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል " - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋር እና ሶማሌ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት ማገርሸቱ ገልጿል።

ኮሚሽሙ ግጭቱ እንዳሳሰበውም አመልክቷል።

ኢሰመኮ በቅርቡ በሚያዚያ ወር የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ በሶማሊ ክልል ሽንሌ ዞን እና አፋር ክልል አዋሳኝ ያገረሸው ግጭት አሳሳቢ ነው ብሏል።

ግጭቱ ለሰላማዊ ሰዎች ግድያ እና መፈናቀል ምክንያት እንዳሆነ ገልጿል።

በኮሚሽኑ የጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ሰኢድ ደመቀ ለዶይቼ ቬለ በሰጡት ቃል ፤ " የአሁኑ ግጭት የተጀመረው ከግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም 2024 ወዲህ ነው " ብለዋል።

" በግጭቱ የተወሰኑ ሰዎች ሞት፤ መፈናቀል እና የአካል ጉዳት፤ የንብረት መውደም እንደደረሰ ነው ያለው መረጃ በእኛ በኩል ግጭቱ እንዳገረሸ። በትክልል ስንት ሰው ሞተ፤ ቆሰለ የሚለውን ገና በምርመራ የምናጣራው ነው " ብለዋል።

" በአሁኑ ወቅት ግን ጠቅለል ባለ መልኩ የሰው መፈናቀል፤ ሞት እና ጉዳት እንዳለ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ኢሰመኮ ከሁለቱ ክልሎች የመንግስት አስተዳዳሪዎች ተረዳሁት ባለው መሠረት ፥ በሁለቱም ክልሎች በኩል የሰላማዊ ሰዎች ግድያ እና መፈናቀሎች ተፈጽሟል።

በቅርቡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለተገኘው አዎንታዊ የሰላም ማስፈን ሂደት ሁለቱ ክልሎች ያሰጡትን አዎንታዊ ምላሽ ያደነቀው ኢሰመኮ፤ የተጀመረው የሰላም ጥረት እንዲቀጥል የፌዴራልም ሆነ የሁለቱ ክልሎች መንግስታት የቀጠለውን ግጭት እንዲያስቆሙት ጥሪውን አቅርቧል።

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የፌዴራል መንግስት አስቸኳይ የግጭት ማስቆም ጥረት እንዲያስደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

የሁለቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በቀጣይ ሕዝበ ሙስሊሙ ከሚያከብረው የኢድ አል-አደሃ በዓል አስቀድሞ ሰላም እንዲሰፍን ጥረት እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።

#DWAmharic #EHRC

@tikvahethiopia