TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬆️

በአዲስ አበባ #በካርቶን የታሸገ 3 ሚሊዮን 5 መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር እና 61400 የአሜሪካ #ዶላር በነሐሴ ወር 2010 ዓ/ም #መያዙን የከተማይቱ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የቻይና ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦች ከቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን በየቀኑ ማታ ማታ በካርቶን የታሸጉ ብሮች ያወጡ እንደነበር ከአስራ አምስት ቀን በላይ ከፈጀ #ጥብቅ ክትትል በኋላ ፖሊስ ደርሶበታል፡፡

ነሀሴ 28 ቀን 2010 ዓ/ም ምሽት ላይ መነሻዋን ከቦሌ ሻላ ያደረገች ፕራዶ መኪና ወደ ቦሌ ሩዋንዳ ታመራለች፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የክትትልና ኦፕሬሽን ክፍል አባላትም መኪናዋን በቅርብ ርቀት መከታተል ይጀምራሉ፡፡

ፕራዶዋ ቦሌ ሩዋንዳ ከአንድ ሰዋራ ቦታ ትደርስና ከአንዲት ነጭ ዶልፊን መኪና አጠገብ ትቆማለች፡፡

ከዚያም ከፕራዶዋ ውስጥ የነበሩት ተጠርጣሪዎች በካርቶን የታሸጉት የገንዘብ ኖቶችን ወደ ዶልፊነኗ ሲያዛውሩ በክትትል ቡድኑ በቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡

በዕለቱ በቁጥጥር ስር የዋሉት ቀደም ሲል የተጠቀሱትና የቻይና ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦችና አንድ ኢትዮጵያዊ ግብረአበራቸው በድምሩ 3 ተጠርጣሪዎች ናቸው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በወቅቱ ለክትትል ፖሊስ አባላቱ 2 ሁለት ሚሊየን ብር እንስጣችሁነና ልቀቁን ሲሉ ተማፅነዋቸዉ የነበረ ቢሆንም የፖሊስ አባላቱ ግን ቀጥታ ጉዳዩን ለኃላፊዎቻቸው በመንገር ከእነ ኤግዚቢቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተነግሯል፡፡

©ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ‼️

በአዲስ አበባ በህገወጥ መንገድ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን #በሚመነዝሩ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ከ2 ሚሊየን የሚበልጥ የኢትዮጵያ ብር እና የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችን #መያዙን የከተማዋ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

ታህሳስ 26 እና 27 ቀን 2011 ዓመተ ምህረት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ኢትዮጵያ ሆቴልና ጋንዲ አካባቢ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ገንዘቦቹን መያዛቸውን ኮሚሽኑ ለfbc በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ከዚህ በፊት በአካባቢዎቹ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ለምንዛሪ የተዘጋጁ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችና የኢትዮጵያ ብር መያዙን ኮሚሽኑ በመግለጫው አስታውሷል።

ሁለቱ ተቋማት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ተጠርጥረው የተያዙ አምስት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ነው ያስታወቀው።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመግታት ከባለድርሻ አካላት እና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ተግባሩን እንደሚቀጥል በመግለፅ፥ የከተማው ነዋሪ ይህ ጥረት እንዲሳካ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ጠይቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካሥቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአንድ ፒካፕ ተሽከርካሪ ላይ በተደረገ ፍተሻ ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓጓዙ የነበረ ሦስት መትረየስ፣ 1924 የስታር እና 1856 የማካሮቭ ሽጉጥ ጥይቶች ከ37 የጥይት መያዥ ጋር #መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 20/2011 ዓ.ም.

የጀርመን ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር #ፍራንክ_ዋልተር_ሽቴይንሜይር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።
.
.
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀድሞ አፈ ጉባኤ አቶ #ዳዊት_ዮሃንስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
.
.
ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል #የደም_ስር_መጥበብ ችግር ላለባቸው ታካሚዎች ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የፒሲአይ የነጻ ህክምና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
.
.
ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ ኢትዮጵያን እየጎበኙ ካሉት ከጀርመን ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ዋልተር ስታይንማየር ልዑካቸውን ተቀብለው አነጋግረዋል።
.
.
ለኢፌድሪ ፕረዝዳንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ታከለ ኡማ(ኢ/ር) የEuropean Tourism Academy Membership ሽልማት ሊሠጥ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ በ2011 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 4 ሚሊየን 234 ሺህ 856 መቶ ተሸከርካሪዎች በማስተናገድ በአጠቃላይ ብር 124 ሚሊየን 578 ሺህ 594 መቶ ብር መሰብሰብ መቻሉ ተሰምቷል።
.
.
#አለን_ኢትዮጵያ የበጎ-አድራጎት ድርጀት የሰው ልጆች የለውጥ ማዕከል ህጋዊ እውቅና በማግኘት ትላንት በ19/05/01 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ሥራ ጀምሯል።
.
.
በአንድ ፒካፕ ተሽከርካሪ ላይ በተደረገ ፍተሻ ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓጓዙ የነበረ ሦስት መትረየስ፣ 1924 የስታር እና 1856 የማካሮቭ ሽጉጥ ጥይቶች ከ37 የጥይት መያዥ ጋር #መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
የጀርመኑ ግዙፍ የመኪና አምራች ኩባንያ ቮልስዋገን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
.
.
የሚድሮክ ግሩፕ የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲንን ከእስር #መፈታትን ምክንያት በማድረግ ሠራተኞቹን #አንበሻብሿል
.
.
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለሙስና ተጠርጣሪው የጄኔራል ክንፈ ዳኘው ወንድም #ኢሳያስ_ዳኘው ፈቅዶት የነበረውን የዋስትና መብት ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሻረው ካፒታል ዘግቧል፡፡
.
.
ጠ/ሚር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ዛሬ ምሽት #በብሄራዊ_ቴአትር በየሶስት ወሩ የሚካሄደውን የኪነ ጥበብና የባህል ምሽት ተካፍለዋል።
.
.
ሚድሮክ ኢትዮጵያ የሼክ ሞሃመድ አላሙዲን መፈታት አስመልክቶ፦ የሚድሮክ ንብረት በሆነው #ዩኒቲ_ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ተማሪዎች ላንድ ወሰነ ትምህርት(1 ሴሚስተር) #በነጻ እንዲማሩ ፈቅዶላቸዋል፡፡
.
.
ምንጭ፦ ዋልታ፣ ፋና፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ሬድዮ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
የነገ ሰው ይበለን!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

ሰባት ኪሎግራም ወርቅና ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ሃገራት ገንዘብ #መያዙን ገቢዎች ሚኒስቴር ገለፀ። አራት ተጠርጣሪዎችም #በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

የገቢዎች ሚኒስቴር #ቶጎ_ውጫሌ ኬላ ላይ ሰባት ኪሎ ግራም ወርቅና ከፍተኛ መጠን ያለው የውጪ አገር ገንዘብ መያዙን ገልጿል።

የአሜሪካ፣ የካናዳና የአውስትራሊያ ዶላር፣ ዩሮ፣ ድርሃምና የሌሎች ሃገራት ገንዘብ ነው የተያዘው ብሏል ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ።

ትናንት ምሽት ሰባት ኪሎ ግራም ወርቅና መጠኑ ከፍተኛ የሆነ የውጪ አገር ገንዘብ ከአራት ተጠርጣሪ ኮንትሮባንዲስቶች ጋር በቶጎ ዉጫሌ ኬላ በጉምሩክ ሰራተኞች ተይዟል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia